The following are broad brush strokes of my personal outlooks about the epoch I have lived and strived in. I leave the descriptive details of events and facts to professional historians. The 1974 revolution that replaced the Imperial Regime gave birth to an era of terror and lawlessness. Since then Ethiopian history has been subject to many interpretations according to the ideological, political and personal persuasion of the narrator. Although a lot of well researched books and papers have been … [Read more...] about PERSPECTIVES OF ETHIOPIA’S FUTURE
Right Column - Primary Sidebar
ኢህአዴግ የሰራው ቤት! ግድግዳው ሰንበሌጥ!
እንደመግቢያ ፌደራሊዝም የመንግስት ኣወቃቀር ሰፊ የቆዳ ስፋትና ብዙ ህዝብ ላላቸው ኣገሮች፣ በዛ ያሉ የተለያየ ቋንቋና ባህል ያላቸው ቡድኖች ላላቸው ሃገሮች፣ ተመራጭ ኣስተዳደራዊ መዋቅር እንደሆነ እጅግ ብዙ ሰው በዓለም ላይ ይስማማል። ፌደራሊዝም የተመረጠበት ዋናው ምክንያት ስልጣን እና ፍትህ ከህዝቡ እንዳይርቅ ነው። እንዳይርቅ ስንል ከመልክዓ ምድርም ከወረፋም ኣንጻር ነው። ትላልቅ የሆኑ ኣገሮች ስልጣንን ቢያማክሉ ዜጎች ለኣንዳንድ ጉዳዮች ስልጣን ወደተጠራቀመበት ለመሄድ ስለሚርቃቸው ብዙ ከሆኑ ደግሞ ሰልፉ ስለሚበዛ ወረፋው መጉላላትን ስለሚፈጥር ነው። ዜጎች ስልጣን ወርዶ ከፍተኛ የሆኑ ጉዳዮቻቸውን ሳይቀር በክልሎቻቸው እንዲታይላቸው መደረጉ ጠቀሜታ ያለው ሲሆን ፍትህንና ኣገልግሎትን ለማደል በጣም ይረዳል። ስልጣን ተማክሎ የመካከለኛና ዝቅተኛ ደረጃ ባለስልጣናት እንደ ቧንቧ … [Read more...] about ኢህአዴግ የሰራው ቤት! ግድግዳው ሰንበሌጥ!
የአይሲል (ISIL) እንቅስቃሴ ምንነትና አንደምታው (ከአንድ ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ዕይታ)
የአይሲል (Islamic State of Iraq and the Levant - ISIL) እንቅስቃሴ ከሰማይ ዱብ ያለ አዲስ ክስተት አይደለም። አይሲል ( አንዳንዶቹ ISIS ይሉታል - Islamic State of Iraq and Syria ) በመካከለኛው ምሥራቅ ያለው የፖለቲካ ውጥንቅጥ ሀቅ ውጤት ነው። ለአነሳሱ፣ ለዕድገቱና ለሂደቱ ብዙ ነባሪ ምክንያቶች አሉት። በርግጥ የአይሲልን እንቅስቃሴ ከሀይማኖትና ከዘይት ሀብት ለይቶ ማየት አይቻልም። በፍልጥዔማውያንና በእስራዔላውያን መካከል ያለው ማብቂያ የለሽ ያልተቋረጠ ጦርነት አንዱ ምክንያቱ ነው። በኋላ ቀር የአረብ ነገሥታትና በሥራቸው የሚሰቃየው ሕዝብ የኑሮና የሀብት ሥምሪት መራራቅ ሌላው ምክንያቱ ነው። በእስልምና አጥባቂዎችና ለዘብተኛ ተከታዮች መካከል ያለው የግንዛቤ ልዩነት ሌላው ምክንያቱ ነው። አሜሪካኖች የራሳቸውን ጥቅም ለማስጠበቅ … [Read more...] about የአይሲል (ISIL) እንቅስቃሴ ምንነትና አንደምታው (ከአንድ ኢትዮጵያዊ ግለሰብ ዕይታ)
ቅኔና አዘማሪ
መግቢያ ለአዘማሪ ሙያ ተስማሚ የግብር መግለጫ መሆን ያለበት የቱ ነው? አዘማሪ ወይስ አርቲስት? በሚል በአቶ ዓለም ነጻነት ሬድዮ የቀረበው ውይይት ለዚህች ጦማር መነሻ ሆኖኛል። ከቀደሙ አባቶች እንደሰማሁት አዘማሪ ብቻውን የቆመ አይደለም። ከብዙ ነገሮች ጋራ ከቅኔያችን፣ ከዜማችንና ከስሜታችን ጋራ የተያያዘ ነው። አዘማሪ የሚለውን ቃል ከነዚህ ነጥሎ ለማቅረብ መሞከር ያዘማሪን ክብርና ቦታ ዝቅ ያደርገዋል የሚል ስጋት አለኝ። ስለዚህ አዘማሪ ወደሚለው ቃል ዘው ብለን ከመግባታችን በፊት የአዘማሪን ተልእኮ መዳሰስ ሊኖርብን ነው። አዘማሪ የሚለው ቃል የግብሩ (የተልእኮው) መግለጫ ነው። ተልእኮውም ራሱ አዘማሪ ተቀኝቶም ሆነ ገጥሞ ወይም ሌላ የተቀኘውን በዝማሬው ቅላጼ ከጉሮሮውና ከመሳሪያ ጋራ አስማምቶ፣ ቀምሞና አስወድዶ አስውቦ ለህዝብ ማቅረብ ነው። ህዝቡንም ከባህሉ ከታሪኩ … [Read more...] about ቅኔና አዘማሪ
ጄኔራል ታደሰ ብሩና ኮሎኔል ሀይሉ ረጋሳ
ይህንን ፎቶግራፍ ሰሞኑን በኢንተርኔት ላይ ሲንሸራሸር ነው ያገኘሁት፡፡ ፎቶውን ለመጀመሪያ ጊዜ ያወጣው በ1967 በመጋቢት ወር አጋማሽ የታተመ አንድ የአዲስ ዘመን ጋዜጣ ቅጂ ነው፡፡ ያ ጋዜጣ በደርግ ዘመን በድብቅ በከተማችን ይዘዋወር እንደነበረ ትዝ ይለኛል፡፡ በደርግ ውድቀት ማግስት ደግሞ የገለምሶ ከተማ ቀደምት ፎቶ ቤት የሆነው “ፎቶ አብደላ” የጋዜጣውን ኮፒና ይህንን ፎቶግራፍ ለየብቻቸው በማባዛት በሰፊው ሲያሰራጭ ቆይቷል (ፎቶ ቤቱ አንዱን ምስል በሶስት ብር ነው የሚሸጠው)፡፡ ***** በፎቶግራፉ ላይ የሚታዩት የሜጫና ቱለማ ማህበር አንጋፋ አባላት የነበሩት ብርጋዴር ጄኔራል ታደሰ ብሩ እና ኮሎኔል ሀይሉ ረጋሳ ናቸው፡፡ አዲስ ዘመን ጋዜጣ የሁለቱን ሰዎች ፎቶግራፍ ያተመው “ታደሰ ብሩና ግብረ አበሮቹ ተያዙ” የሚል ርዕስ ከሰጠው የዜና ዘገባ ጋር ይመስለኛል (ሙሉ ርዕሱን … [Read more...] about ጄኔራል ታደሰ ብሩና ኮሎኔል ሀይሉ ረጋሳ
ለሁላችንም የሚበጅ የተባረከ የእርቅ አስተሳሰብ
እንግዲህ ያረጀ የአመፅ ታሪክ ከመድገም፤ ከውጭ አገር መፍትሔ ከመኮረጅና፤ እልከኛና አንገተ ደንዳና ሆነን ለአዲሱ ጤናማ ኢትዮጵያዊነት አስተሳሰብ የማንመች ከመሆን ይጠብቀን። በአይነቱ ኢትዮጵያዊ የሆነውንና የኛው በኛው ለኛው ሆኖ የሚያኮራንን አዲስ የእርቅና የመግባባት ስሌትን መፍጠር እንችላለን የሚል አስተሳሰብ ይኑረን። እንቆቅልሻችንን እንፍታና የአገር ልጅነት ግዴታችንን በታማኝነት እንወጣ። በተቃራኒ የፖለቲካ አስተሳሰብ የተከፋፈልን ህዝብ ብንሆንም፦ ጥላቻና ንቀትን አስወግደን፤ ሁለቱም ጎራ (መንግስትና ተቃዋሚ) በጡንቻ መጠቀምን እንደ ኋላቀርነት ለመቁጠር የሚያስችል ብስለትና ድፍረት ይታይብን። በብዙ የተለያየ ባህልና ቋንቋ የበለፀግን ህዝብ ነን። የምንከባበርበትና በእኩልነት የምንተያይባት አዲሲቷን ኢትዮጵያ በልዩነታችን እንደ አንድ ቤተሰብ በመሆን ለመገንባት እንድንችል … [Read more...] about ለሁላችንም የሚበጅ የተባረከ የእርቅ አስተሳሰብ
ናፍቆት (በኑሬ)
ስጋዬ ሲበላኝ በጥርሴ ነከስኩት፤ ቆዳዬ ሲበላኝ በጥፍሬ ፎከትኩት፤ እፎይ አስታገስኩት፤ ፀጥ ረጭ አረ'ኩት። የውስጥ አጥንቴ ግን ሲበላኝ ነዝንዞ፣ ሲነክሰኝ ጠዝጥዞ፣ ምንም አላረ'ኩት፤ ምንም አላከኩት፤ ላልችል ችየ ቻልኩት። አልፎክተው ነገር ቆዳዬን መንቅሬ፣ አላኝከው ነገር ስጋዬን ሰርስሬ፣ ይሔው እስከዛሬ፣ አጥንቴ እየበላኝ፣ አለሁልሽ ፍቅሬ። ኑረዲን ዒሳ (ዒሻራ) 14/02/1995 ዓ.ም … [Read more...] about ናፍቆት (በኑሬ)
የስደት እፍታ – ፋሲል አየር ወለድ
ጥርስ ያልነቀለበት እትብቱ ዘመዱ ያልተቀበረበት ባዕድ መሬት ባዕድ ዓይኑ ውሃ ኹኖ ቦታው ጭጋግ ለብሶ ባሳብ እየዋኘ ሄደ ተመልሶ አገሩ ናፈቀው አሁን ይህን ጊዜ ዓደይ አበባ ነው ደማቅ ሰማያዊ ወሩ መስከረም ነው አጭር ነበር ጉዞው የሄደው ባሳቡ ወዲያው ተመለሰ ተመለሰ ዓይኑ እምባ አቀረረ። (ግጥም ገብረክርስቶስ ደስታ) ስደት ከወጣሁ ሦስት ወራት አልፎኛል። በቀጥታ የገባሁት ወንድሜ ቤት ነበር። ሚስትና ሁለት ህጻናት ልጆች አሉት። ሆኖም የራሴ የሆነ አንድ መኝታ ክፍል አላጣሁም። ተዋበ በፊት የማውቀውን አይነት ሆኖ አላገኘሁትም። ሳቁ ደርቋል፣ አጫጭር ነገሮች ተናጋሪ ሆኗል። ነገሮች የሰለቹት አይነት ነው። ሊያውራ የጀመረውን እንኳን አይጨርሰውም። በእንጥልጥል እያለ ወደሌላ ይሸጋገራል። የሌላን ሰው ንግግር የሚሰማው ከፊሉን ነው። የገባው ስለሚመስለው አይፈልገውም፤ … [Read more...] about የስደት እፍታ – ፋሲል አየር ወለድ
ከነጻነት ታጋዮች ጋር በቂሊንጦ
ባለፈው ሳምንት በማህበራዊ ሚዲያው “ጥቁር ሳምንት” (black week) በሚል ለአምስት ቀናት ዘመቻ (campaign) መካሄዱ ይታወሳል፡፡ በዚያ የጥቁር ሳምንት ዘመቻ ወቅት በመጨረሻው ቀን አስተባባሪዎቹ አዲስ አመትን በማስመልከት “አዲስ አመት በዓልን ከነጻነት ታጋዮች ጋር” በሚል የታሰሩ የነጻነት ታጋዮች እንዲጠየቁ ጥሪ መተላለፉ አይዘነጋም፡፡ በመሆኑም የሰማያዊ ፓርቲ ወጣቶችና የነገረ ኢትዮጵያ ዝግጅት ክፍል ጳጉሜ 5 ቀን 2006 ዓ.ም በቂሊንጦ የሚገኙ የዞን 9 የጡመራ ቡድን አባላትንና የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላትን በመጠየቅ የዘመቻውን አካል አከናውነዋል፡፡ ቀጥሎም የጥቂት እስረኞችን መልዕክት በአጭር በአጭሩ አቅርበናል፡፡ ጦማሪ ናትናኤል ፈለቀ “ሀገሬ ላይ እርግጠኛ የሆንሁበት ጉዳይ ቢኖር እኔን እንደ ዜጋ የሚጠብቀኝ መንግስት የሌለኝ መሆኑን ነው፡፡ … [Read more...] about ከነጻነት ታጋዮች ጋር በቂሊንጦ
… ለልማታዊ ሆድ
እንዳገኘ በልቶ እንዲህ ተነርቶ እንዲህ ሆዱ ሰፍቶ ቁርጡ ቀን ሲመጣ፥ ወያኔ ሲወገድ ገና መዋጮ አለ፥ ለልማታዊ ሆድ። … [Read more...] about … ለልማታዊ ሆድ










