• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የቴሌ “አገልግሎት” መስተጓጎል ከሳምንት በላይ አስቆጠረ

October 23, 2014 08:15 pm by Editor Leave a Comment

ኢትዮ ቴሌኮም ከ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ውስጥ የአዲስ አበባ ከተማ የሞባይል ማስፋፊያ መጠናቀቁ ቢገለጽም፣ አገልግሎቱ አሁንም በሞባይል አገልግሎት ላይ የሚታየውን ችግር ሊቀርፍ ባለመቻሉ፣ በተለይ ሰሞኑን ከአገልግሎት ጥራት ጋር በተያያዘ ደንበኞች ምሬታቸውን እየገለጹ ነው፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም በበኩሉ ችግሩ የተከሰተው በተወሰኑ ቦታዎች እንደነበረና በአሁኑ ወቅት ግን ሙሉ ለሙሉ ተቀርፏል ይላል፡፡

በተለይ ሪፖርተር ያነጋገራቸው የከተማዋ የሞባይል ስልክ ተጠቃሚዎች፣ የሞባይል መቆራረጥና የጥሪ መስተጓጎል ከሳምንት በላይ ያስቆጠረ ቢሆንም ባለፉት አምስት ቀናት ግን ችግሩ ይበልጥ መባባሱን አመልክተዋል፡፡

ካለፈው ዓርብ ማምሻውን ጀምሮ በሞባይል ስልኮች ለመጠቀም ከፍተኛ ችግር እንዳጋጠማቸው ጠቅሰዋል፡፡ የሞባይል ጥሪ ቅዳሜና እሑድም ተባብሶ መቀጠሉን ደንበኞች በምሬት ገልጸዋል፡፡ ከጥሪ አገልግሎትም በተጨማሪ በአጭር ጽሑፍ መልዕክትና የሒሳብ መጠየቂያና የቅድመ ክፍያ ካርዶችን ለመሙላት እንኳን አዳጋች ሆኖ ነበር፡፡

የኢትዮ ቴሌኮም ኮርፖሬት ኮሙዩኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ አብዱራሂም አህመድ  ሰሞኑን የባሰበትን የሞባይል አገልግሎት መስተጓጎልና መቆራረጥ አምነው፣ ‹‹በአሁኑ ጊዜ ችግሩ ሙሉ በሙሉ ተቀርፏል፤›› በማለት ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

በተለይ በአራዳ ክፍለ ከተማ አካባቢ የኃይል መቆራረጥ በማጋጠሙ ኦሲኤስ (OCS) የተባለው ኃይል አስተላላፊ ሥራ በማቋረጡ ችግሩ ተፈጥሯል ብለዋል፡፡ እንደ እሳቸው ገለጻ ችግሩ የተስተዋለው የቅድመ ክፍያ አገልግሎት የሚሰጡ (Prepaid) የሞባይል መስመሮች ላይ ነበር፡፡

አቶ አብዱራሂም ይህንን ቢሉም፣ ጥቅምት 11 ቀን 2007 ዓ.ም. ከማለዳ ጀምሮ የጥሪ ችግሩ በሞባይል ስልኮች ላይና በመደበኛ የስልክ አገልግሎቶች ላይ ተስተውሏል፡፡ በተመሳሳይም ችግሩ ከአዲስ አበባ በተጨማሪ በዱከም፣ በቢሾፍቱና በአጎራባች ከተሞች ጭምር መከሰቱን ደንበኞች ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

‹‹ኢትዮ ቴሌኮም የሞባይል የማስፋፊያ ሥራዎችን አጠናቅቄያለሁ፤ ይስተዋሉ የነበሩ ችግሮችን ቀርፌዋለሁ ባለ በጥቂት ደቂቃዎች ውስጥ ችግሩ በድጋሚ ተከስቷል፡፡ አሁን ደግሞ እንደሚታየው ላለፉት አምስት ቀናት ያህል ጭራሽ ኔትወርኩ ሞቷል፡፡ ወይ አንድ ፊቱኑ ሞባይል የሚባለውን ነገር ቢተውት ይሻላል፤›› ሲል ከቦሌ ወደ መገናኛ በሚጓዝ ታክሲ ላይ ሪፖርተር ያነጋገርነው ተሳፋሪ ገልጿል፡፡

ባለፈው ዓመት መጨረሻ ኢትዮ ቴሌኮም በአዲስ አበባ ተከናውኗል ያለውን የሞባይል ማስፋፊያ ሥራ ሙሉ ለሙሉ በቻይናው ሁዋዌ ኩባንያ አማካይነት ማከናወኑንና የነበሩት የአገልግሎት ችግሮች መቀረፋቸውን ኢትዮ ቴሌኮም መግለጹ ይታወሳል፡፡ ከመደበኛው የሞባይል ማስፋፊያ በተጨማሪ ‹‹3G›› እና ‹‹4G›› የተባሉት አገልግሎቶች መጠናቀቃቸውንና ለተጠቃሚዎች ዝግጁ መሆናቸውም ጨምሮ አስታውቆ ነበር፡፡ የ‹‹3G›› አገልግሎት የተጀመረ ቢሆንም እስካሁን የ‹‹4G›› አገልግሎት ግን አልተጀመረም፡፡

ኢትዮ ቴሌኮም ከቻይናዎቹ ሁዋዌ እና ዜድቲኢ ኩባንያዎች የ1.6 ቢሊዮን ዶላር የማስፋፊያ ፕሮጀክት ከአንድ ዓመት በፊት ተፈራርሟል፡፡ እስካሁን ግን በስምምነቱ መሠረት የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ቢጀመርም፣ መላ አገሪቱን የሚያዳርሰው ግን አለመጀመሩ ይታወቃል፡፡

ሁለቱ የቻይና ኩባንያዎች እያንዳንቸው የ800 ሚሊዮን ዶላር ሥራ የተረከቡ ሲሆን፣ ዜድቲኢ የአዲስ አበባው ፕሮጀክት ሙሉ በመሉ ለተቀናቃኙ ዜድቲኢ መሰጠቱ እንዳላስደሰተው እየተነገረ ነው፡፡ ረዥም ጊዜ የወሰደ ተጨማሪ ውይይት ከመንግሥት ጋር እያደረገ እንደነበር በተደጋጋሚ መዘገቡ ይታወሳል፡፡ በዜድቲኢ ሥራ አለመጀመርና በአዲስ አበባ ተጠናቋል በተባለው ፕሮጀክት በመንግሥትና በኢትዮ ቴሌኮም ላይ የሕዝብ ጥያቄ እየተነሳ ነው፡፡

ባለፈው ዓመት ፓርላማው ጭምር በኢትዮ ቴሌኮም ላይ ተደጋጋሚ ጥያቄዎች ሲነሱበት መቆየቱም ይታወሳል፡፡ በተለይም ከመደበኛ ስብሰባዎች በተጨማሪ የመሠረተ ልማት፣ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ የድርጅቱን ኃላፊዎች በተደጋጋሚ በመጥራት ማብራሪያ መጠየቁና ማሳሰቢያም መስጠቱ ይታወሳል፡፡

አቶ አብዱራሂም አህመድ፣ በተደጋጋሚ ወደ ሕዝብ በመውጣት ድርጅቱን በሚመለከት በሕዝብ የሚነሱ ጥያቄዎችን ምላሽ ለመስጠት በመገናኛ ብዙኃን ብቅ ማለታቸው የተለመደ ቢሆንም፣ ነገር ግን ዋና ሥራ አስፈጻሚው አቶ አንዱአለም አድማሴንና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ቀርበው ያለውን ሁኔታ አለማስረዳታቸው የድርጅቱን አጠቃላይ አሠራር ግልጽ እንዳይሆን ተፅዕኖ ማድረጉንና በድርጅቱ አቅም ላይም ብዥታን እየፈጠረ መሆኑን የሚገልጹ አስተያየት ሰጪዎች አሉ፡፡

ሊጠናቀቅ አንድ ዓመት ብቻ በቀረው የዕድገትና ትራንስፎርሜሽን መጨረሻ በአገር አቀፍ ደረጃ የሞባይል ተጠቃሚዎችን ቁጥር 59 ሚሊዮን ለማድረስ የታቀደ ሲሆን፣ በአሁኑ ወቅት የተጠቃሚዎች ቁጥር 29 ሚሊዮን መድረሱን መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ (ምንጭ: ሪፖርተር)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule