• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ዘመነ መሳፍንትና የፖለቲካ መሪዎቻችን የወረሱት ቅርስ

December 7, 2014 02:31 am by Editor Leave a Comment

በዘመነ መሳፍንት ወቅት፤ ለስሙ በዙፋኑ ላይ የዘር ግንድ ያለውን ሰው አስቀምጠው፤ ራሳቸውን እንደራሴ በመሾም፤ ጉልበተኞች ያደረጉት ሁሉ ግልጽ ነው። የውጭ ሀገር መንግሥታት ደግሞ በወኪሎቻቸው አማካኝነት ፀረ-ኢትዮጵያ ሚና ተጫወቱ። በደንብ በዝርዝር የሚያስረዳ መዝገብ ግን አላገኘሁም። ከዚህም ከዚያም ለቃቅሜ የተገነዘብኩትን ይዣለሁ። የእስክንድርያውን የኦርቶዶክስ ቤተክርስትያን በመጠቀም፤ ግብፅና ቱርክ በአንድ በኩል፣ በፖርቹጋሎች የተጀመረውን ግንኙነት በመጠቀም፤ የካቶሊክ ቤተክርስትያን በሌላ በኩል፣ በእንግሊዝና በፈረንሳይ በኩል ደግሞ የፕሮቴስታንትና የአድቬንቲስት ተቋሞች በማዕከላዊው የሀገራችን ክፍል ያላደረጉት ተንኮል የለም። የሁሉም ጥርቅም ጥረት፤ ክርስትናን ወይንም እስልምናን ተከትለው፤ የፈጣሪያቸውን ሥራ ለማስተማር ሳይሆን፤ ጠንካራ ኢትዮጵያ እንዳትኖር ለማድረግ ነበር። አባይን እንዳትገድብ፣ ለቅኝ ግዛት ተቀናቃኝ እንዳትሆን፣ የጥቁር መንግሥት ሆና ለባሪያ ንግዳቸው እምቢተኝነት መመኪይ እንዳትሆን ነበር። ማዕከላዊ ጥንካሬው እየበረታ የሄደው የኢትዮጵያ መንግሥት፤ በክልሉ ያሉትን ዜጎች እያስተዳደረና ኢትዮጵያዊነትን እያጎለበት በሄደ ጊዜ፤ ለረጅም ዘመን በኢትዮጵያዊ መንግሥታት ሥር የነበሩ ክልሎችን አምጡ ማለቱና፤ የአውሮፓዊያንን የቅኝ ግዛት በአካባቢው ለማስፋፋት መሯሯጥ የሚገታ መሆኑ ሁሉንም አስጋ። እናም ይህ የውጪ ያላባራ ተንኮል፤ ሀገራችን ባሉት ባላባቶች ውስጥ፤ ያላቋረጠ የመጠፋፋት መናኮርን አፋፋመ። አንድና ሁለት ጠመንጃዎች ካስርና ሃያ ጥይቶች ጋር በመጸሐፍ ቅዱስ በመጠቅለልና በማቀበል ቆስቋሾቹ እያራገቡት፤ ግለቱ እየጨመረ፤ አንድ ጳጳስ በመላክ ውስጡን እያመሱ፤ ትርምሱ እያደገ፤ በሀገራችን ውስጥ የጎጥ ገዥዎች አየሉ። በዚያ ጊዜ የተተከለው መርዝ አሁንም እያመረቀዘ፤ ጥዝጠዛውና ግማቱ እኛን አፍኖናል። እንዴት? ይህን ነው የዚህ ጽሑፍ ማጠንጠኛ። አንድ ቢሆኑ ኖሮ!

ከፍጻሜ መንግሥት አንስቶ አፄ ቴዎድሮስ እስከተነሱበት ድረስ፤ ዘመነ መሳፍንት እየተባለ የሚጠራው የታሪካችን ወቅት፤ ምን ያህል የሀገራችን ዕድገት ወደ ኋላ እንዲጎተት እንዳደረገው በሰፊው የተመዘገበ ነው። ይህ ዘመን፤ ለረጅም ጊዜ፤ እየተዋጉም ሆነ አባት ለልጁ እያወረሰ፤ ተከታታይነት የነበረውን የማዕከላዊ መንግሥት ሕልውና ከጥያቄ ውስጥ አስገባው። እኔስ ከማን አንሳለሁ በማለት፤ ወገኖቹንና ነፍጥ በማሰባሰብ፤ ያካባቢው ገዥ እኔ ነኝነት ነገሠ። በዳር ዳር በሚባሉ አካባቢዎች የሚገኙት ዜጎች ከማዕከላዊው መንግሥት የነበራቸው ግንኙነት ላላ። ትግራይ፣ ወሎ፣ ወልቃይት፣ ላስታ፣ የጁ፣ ስሜን፣ ሸዋ፣ ጎጃም፣ ቋራ፣ ከፋ፣ ሐረር፣ ኦጋዴን፣ ሞያሌ፣ የሚባሉት ክፍሎች፤ የየራሳቸው ጉልበተኞች እንደራሴዎች ሆኑባቸው። ሲደክሙ ለጉልበተኛው እየገበሩ፣ ሲጎለብቱ ራሳቸው እያስገበሩ፤ መንግሥታዊ ተግባር የሚባለውን ረስተው፤ ነፍጥ መሰብሰብንና ለሚቀጥለው ውጊያ መዘጋጀትን፤ የሕልውናቸው አውታር አደረጉት። ትብብር ማለት፤ እኔን ነገ እስከጠቀመኝና እሱን ወግቼ እስካቸነፍኩት ድረስ በሚለው ስልት ተለወጠ። እንግዲህ ይህ የውስጡ ሀገራዊ አስተዳደሩ ነበር። መቼም ይህ ለሁላችን ግልጽ ነው። ታሪክ መመርመር ሳይሆን ያለንበትን መመርመሩ በቂ ማስረጃ ነው። የውጪ ጣልቃ ገቦች ለዚህ ሂደት ምን ያህል ተጠያቂነት አላቸው? አሁን ላለንበትስ? እንግዲህ እዚህ ላይ ነው የዘመነ መሳፍንት ቅርሳችን እና የፖለቲካ መሪዎቻችን ተወራራሽነት በግልጽ የሚታየው። አንድ ቢሆኑ ኖሮ!

አፄ ቴዎድሮስ ለዘመነ መሳፍንት ፍጻሜ ከሠጡት ይሄው ከአንድ መቶ ሃምሳ ዓመት በላይ ሆኖታል። ዘመኑን እንጂ አብሮን ያለውን አመለካከቱን ማለቴ አይደለም። በአእምሯችን ያንን የታሪካችንን ወቅት ብናስወግደውና ተከታታይነቱን የጠበቀ የኢትዮጵያ መንግሥት ቢኖር ኖሮ የሚለውን አስተባቅተን፤ አሁን ሀገራችን ልትደርስበት የምትችልበትን ብናጤን፤ አሁን ካለንበት ምን ያህል ይለይ ነበር? መቼም የታሪክ ሂደት በሰዎች እቅድና ፍላጎት እንደማይመራ ዕውቅ ነው። ታልሞና ተቀምሮ የሚነደፍና የሚገፋ እንዳልሆነ ስቼ አይደለም። ነገር ግን ትልሙን በመዘርጋት ዕይታ ለመፍጠር ስል ነው። የተደናቀፈው ሁሉ ቢስተካከል፤ የት ልንደርስ እንችል እንደነበር መገመቱ ቀላል ነው። በአኳያው ደግሞ፤ ከዚያ ትምህርት ወስደን፤ የያኔውን ወቅት ስህተት አለመሥራቱ፤ የኛ ታሪካዊ ግዴታ ነው። እንደያኔዎቹ አሁንም ያንኑ ሆኖ መገኘት፤ ጅልነት ነው። ጅልነቱም በቀላሉ ሲመነዘር ነው። ከዚያ ለከፋ ስድብ ራስን ማሰለፉ አልጥም ስላለኝ ነው። እንደያኔዎቹ የየራሳችን ቦታ ባንይዝም፤ በትካቸው ድርጅቶች አሉን። እናም የየድርጅቶቻችን ንጉሥች አሉን። ዙፋኑንም ለማንም ላለማውረስ፤ ለሚነሳው ተቀናቃኝ የስድብ ውርጅብን በመቆለል ትንንሽ ሌሎች ድርጅቶች እየተፈጠሩ፤ ተደላድለው በመቀመጥ ዓመታትን ያስቆጠሩ ስንት ንጉሦች አሉን? እንግዲህ ቦታውና በዙፋኑ የተቀመጠው ንጉሥ፤ በድርጅት ተተክቷል። እንደራሴዎች የሆኑት ያሁኖቹ የድርጅቶቻችን መሪዎች ናቸው። ሀገር ማለት፣ ወገን ማለት፣ ታሪክ ማለት፣ ድርጅት ሆኗል። በቃ አለቀ በቃ! የኔ ድርጅት ያቸንፍ! አለያ ገደል ግቡ ተብለናል። ተሳስቼ ይሆን? አንድ ቢሆኑ ኖሮ!

የያኔዎቹ ባላጋራቸውን እያብጠለጠሉ ለውጭ መንግሥታት አቤቱታ በማቅረብ ይለምኑ ነበር። አሁን ደግሞ ሌላውን ታግይ ድርጅት መኮነን፣ ሰላማዊ ሰልፍ በውጭ ሀገሮች ማድረግና መታገያ እንዲሆነን የበጎረቤት ሀገር መጠጋቱን ሙያችን ብለነዋል። ድንቄም! አለች ጎረቤቴ! አንድ ቢሆኑ ኖሮ!

(አንዱዓለም ተፈራ – የእስከመቼ አዘጋጅ)
እሁድ ታህሣሥ ፳ ፱ ቀን ፳ ፻ ፯ ዓመተ ምህረት (12/7/2014)

ተጨማሪ ጽሁፎችን በአቶ አንዱ ዓለም ተፈራ ብሎግ ላይ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule