* “አሸባሪዎችን” ለይቶ የመያዝ “ልዩ ችሎታና ብቃት” ያለው ፖሊስ ያልያዘው ተጠርጣሪ አለ ሃና ላላንጎ የተባለችውን ተማሪ በሚኒባስ ታክሲ አፍነው በመውሰድ፣ በቡድን በመድፈርና ሕይወቷ እንዲያልፍ አድርገዋል በሚል ተጠርጥረው በእስር ላይ የሚገኙትን አምስት ተጠርጣሪዎች የፍርድ ቤት ጉዳይ በዝግ ችሎት መታየት ጀመረ፡፡ ተጠርጣሪዎቹ ለሦስተኛ ጊዜ ኅዳር 22 ቀን 2007 ዓ.ም. በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፍርድ ቤት፣ ቂርቆስ ምድብ ችሎት የቀረቡ ሲሆን፣ ፖሊስ ቀደም ባለው ቀጠሮ እንደሚሠራቸው ያስመዘገበውን ቀሪ የምርመራ ሒደት፣ ለችሎቱ ያስረዳበትና ተጠርጣሪዎቹን ያቀረበበት ሰዓት፣ ከሌሎች ቀናት የተለየ ነበር፡፡ ሟች ሃና ላላንጎ በቡድን ተደፍራ ሕይወቷ ማለፉ በመገናኛ ብዙኃን ከተሰራጨበት ጊዜ አንስቶ እያነጋገረ ከመሆኑም በተጨማሪ፣ በየቀጠሮው ፍርድ ቤት የሚገኘው ታዳሚ ቁጥር … [Read more...] about የሃና ላላንጎ ጉዳይ በዝግ ችሎት ታየ
Right Column - Primary Sidebar
የተዘጋውን የአረብ ሀገራት የኮንትራት ሰራተኛ አቅርቦትን ለመክፈት የወጣው ረቂቅ!
* ስለ ሰራተኞች መብት ጥበቃ መነሳቱ አልተዘገበም * በተወያይ ኤጀንሲዎች በኩል ግን ረቂቁ ውዝግብ አስነስቷል * ከዚህ ቀደም ያለ በኮንትራት ለተበተኑትስ ዜጎችስ ምን ታስቧል? አዲሱን መረጃ ያገኘሁት ሃገር ቤት ከሚታተመው ከአድማስ ጋዜጣ ላይ ነው፣ እንዲህ ይላል "ወደ አረብ አገራት የሚሄዱ ሰራተኞች ላይ የሚደርሰውን ችግርና እንግልት ለማስቀረት በሚል ከአንድ ዓመት በላይ ተቋርጦ የቆየውን አሰራር ለማስጀመርና ለመቆጣጠር የተዘጋጀው ረቂቅ አዋጅ ውዝግብ አስነሳ፡፡" ... ወረድ ብለን ዝርዝር መረጃውን ስንቃኝ በዋናነት መታየት ያለበት አንኳሩ የሰራተኞች ይዞታና የመብት ጥበቃ ጉዳይ በዘገባው ላይ አልተካተተም። ይህም ይሁን ብለን ዝርዝሩን ስንቃኝ ከዚህ ቀደም በነጻ ያገኙትን ቪዛ በደላላ በየገጠር ከተሞች ሰብስበው እህቶቻችንን ከመላካቸው አስቀድሞ ፈቃድ ሲያወጡ ለመንግስት … [Read more...] about የተዘጋውን የአረብ ሀገራት የኮንትራት ሰራተኛ አቅርቦትን ለመክፈት የወጣው ረቂቅ!
ጸረ- ወያኔው ትግል ይፋፋም!
የወያኔን ጸረ-ዴሞከረሲያዊንት ለማስረገጥ ሐቁ ሞልቶ መፍስስ ከጀመረ ብዙ ዓመታትን አስቆጠረ። ወያኔ ለህግ የበላይነት ይገዛል ብሎ ማስብ ከእባብ እንቁላል እርግብ እንደመመኘት ይሆናል ብንል ማጋነን አይሆነብንም። ወያኔ ክፍጥረቱ ጀምሮ እሰክዛሬ ድረስ ከሐቅ ተጣልቶ፣ ሀሰተን አንግሶ፣ ጥላቻን ተላብሶ በማደናገርና በማወናበድ ፓሊሲ የተመራ በመሆኑ አሁንም እድሜውን ጨርሶ በማብቂያው አዝማሚያ ያላደገበትን፣ ያልለመደውን ፍትህና ዴሞከርሲያዊ ባህሪ እንዲያሳይ ልንጥብቅ ከቶ አይግባም። (ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ጸረ- ወያኔው ትግል ይፋፋም!
Moresh open letter to the United Nations Security Council
This letter is written to file a formal complaint regarding the report ‘SEMG S/2014/727’ dated 13 October 2014. I would like to bring to your attention specifically to the content and implications of the text stated on page 31, paragraph 78, which states “Ginbot Sebat is a banned opposition group formed in 2005 by Amhara political elites committed to regime change in Ethiopia through armed struggle.” We are utterly baffled by the motive behind this false information and data contained in the … [Read more...] about Moresh open letter to the United Nations Security Council
አባት አቶ ላላንጎ እና እናቷ ወ/ሮ ትርፌ ስለ ሃና ተናገሩ!
እህት ሃና በሰው አራዊቶች ለአምስት ተከታታይ ቀናት ተደፍራ ወድቃ ያገኟት አባት ልጃቸው ህክምና ታገኝ ዘንድ ከሆስፒታል ሆስፒታል ስለተንከራተቱበት፣ የህክምና እርዳታ ስለተነፈጉበት አሳዛኝ ሂደት ሀገር ቤት በሚተላለፈው ኤፍ ኤም ራዲዮ ተናግረዋል። አባት ሲናገሩ ለሃና ህክምና ማድረግ ያልቻሉት የመንግስት ህክምና ተቋማት ሳያንስ ፖሊስ ጉዳዩን እንዲመረምር በልመና ካሳኩ በኋላ ህክምና ማግኘት ባለመቻላቸው የሚረዳቸው አጥተው ተጎጅ ልጃቸውን ይዘው ወደ ቤታቸው ወስደው ስላሳደሩበት እንግልት ሰምተናል፣ ይህም ያማል፡፡ እንደ አባት አቶ ላላንጎ ገለጻ ልጃቸው እህት ሃና ከጋንዲ ጥቁር አንበሳ ከጥቁር አንበሳ ዘውዲቱ ግልጋሎት ተነፍገው ተንከራተዋል። ወደ መጨረሻም በዘውዲቱ ሆስፒታል አልጋ ተሰጥቷን መታከም መጀመሯንና በህክምና እያለች የምስክርነት ቃሏን በደል አድራሽ ያለቻቸውን ሶስቱ በፖሊስ … [Read more...] about አባት አቶ ላላንጎ እና እናቷ ወ/ሮ ትርፌ ስለ ሃና ተናገሩ!
የማህበረሰብ ውይይት በኢትዮጵያ ዘለቄታዊ ሰላምና ትብብር
በሰሜን አሜሪካና አውሮፓ የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ከቅርብና ከሩቅ ተጠራርተው ቅዳሜለት (ኅዳር 6/Nov. 15) በአርሊንግተን ቨርጂኒያ ስብሰባ አድርገው ነበር። ውይይታቸው በኢትዮጵያ ዘለቄታ ያለው ትብብር ለመገንባት የሚያስችሉ አዳዲስ ሃሳቦችና የጋር እሴቶችን በመመርመር ላይ ያተኮረ ነበር። በሰሜን አሜሪካ የሚገኘው የጋራ እንቅስቃሴ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የተባለ የሲቪክ ድርጅት ያሰናዳው ጉባዔ ከተለያዩ ብሄሮች፤ ጾታና የሃይማኖት አባላት፤ እራሳቸውን እንደግለሰብ ወክለው የተሳተፉበት ነበር። ቅዳሜለት በዋሽንግተን ዲሲ አቅራቢያ በምትገኘው አርሊንግተን ቨርጂኒያ የተሰባሰቡ ኢትዮጵያዊያን፤ በሀገራቸው ተቋማዊ አስተዳድር ባልተጠናከረበት መልኩ፤ ማህበረሰቦች ሊጫወቱት የሚገባቸው ሚና፣ እንዲሁም እርስ በርስ የመተባበር ሃሳቦች ላይ ያተኮረ ነው። የጋራ እንቅስቃሴ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ በዋሽንግተን … [Read more...] about የማህበረሰብ ውይይት በኢትዮጵያ ዘለቄታዊ ሰላምና ትብብር
“ለነሱማ…”
ለሕዝቦች አርነት — ላገርህ አንድነት፣ አርቀህ ማለምህ — አሕዛብን ማንቃትህ፣ “..ጠጣሩ እንዲላላ..” ምክር መለገስህ፣ “በረከት” አድርገህ “ርግማን” ማውረድህ..፣ አቤት! “ለነሱማ” እጅግ ማስፈራትህ! እነ-ኮሎኒያሊስት — ደግሞ እነ-እምፔሪያሊስት...፣ ያገርህ ደመኞች፟- ህሊና የለሾች፣ የሞራል፣ የባህል፣ የታሪክ አልቦዎች፣ አጠገብህ መቆም ከቶ ሲሳናቸው፣ እሚያረጉት ሲያጡ — ወኔ ሲከዳቸው፣ ሃቅን ስለሚሸሹ፟- መበለጥን ስለማይሹ፣ ምኑ ነው እሚደንቅህ? “ዕብድ” ነውስ ቢሉህ! ለኛ እንጂ ጥበብህ — ባለቅኔነትህ፣ የታሪክ፣ የባህል፣..መምህርነትህ፣ የፍትህ፣ ያንድነት.. ዓርማ ቤዛነትህ..፣ “ለነሱማ” አስፈሪ — ልክ-ልኩን ነጋር፣ ቆጥቋጭ የግር-እሳት — ቀሳፊ የጎን ውጋት፣ ሾተላይ ጸሐፊ — ታሪክ አሳላፊ...፤ ጌታቸው አበራ ኅዳር 2007 … [Read more...] about “ለነሱማ…”
ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች፣ አልማዝ በኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ቀረች !
የተረፈችው የእህት ብርቱካን ጉዳይ ... በሃገረ ሊባኖሰ ቤሩት ከ4ኛ ፎቅ ወድቃ የተረፈችው እህት ብርቱካን ጤንነት የተስተካከለና ከድካም ህመሟ ሙሉ በሙሉ እያገገመች መሆኑን መረጃዎች ማምሻውን ደርሰውኛል። የቆንስል ሃላፊዎች አልማዝን ሲያነጋግሯት በሊባኖስ ቆይታ ስራ መስራት እንጅ ወደ ሀገር ቤት መመለስ እንደማትፈልግ እንደገለጸችላቸው አምባሳደር ሐሊማ ሙሃመድ አጫውተውኛል። በቀጣይ ቀናትም ህክምና እየወሰደች ያለችበትን መካስድ ሆስፒታልን ለቃ እንደምትወጣ ፣ በቤሩት የቆንስል መጠለያ ሆና ህክምናና ጉዳይዋን እንደምትከታተል ተረድቻለሁ ! ተስፋ የቆረጡት ኢትዮጵያውያን አስተያየት ... በብርቱካን ጉዳይ ዙሪያ ያነጋገርኳቸው ብዙ ነዋሪዎች የቆንስል ተዋካዮች ላይ እምነት እንደሌላቸው ይገልጻሉ። እንደ አማራጭም የብርቱካንን ጉዳይ በጠበቃ አስይዘው ለመከራከር የሚቻልበትን ንገድ … [Read more...] about ብርቱካን በሊባኖስ ተረፈች፣ አልማዝ በኦማን የአካል ጉዳተኛ ሆና ቀረች !
የልጆቻችን ሀገር
አያቶቻችን የልጆቻችን መሬት ነች ብለው ደማቸውን አፍስሰው ሀገራችንን ከወራሪ ፋሽት ታደጉልን አባቶቻችን በውርስ እርስ በእርስ ሲጣሉ ሳይኖሩበት ሳያኖሩበት ይኸው አሉ ። ልጆች የሚሆነው ሳይገባቸው ውሉ የጠፋባቸውን አባቶቻቸው እያዩ ነው፤ ግራ መጋባታቸውን እየወረሱ ግራ እየተጋቡ ነው ፤ ወይ በሽሽት ላይ ናቸው፤ ነገር ግን እትብታቸው የተቀበረባትን ቀዬ ከማዶ ሆነው እያዪ የጨው አምድ ሆነው ቆመዋል፤ ብቻ ልቦቻቸው ያነባሉ። እንዲህ እያሉ:- የአያቶቻችን ቀዬ - የአባቶቻችን የጦር አውድማ፣ ለኛማ ህልም ብቻነች -ያልተጨበጠች ከተማ፤ ቆመንባት የምትፋጅ- ስንርቃት የምትናፍቅ፣ የሆነች -ነች የቅርብ ሩቅ፤ እንዳንተዋት ማረፊችን፣ እንዳይዛት ማን ፈቅዶልን?፣ አያስነካን - የማይጠግበው አባታችን፣ ብቻ እዛ ማዶ ተገትርን፣ እዚህም ከግለቱ ላይ ተጥደን ፣ ለልጆቻችን አስቀሩልን … [Read more...] about የልጆቻችን ሀገር
THE BRUSSELS ETHIOPIAN HISTORICAL MARCH!
The Woyyane (The TPLF) is a terrorist organisation that is holding Ethiopia at ransom. Since the these criminals came to power, nothing changed in their wild behaviour. They were terrorists yesterday, they are terrorists today and unless they are stopped now, they wouldn’t change their behaviour in the future. The worsening brutality of the ethno-apartheid Woyyane (i.e. ethnic based black on black apartheid) regime has left Ethiopians with no option but to come together and resist tyranny of the … [Read more...] about THE BRUSSELS ETHIOPIAN HISTORICAL MARCH!










