ጋዜጣዊ መግለጫ ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ-የኢትዮጵያ ጉዳይ በፍትሕ ለሚያምኑ ድርጅቶችና ሰዎች በሙሉ መልካም ምኞቱን እየገለጸ በቫቲካን ድጋፍ በመርዝ ጋዝ ጭምር በመጠቀም ኢትዮጵያ ላይ ስለ ተፈጸመወ የፋሺሽት የጦር ወንጀል የሰው እልቂትና እጅግ ከፍ ያለ ውድመት የካቲት 12-14 ቀኖች 2007 ዓ/ም ወይም በዚያን ሰሞን በየሐገሩና በየከተማው የመታሰቢያ ክብረ በዓል በማዘጋጀት እንዲዘክሩት ግብዣውን በትሕትና ያቀርባል። እንደሚታወቀው፤ ፋሺሽት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በወረረችበት በ1928-34 ዘመን አንድ ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን ከመጨፍጨፋቸው በላይ 2,000 ቤተ ክርስቲያኖችና 525,000 ቤቶች ወድመዋል። እንዲሁም በሚሊዮን የሚቆጠሩ እንስሳት አልቀዋል። በተለይ፤ በየካቲት 12-14 ቀኖች 1929 ዓ/ም ፋሺሽቶች አዲስ አበባ ከተማ 30000 ኢትዮጵያውያንን እንደ ጨፈጨፉ የታወቀ ነው። … [Read more...] about ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ – የኢትዮጵያ ጉዳይ
Right Column - Primary Sidebar
ANUAK MASSACRE OF 2003 WILL BE REMEMBERED BY MANY ETHIOPIAN ANUAK LIVING IN REFUGEE CAMPS
11-YEAR ANNIVERSARY OF ANUAK MASSACRE OF 2003 WILL BE REMEMBERED BY MANY ETHIOPIAN ANUAK LIVING IN REFUGEE CAMPS AFTER BEING FORCIBLY UPROOTED FROM THEIR INDIGENOUS LAND This year, members of the Ethiopian community in the Greater Houston, Texas, have sent a significant gift of encouragement to the Anuak who have been uprooted from their land and homes. December 13, 2014 PRESS RELEASE. FOR IMMEDIATE RELEASE (Vancouver, BC, Canada) December 13, 2014 will mark the 11-year anniversary of the … [Read more...] about ANUAK MASSACRE OF 2003 WILL BE REMEMBERED BY MANY ETHIOPIAN ANUAK LIVING IN REFUGEE CAMPS
በአባ ፋኑኤል ፓትሪያርክ?
የቀድሞው ቄስ ታደሰ ሲሳይ የልጆቻቸውን እናት ከፈቱበት (ሰኔ ፲፱፻፺፰ ዓ.ም. ወይም June 2006) ጀምሮ ለበርካታ ዓመታት የቤተ ክርስቲያኗ ችግር ለተመልካች ሁሉ አሰልቺ፤ እምነታችንንና ባሕላችንን አስተቺና አስነቃፊ ሆኖ ያለ አንዳች መፍትሄ ሲጓተት መቆየቱ ለሁሉም የታወቀ ነው። ችግሩ ቤተ ክርስቲያኒቱን በዓለም ዓቀፍ ደረጃ በሀፍረት ላይ በመጣሉ፤ በዋሽንግተን ዲሲ: በቨርጅንያና በሜሪላንድ የሚኖሩ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ክርስቲያኖች ተሰባስበው የራሳቸውን የቀድሞው ቄስ ታደሰን ወላጅ እናት በመጨመር በየሳምንቱ የሚታየው ውዝግብ በሽምግልና እንዲያልቅ ብዙ ጥረት አደረጉ። ይሁን እንጅ በቀድሞው ቄስ ታደሰ ሲሳይ በኩል ሽምግልናው ተቀባይነትን ሳያገኝ ቀረ። ይልቁንም “ከሁሉም ገለልተኛ አድርጌ በስሜ ባስመዘገብኩት ንብረት የፈለግሁትን ባደርግ ጠያቂ ሊኖርብኝ አይገባም በማለት … [Read more...] about በአባ ፋኑኤል ፓትሪያርክ?
ዓይን አጥፊው የዓይን “ማከሚያ ቤት”
* “ብዙ ብር ከፍለን የዓይን ብርሃናችንን አጥተን ተመልሰናል” - ታካሚዎች * ከመነሻው የማዕከሉ አደረጃጀት አዋጁን የሚቃረን ነው - የአዲስ አበባ ጤና ቢሮ * ማዕከሉ በየዓመቱ የሚታደስ የህክምና አገልግሎት ፈቃድ አልተሰጠውም ከአንድ ዓመት ተኩል በፊት የተሻለ የአይን ህክምና ለመስጠት፣ ለኢትዮጵያውያን ሀኪሞች የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲያደርግና በዘርፉ ምርምርና ጥናት እንዲያካሂድ ታስቦ በዘውዲቱ ሆስፒታል ግቢ ውስጥ የተገነባው የህንድ የአይን ህክምና ማዕከል በታካሚዎች ላይ ጉዳት እያደረሰ መሆኑ ተገለፀ፡፡ ጉዳት የደረሰባቸው ታካሚዎች እንደተናገሩት በማዕከሉ በተሰጣቸው ህክምና ሳቢያ የዓይን ብርሃናቸውን አጥተዋል፡፡ በማዕከሉ የሚሰሩ ኢትዮጵያውያን ባለሙያዎች ለአዲስ አድማስ እንደገለፁት የተሟላ የህክምና ቁሳቁስ፣ በዘርፉ በቂ እውቀት ያላቸው ባለሙያዎችና ደረጃውን የጠበቀ … [Read more...] about ዓይን አጥፊው የዓይን “ማከሚያ ቤት”
ልማታዊ ሙስና?
ባለፈው ዓርብ በተከፈተው የመሬት ሊዝ ጨረታ በአንድ ካሬ ሜትር 305 ሺሕ ብር ቀረበ፡፡ ይህ ዋጋ በከተማው ታሪክ እጅግ ከፍተኛ መሆኑ የሊዝ ጨረታን የወቅቱ አነጋጋሪ ክስተት አድርጓል፡፡ በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ መርካቶ በርበሬ አካባቢ 449 ካሬ ሜትር ቦታ ለጨረታ ቀርቧል፡፡ በካሬ ሜትር የቀረበው ገንዘብ ሲሰላ ይህ አነስተኛ ቦታ 136.9 ሚሊዮን ብር የሚያወጣ ሆኗል፡፡ 20 በመቶ ብቻ የተከፈለበት ይህ መሬት ከነወለዱ እስከ 300 ሚሊዮን ብር በ30 ዓመት ሊደርስ እንደሚችል ባለሙያዎቹ ገልጸዋል፡፡ ይህ ክስተት ለአዲስ አበባ ሊዝ ሥሪት ባለሙያዎች እንዲሁም በጨረታው ለታደሙ ባለሀብቶች የቀረበው ዋጋ ብዥታን ፈጥሯል፡፡ በጨረታው ላይ ሁለተኛ ሆኖ የቀረበው ዋጋም ከዚህ ቀደም ቀርቦ የማያውቅ ሲሆን፣ የቀረበውም በካሬ ሜትር 288 ሺሕ ከ90 ሳንቲም ነው፡፡ "በአዲስ አበባ የሊዝ ዋጋ … [Read more...] about ልማታዊ ሙስና?
ቴዲ አፍሮን ቦሌ ላይ ለምን አገቱት?
ወደ አውሮፓ የሚያስገባውን ቪዛ እና ትኬት ይዞ ከወዳጆቹ ጋር ጉዞውን ለመጀመር ወደ ቦሌ አለም-ዓቀፍ አውሮፕላን ጣቢያ አቀና። እዚያው እንደደረሰ የተለመደው የፓስፖርትና ትኬት ቁጥጥር ተደረገ። ሁሉም የተሟላ ነበር። ቴዲ ሸኚዎቹን ተሰናብቶ ወደ ውስጥ ጋባ። እለተ ሐሙስ፣ ህዳር 28 ቀን 2007 ዓ.ም.። የአውሮፓው ኮንሰርት በፊንላንድ፣ ሄልሲንኪ ቅዳሜ፤ ህዳር 28 ቀን ይጀምራል። ፊንላንድና አካባቢው ያሉ የቴዲ አድናቂዎች ትኬት ቆርጠው አርቲስቱን በጉጉት እየተጠባበቁት ነው። የቴዲ አፍሮ ማናጀርም አቡጊዳ ባንድን ይዞ ሄልሲንኪ ላይ ለቅዳሜው ስራ በልምምድ ላይ ይገኛል። ቴዲን ቦሌ አውሮፕላን ማረፊያ ተሰናብተው የተመለሱ ወዳጆቹ አውሮፓ ደውለው አርቲስቱን ሄልሲንኪ ላይ እንዲቀበሉት ተናግረው ነበር። ነገሩ እነሱ እንዳሰቡት ግን አልነበረም። ዘግየት ብሎ ሌላ ነገር መጣ። ሰዎቹ ቦሌ ላይ … [Read more...] about ቴዲ አፍሮን ቦሌ ላይ ለምን አገቱት?
Ethiopia: Making Reconciliation Work
The reconciliation dialogue needs to progress in parallel on two fronts: (1) among the several opposition groups; and, (2) between the government and oppositions. Allow me to be pragmatic by putting myself in the shoes of both the government and the opposition to deal with the reconciliation dialogue on the latter front. Since there is so much mistrust between the government and oppositions, tossing the word “reconciliation” around will not get us anywhere. It means different things for … [Read more...] about Ethiopia: Making Reconciliation Work
ዘመነ መሳፍንትና የፖለቲካ መሪዎቻችን የወረሱት ቅርስ
በዘመነ መሳፍንት ወቅት፤ ለስሙ በዙፋኑ ላይ የዘር ግንድ ያለውን ሰው አስቀምጠው፤ ራሳቸውን እንደራሴ በመሾም፤ ጉልበተኞች ያደረጉት ሁሉ ግልጽ ነው። የውጭ ሀገር መንግሥታት ደግሞ በወኪሎቻቸው አማካኝነት ፀረ-ኢትዮጵያ ሚና ተጫወቱ። በደንብ በዝርዝር የሚያስረዳ መዝገብ ግን አላገኘሁም። ከዚህም ከዚያም ለቃቅሜ የተገነዘብኩትን ይዣለሁ። የእስክንድርያውን የኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን በመጠቀም፤ ግብፅና ቱርክ በአንድ በኩል፣ በፖርቹጋሎች የተጀመረውን ግንኙነት በመጠቀም፤ የካቶሊክ ቤተክርስትያን በሌላ በኩል፣ በእንግሊዝና በፈረንሳይ በኩል ደግሞ የፕሮቴስታንትና የአድቬንቲስት ተቋሞች በማዕከላዊው የሀገራችን ክፍል ያላደረጉት ተንኮል የለም። የሁሉም ጥርቅም ጥረት፤ ክርስትናን ወይንም እስልምናን ተከትለው፤ የፈጣሪያቸውን ሥራ ለማስተማር ሳይሆን፤ ጠንካራ ኢትዮጵያ እንዳትኖር ለማድረግ ነበር። አባይን … [Read more...] about ዘመነ መሳፍንትና የፖለቲካ መሪዎቻችን የወረሱት ቅርስ
ለለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን በሙሉ
መልዕክቱን አባዝቶ ለሌሎች በማዳረስ ለ24 ሰዓቱ ሰልፍ ቅስቀሳ የበኩላችሁን እገዛ እንድታደርጉ ጥሪ እናስተላልፋለን! ያለመስዋዕትነት ድል የለም! … [Read more...] about ለለውጥ ፈላጊ ኢትዮጵያውያን በሙሉ
በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ
በእነ ሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ የሽብር ክስ ተመስርቶባቸው ጉዳያቸው እየታየ ያሉት ጦማርያን እና ወዳጅ ጋዜጠኞች ላይ የተመሰረተው ክስ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው የክስ ዝርዝር ከትላንት በስቲያ በልደታ ከፍተኛው ፍርድ ቤት ተሰምቷል፡፡ ዛሬ ህዳር 24/2007 ጠዋት በዋለው ችሎት፣ በጦማርያኑ እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ የቀረበው የክስ ዝርዝር በንባብ የተሰማ ሲሆን በክስ ወረቀቱ ላይ ከተመለከቱት ነጥቦች መካከል ግልጽ ያልሆኑ ነጥቦችን አካትቶ እንዲሰጥ ለአቃቤ ህግ ትዕዛዝ ተሰጥቶታል፡፡ ስለሆነም ሙሉ የክስ ወረቀቱ አርብ ለጠበቆቹ እንደሚደርስ ይጠበቃል፡፡ በጠበቆቹ በኩል ክሱ ቀደም ብሎ ፍርድ ቤቱ በሰጠው ትዕዛዝ መሰረት መሻሻሉን ለማረጋገጥ ያለፈው የፍርድ ቤቱ ብይን ግልባጭ እስካሁን እንዳልደረሳቸው በመግለጽ፣ በአጭር ጊዜ ውስጥ እንዲደርሳቸው ጠይቀዋል፡፡ በዚህም የተነሳ የብይኑ … [Read more...] about በጦማርያን እና ጋዜጠኞች ላይ ተሻሽሎ ቀርቧል የተባለው ክስ ተሰማ










