በባህላችን የሰው ስም በትርጉም አልባነት እንደማይለጠፍ፤ ከሰውነታችን ጋራ የሚገናኙ ነገሮችም ስማቸው ከመነሻቸው ጋራ የተያያዘ ነው። “እንጀራ” ከምድራዊ ህይወታችን ጋራ ከተገናኙት መሠረታውያን ነገሮች አንዱ ነው። እንጀራ እስካሁን ድረስ የተነሳበትን የታሪክ ትዝታ ተሸክሞ ብዙ ዘመን ተጉዟል። እንጀራ ከወላጅ እናቱ ከጤፍ ጋራ በመተባበር ከኢትዮጵያና ከህዝቧ ጋራ ያላቸው ግንኙነት ሩቅና ጥልቅ ትስስር እንዳለው ሁሉ፤ ከመብላት ስሜትና ሱስ ጋራ ተዋህዶ በሰውነታችን ስለጋባ፤ ዝንት ዓለም የኖረ ይህን ጥብቅ ግንኙነት የሚያስለቅቅ፤ ጥብቅ ምክንያት መቅረብ ያለበት ይመስለኛል። ከኢትዮጵያ እየተጫነ የሚመጣውን እንጀራ አትብሉ ወደሚለው ሀሳብ ምን እንደወሰደን በግልጽ ለማቅረብና፤ እንዴትስ እናቁም ወደ ሚለው ውይይት ለመግባት፤ ከጉባዔ ትምህርት ቤት መምህራን የሰማሁትን ለውይይታችን መንደርደሪያ … [Read more...] about እርም (ሐራም)
Right Column - Primary Sidebar
“ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፕሮግራሙን ይፋ አደረገ
ጥቅምት 12 ቀን 2007 ዓ.ም 9 ተቃዋሚ ፓርቲዎች የመሰረቱት ትብብር "ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ" በሚል ለአንድ ወር የሚቆይ የመጀመሪያ ዙር የህዝባዊ ትግል ፕሮግራሙን ዛሬ ጥቅምት 25/2007 ዓ.ም በሰማያዊ ፓርቲ ጽ/ቤት ይፋ አደረገ፡፡ "ነጻነት በሌለበት ፍትሃዊ ምርጫ የማይታሰብ በመሆኑ የተዘጋውን በር ለመክፈት የ‹ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ› በሚል የፕሮግራም መርሃ ግብር ለመክፈት ወስኖ የመጀመሪያው ዙር እንቅስቃሴ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ" እንዳዘጋጀ ያሳወቀው ትብብሩ የትግሉ ዓላማ ፍትሃዊ ምርጫ እንዲኖር የሚያስችል መሆኑን ገልጾአል፡፡ "ምርጫ ቦርድ ለገዥው ፓርቲ ያለውን ወገናዊነትና ጉዳይ አስፈጻሚነት ፍንትው አድርጎ አሳይቷል" ያለው መግለጫው በመጀመሪያ ዙር የአንድ ወር ፕሮግራሙ 6 ዋና ዋና ተግባራትን ለመፈጸም ዝርዝር እቅዶችን አውጥቶ ዝግጅቱን ማጠናቀቁን … [Read more...] about “ነጻነት ለፍትሃዊ ምርጫ” የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ፕሮግራሙን ይፋ አደረገ
መንግስት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ገጥሞታል
የኢትዮጵያ መንግስት ከፍተኛ የሆነ የውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደገጠመው የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገለጹ፡፡ አንድ ስማቸውን መግለጽ ያልፈለጉ የብሄራዊ ባንክ ከፍተኛ የኢኮኖሚ አጥኚ እጥረቱ መኖሩን አረጋግጠዋል፡፡ ከ20 ቀናት በፊት እያንዳንዱ የንግድ ባንክ ቅርንጫፍ የውጭ ምንዛሬ ይሸጥ እንደነበር የተናገሩት ምንጮች፣ ከ20 ቀን ወዲህ ግን በሁሉም የንግድ ባንክ ቅርንጫፎች ማንኛውም አይነት የውጭ ምንዛሬ እንዳይሸጥ በደብዳቤ (circular ዞሯል) ተከልክሏል፡፡ በመሆኑም አሁን ላይ ዜጎች በውጭ ምንዛሬ እጥረት እንደተቸገሩ ለማወቅ ተችሏል፡፡ "በተለየ ሁኔታ የሚሸጥላቸው ሰዎች ከጉዞ ወኪላቸውና ከበላይ አካል ይዘውት በሚመጡት ደብዳቤ መሰረት ብቻ ነው ምንዛሬ ሊያገኙ የሚችሉት፡፡ ከዚህ ውጭ ግን እንደበፊቱ ማንም የውጭ ምንዛሬ ማግኘት አይችልም" ሲል አንድ የንግድ ባንክ ሰራተኛ … [Read more...] about መንግስት ከፍተኛ የውጭ ምንዛሬ እጥረት ገጥሞታል
በአንድነት ተሰባስበን መታገሉ ግዴታችን ነው
ውድ ኢትዮጵያዊ ድረገጽ፤ ከታች ያለውን ደብዳቤ ለግለሰቦች መላክ ፈለግሁና፤ ለማን ልላክ ብዬ ካወጣሁ ካወረድኩ በኋላ፤ የተወሰኑ ስሞችን ሰበሰብኩ። እኒህን ለይቶ ማውጣቱና፤ እኒህ ብቻ ናቸው ብሎ መለየቱ አሳሰበኝ። ማን ማንን ይወክላል? ሌላውስ ላለመወከሉ ምን መከላከያ አለኝ? እኒህን ለመሰሉ ጥያቄዎች፤ አመርቂ አልስ መሥጠት አልቻልኩም። ለምን በጠቅላላው በትግሉ ላይ ለተሰማሩ ኢትዮጵያዊያን በሙሉ፤ ይኼ ኃላፊነት አለብን በማለት አልልክላቸውም? የሚለው ውሳኔ አስታራቂ ሆነልኝ። በየቦታው ኢትዮጵያዊያን እየታገሉ ነው። ይኼን ትግል ወደ አንድ ማዕከል ማምጣቱ ነው የዕለቱ ጥያቄ። በሃይማኖት ተከታዮች በኩል የሚደርሰው በደል፣ በትውልድ ሐረጋቸው የተነሳ የሚደርስባቸው በደል፣ በተሰማሩበት የንግድ መስክ የተነሳ የሚደርስባቸው በደል፣ በመኖሪያ አካባቢያቸው፣ ለንግድ ተብሎ ከቦታቸው በሚፈናቀሉት … [Read more...] about በአንድነት ተሰባስበን መታገሉ ግዴታችን ነው
የምዕራባዊያን የሕክምና ማዕከላት የሴት ልጅ ግርዛትን ተቀበሉ በስፋትም እየፈጸሙ ነው!
ምዕራባዊያኑ በኛ ላይ ያላቸው ዓላማ ምንድን ነው? በእርግጥም ጽሑፉን ካነበባቹህ በኋላ እንደኔ ሁሉ እናንተም “ምዕራባዊያኑ በእኛ ላይ ያላቸው ዓላማ ምንድን ነው?” እንደምትሉ አልጠራጠርም፡፡ ይሄንን እንድል ያስገደደኝ ጉዳይ አንድ ህክምና ላይ አተኩሮ ጽሑፎችን የሚያትም መካነድር ላይ አንድ ይዝ (ሊንክ) ተጠቁሞ አገኘሁና ከፈትኩት ከዚያ እላቹህ ፈጽሞ ያላሰብኩትና ያልጠበኩት እጅግ ደግሞ የገረመኝን ነገር አገኘሁ፡፡ ምዕራባዊያኑን ስናውቃቸው ብዙ ነገሮችን እያወሩ የሴት ልጅ ግርዛትን ከእኛና እኛን ከመሰሉ ሀገራት ሁሉ “ጎጂ ባሕል” በማሰኘት ለማስቀረት ምንያህል እንደደከሙና እያስቀሩትም እንደሆነ ለሁላችንም ግልጽ ነው፡፡ ይሄንን አየሁት ያልኳቹህን ይዝ (ሊንክ) ካየሁት በኋላ ግን እነዚህ ሰዎች ወይ ስለኛ ግርዛት ምንም በማያውቁት ነገር ላይ ነው የሚዘባርቁት ወይ ደግሞ ከሚሉን ነገር … [Read more...] about የምዕራባዊያን የሕክምና ማዕከላት የሴት ልጅ ግርዛትን ተቀበሉ በስፋትም እየፈጸሙ ነው!
The Ethiopians and their recent history
We all repeat by rot that our country is three thousand years old. It has always been like that ever since I remember. Not a single year more or one day less. I doubt anyone knows the details but we all seem to be happy repeating that mantra. I am not going to argue nor go on a fishing expedition to prove it right or wrong. To tell you the truth I am very comfortable with that aspect of our history. We are poor, when it comes to technology we are very backward, we still experience real famine … [Read more...] about The Ethiopians and their recent history
አዲስ አበባ ውስጥ ሌሊት የሚለጠፉ ወረቀቶችን ተከትሎ ውጥረት ነግሷል
የበር መብራት ማጥፋት ክልክል ነው፤ በሕግ ያስቀጣል “መውጫና መግቢያ ሰዓታችሁ መመዝገብ ይጀመራል ተብለናል” ነዋሪዎቹ ከትናንት በስቲያ በጨርቆስ አካባቢ አንድ ሰው በአሰቃቂ ሁኔታ ተገድሎ መገኘቱን እና ሌሊት ላይ በቦሌ አካባቢ የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችን የሚያስተጋቡ ወረቀቶች በየግድግዳውና የኤሌክትሪክ ምሶሶ ላይ ተለጥፈው መገኘታቸውን ተከትሎ በከተማዋ ውጥረት መንገሱን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡ “አንድ የጨርቆስ አካባቢ ነዋሪ ተገድሎ መገኘቱን ተከትሎ ‹የጨርቆስ ወጣቶች› ተሰባስበው ይህን ድርጊት ይፈጽሙ ይሆናል ብለው በገመቱት ላይ ቁጣቸውን ገልጸው ነበር፡፡ በተለምዶ ካታንጋ ወደሚባል ስፍራ ሄደው ገዳዩን አውጡ ብለዋል፡፡ መኪኖችን ሰባብረዋል፡፡ ካታንጋ ምንም ፍንጭ ሲያጡ ወደ ፊላሚንጎ አምርተዋል፡፡ በዚህ ጊዜ ፖሊስ የተወሰኑትን ይዟል፤ ያመለጡም አሉ፡፡ … [Read more...] about አዲስ አበባ ውስጥ ሌሊት የሚለጠፉ ወረቀቶችን ተከትሎ ውጥረት ነግሷል
ተመስገን ደሳለኝ 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት
የፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ የነበረው ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ በዛሬው ቀን በዋለው ችሎት 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት፡፡ ፍትህን ሲያሳትም የነበረውና ሁለተኛ ተከሳሽ የሆነው ማስተዋል ህትመትና ማስታወቂያ በ10 ሺህ ብር ቅጣት ተጥሎበታል፡፡ ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ጥቅም 3/2007 ዓ.ም የመንግስትን ስም ማጥፋት፣ ህዝብን ማነሳሳትና የህዝብን አመለካከት ማናወጽ በሚሉ ሶስት ክሶች ጥፋተኛ የተባለ ሲሆን አሁን የተፈረደበት በትኛው እንደሆነ ባይታወቅም በአንደኛው ክስ ነው ተብሏል፡፡ የጥፋነኝነት ክሱ በተነበበት ወቅት ግን ‹‹መንግስት ይገድላል፣ ያፍናል፣ ይጨቁናል ብሎ ጽፏል፡፡›› በሚል ጥፋተኝ ነው ተብሏል፡፡ አቃቢ ህግ የቅጣት ማክበጃ ያላቀረበ ሲሆን ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝም ሆነ ጠበቃው የቅጣት ማቅለያ አላቀረቡም፡፡ በሌላ በኩል የጋዜጠኛው ጠበቃ አምሃ መኮንን ይግባኝ … [Read more...] about ተመስገን ደሳለኝ 3 አመት ጽኑ እስራት ተፈረደበት
የአ.አ ከንቲባ ጽ/ቤት ጠባቂ ፖሊሶች ተታኮሱ
የአዲስ አበባ መስተዳደር ማዘጋጃ ቤት (ከንቲባ ጽ/ቤት) ውስጥ የሚሰሩ ፖሊሶች ዛሬ በግምት ከቀኑ 6 ሰዓት አካባቢ እርስ በእርሳቸው መታኮሳቸውን አስተዳደሩ ውስጥ የሚሰሩ ሰራተኞች ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ ፖሊሶቹ የተታኮሱት በከንቲባው ጽ/ቤት ውስጥ የሚሰሩ ፖሊሶች በነበራቸው ግምገማ በተፈጠረ አለመግባባት እንደሆነ ታውቋል፡፡ ፖሊሶቹ የተታኮሱት ከስብሰባው እንደወጡ እንደሆነም ምንጮቹ ገልጸዋል፡፡ በከንቲባ ጽ/ቤት ፖሊሶች በተታኮሱበት ወቅት የአትክልት ተራን ጨምሮ በአካባቢው የሚገኘው ማህበረሰብ በድንጋጤ ውስጥ እንደነበርና አብዛኛው ከተኩሱ በኋላ ወደ አስተዳደሩ ቢሮ በማቅናቱ በከንቲባው ጽ/ቤት አካባቢ በርከት ያለ ህዝብ እንደሚገኝ ምንጮቻችን ጠቅሰዋል፡፡ ፖሊሶቹ በተታኮሱበት ወቅት ገላጋዮች መሃላቸው በመግባታቸው በሰው ላይ የደረሰ ጉዳት እንደሌለና ይህም በግምገማው ወቅት … [Read more...] about የአ.አ ከንቲባ ጽ/ቤት ጠባቂ ፖሊሶች ተታኮሱ
የቴሌ “አገልግሎት” መስተጓጎል ከሳምንት በላይ አስቆጠረ
ኢትዮ ቴሌኮም ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ የሞባይል ማስፋፊያ መጠናቀቁ ቢገለጽም፣ አገልግሎቱ አሁንም በሞባይል አገልግሎት ላይ የሚታየውን ችግር ሊቀርፍ ባለመቻሉ፣ በተለይ ሰሞኑን ከአገልግሎት ጥራት ጋር በተያያዘ ደንበኞች ምሬታቸውን እየገለጹ ነው፡፡ ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ ችግሩ የተከሰተው በተወሰኑ ቦታዎች እንደነበረና በአሁኑ ወቅት ግን ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ይላል፡፡ በተለይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የከተማዋ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች፣ የሞባይል መቆራረጥና የጥሪ መስተጓጎል ከሳምንት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም ባለፉት አምስት ቀናት ግን ችግሩ ይበልጥ መባባሱን አመልክተዋል፡፡ ካለፈው ዓርብ ማምሻውን ጀምሮ በሞባይል ስልኮች ለመጠቀም ከፍተኛ ችግር እንዳጋጠማቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሞባይል ጥሪ … [Read more...] about የቴሌ “አገልግሎት” መስተጓጎል ከሳምንት በላይ አስቆጠረ










