በ1967 የወሎ ሕዝብ በድርቅ ሲረግፍ ንጉሱ ለልደታቸው ከእንግሊዝ አገር በመጣ ኬክና ከእስኮትላንድ በተጫነ ውስኪ ይራጩ ነበር የሚል ዜና ደርግ ሲያስነግር አገሪቷ በሰላማዊ ሰልፍ ቀውጢ ሆነች። ይህም የቀዳማዊ ኃይለስላሴን አገዛዝ ለመገርሰስ ግብዓት ሆነ። በ1977 የትግራይና የወሎ ሕዝብ በረሃብ ሲረግፍ ደርግ አስረኛ የልደት በአሉን ለማክበር ከኮሪያ ባስመጣው ርችት ታጅቦና አገሪቷን በቀለም አዥጎርጉሮ ያረግዳል የሚል ዜና ሲያስተጋባ ምእራባውያን ለሕወሃት/ኢህአዴግ ከፍተኛ እርዳታና ይሁንታ ሰጡ። ይህም ለደርግ መውደቅ የራሱን አስተዋጽኦ አበረከተ። በ2008 ድርቅ አስር ሚሊዮን የሚሆን ወገናችንን ሲያጠቃ ኢህአዴግ ሰፋ ብላ የድርጅቶቿን ልደት በሚሊዮን በሚቆጠር ብር እያከበረች ነው። ይህ ሁሉ ወገን በሚራብበትና በሚቸገርበት አገር ውስጥ ከሰሞኑ የተነገረው ዜና ደግሞ ጆሮ ጭው … [Read more...] about ለሌባ ባለሥልጣናት መጦሪያ ቤት?
Right Column - Primary Sidebar
ብሔር ወይስ ሰው-ነት?
መኃኑን ታሪክ ለማዋለድ በሚደረገዉ "ጥረት" አብዝቼ ባዝንም፣ የቀደመዉን የሃገሬን ጠመዝማዛ የታሪክ መንገድ ግን ከነእንከኑ እቀበለዋለሁ፡፡ የታሪክ ክህደትም ሆነ የታሪክ ብዜትን ሊጭኑብኝ ለሚሞክሩ ሰንባችም ሆኑ አርፋጂ ብሄረተኞች ጆሮዬንም ሆነ አዕምሮዬን የምሰጥ ሰዉ አይደለሁም፡፡ ትላንትን በዛሬ መነጽር ባላየዉ እንኳን የቀደመዉን ዘመን በሰብዓዊነትና በማህበረሰባዊ ዉል ሚዛን ላይ አስቀምጬ እንድመለከተዉ ሰው-ነቴ ያስገድደኛል። ሰው ነኝና። ሰው።. . . . በገባኝ መጠን የዛሬዋን ቁርጭምጭሚት ኢትዮጵያ ወደ ቀደመ ከፍታዋ ለማውጣትና ገጽታዋን ለማደስ ሲሚንቶው ሰብዓዊነት ሊሆን ይገባል። ከብሔር አጥር ባሻገር ዜግነት የሚባል ሰፊ ሜዳ እንዳለ ልብ እንበል። ኢትዮጵያችንን ከሁለንተናዊ ውድቀት ለመታደግም ሆነ ዳግም ለመገንባት የቀጥታ ፖለቲካዊ ተሳትፎ ብቻ መፍትሄ አይደለም። ይልቁንስ … [Read more...] about ብሔር ወይስ ሰው-ነት?
Center for the Rights of Ethiopian Women welcomes Reeyot Alemu
Center for the Rights of Ethiopian Women (CREW) is delighted to announce the arrival of the award winning journalist, Reeyot Alemu to the United States on Saturday, November 7, 2015. CREW sent invitation to the respected journalist and freedom of speech advocate, Reeyot Alemu and her sister Eskedar Alemu to speak at the upcoming Women and Leadership Conference which will be held sometime in the coming month. Reeyot has been imprisoned for over 4 years and was released in July of 2015. Reeyot … [Read more...] about Center for the Rights of Ethiopian Women welcomes Reeyot Alemu
ሥደት
ቦሳሶ፣ ሶማሊያ ቦሳሶ በገልፍ ባህረ ሰላጤ ደቡባዊ ክፍል፣ሶማሊያ ጠርዝ ላይ የምትገኘው ከተማ፣ ካርታ ላይ ሲመለከትዋት፣ ያፍሪካ ቀንድ ላይ የተቀመጠች ዝምብ ትመስላለች። አፈ ታሪክ ስለከተማዋ አሰያየም እንዲህ ይላል። ቦሳሶ የቀድሞ ሥያሜዋን ያገኘችው ካንድ ታዋቂ ነጋዴ ሥም ነበር - ባንዳር ቃሲም ከተባለ ነጋዴ። ቃሲም ከተማ እየተባለች ትታውቅም ነበር። ነጋዴው፣ ባንዳር ቃሲም ደግሞ እጅግ በጣም የሚያፈቅራት ቡሳስ የተባለች ግመል ነበረችው። ሥለዚህ ከተማዋ ከጊዜ በኋላ በቃሲም ተወዳጅ ግመል ቡሳስ ተብላ ተሰየመች። እያደር ከቡሳስነት ወደ ቦሳሶ ተቀየረች። አለምሰገድና ባለቤቱ ምህረት፣ ምህረትያንድ አመት ልጃቸውን አቅፋ፣ ከቦሳሶ ተነስተው ከሦስት ሰዓት ጉዞ በኋላ ማሬሮ ገብትዋል። ማሬሮ ገደላማ ናት። ካርቶን አንጥፈው የሚቆረቁረው መሬት ላይ ተቀመጡ። አለምሰገድ ለራሱና ለምህረት … [Read more...] about ሥደት
በስዊድን ለአርበኞች ግንቦት ሰባት መርጃ ገንዘብ ተሰበሰበ
በስዊድን ዋና ከተማ በስቶክሆልም ለአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ መርጃ የሚሆን የገቢ ማሰባሰቢያ ዝግጅት ኦክቶበር 31 -2015 (ጥቅምት 20 - 2008 ዓ.ም) ተደረገ። በዝግጅቱ ላይ በርካታ ኢትዮጵያውያንና ኤርትራውያን ተገኝተዋል። በቦታው ላይ በክብር እንግድነት የተገኙት አቶ አበበ ቦጋለ የውጪ እንቢተኝነት ሊቀመንበር እና አቶ ቸኮል ጌታነህ የንቅናቄው ከፍተኛ አመራር ናቸው። ዝግጅቱ ረፋዱን 14፡00 ሰዓት የተጀመረ ሲሆን አቶ ጌታሁን ማሬ የዝጅቱ አስተባባሪ ኮሚቴ ሰብሳቢ የስዊድን የአርበኞች ግንቦት ሰባት የስራ አስፈጻሚ ሰብሳቢ የሆኑትን አቶ ዘለሌ ፀጋ ሥላሴን ስለዝግጅቱ ገለጻ እንዲያደርጉና ዝግጅቱንም እንዲመሩ ጋብዘዋል። አቶ ዘለሌ በበኩላቸው የከተማው የአርበኞች ግንቦት ሰባት ንቅናቄ ያለበትን ሁኔታ ገልጸው እንግዶቹንም በማስተዋወቅ አቶ አበበ ቦጋለና አቶ ቸኮል … [Read more...] about በስዊድን ለአርበኞች ግንቦት ሰባት መርጃ ገንዘብ ተሰበሰበ
የእኔ፣ ያንተ፣ የእናንተ፣ የእኛ ተጠቂዎች!
የብላቴናው መሀመድን እናት እርዳታ አድራጊ ወገኖቸ የቻልኩትን እርዳታ ለመሰብሰብ ወጣ ባልኩበት አጋጣሚ ስልክ ተደወለልኝ። አነሳሁት፣ ከሰላምታ በኋላ "ጠፋህ? የት ነው ያለህ?" ከሚለው አጭር የተለመደ የሰላምታ ማጀቢያ በኋላ ወዳጀ ወደ መልዕክታቸው ገቡ ... "አንተ ነብዩ የት ጠፋህ?" ሲሉ ደገሙና ስመለጥፋቴ ጠይቀውኝ ሲቀጥሉ "ናና አንድ እህት ከጅዳ ቆንስል በር ወድቃለች፣ ጸሀይ እየደበደበ አድክሟታል! እነሱ (የቆንስል ሰዎች ማለታቸው ነው) ቢነግሯቸው አይሰሙም። ሌላም ሶስት እህቶች ከቆንስሉ አጠገብ ካለው ንጉድ ፉአድ ሆስፒታል ያለ ጠያቂ ተኝተዋል። ጎብኟቸውና ችግራቸውን ተረዱ ወይ መፍትሄ ፈልጉ ወይ ወደ ሀገር ስደዷቸው ብል የሚሰማ የለም! አንተን ከሰሙህ ናና እያቸው!" ብለው ቁጣ የተቀላቀለበት መልዕክት አስተላለፈውልኝ ተጣድፈው ስልኩን ዘጉት ... ! የእኒህ ወንድም … [Read more...] about የእኔ፣ ያንተ፣ የእናንተ፣ የእኛ ተጠቂዎች!
Genocide Committed Against the Amhara in Metekel, Ethiopia
1. Background/Introduction This report has been compiled on the recent incidents of genocide in Wembera and Bulen district (Woredas) of Metekel Zone of Benshangul-Gumuz Regional State in Ethiopia. The report pinpoints and underscores the outrageous atrocities committed by members of the Gumuz ethnic group against Amaras with the full knowledge and encouragement of Tigrean People’s Liberation Front (TPLF), the current Oligarchy ruling Ethiopia. The cruel and inhumane crimes are another sad … [Read more...] about Genocide Committed Against the Amhara in Metekel, Ethiopia
ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የመሸገው “ወገን ለወገን” ቡድን አፍራሽ ተግባሩ ቀጥሎበታል
በጅዳ ቆንስላ ጸ/ቤት የመሸገው “ወገን ለወገን” የተሰኘው ቡድን ጽ/ቤቱ ለሕዝብ መሥራት ከሚገባው ጉዳይ በመውጣት በግለሰቦች ማንነት እና ሃይማኖት ላይ ጽንፈኛ አቋም እየያዘ መምጣቱ ታወቀ፡፡ በሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት “በመልካም አስተዳደር ሽፋን” ዙሪያ ይካሄዳል ተብሎ የተጠራው አሁን ካለው የከረረ ሁኔታ አኳያ ግጭት ያስነሳል የሚል ስጋት ፈጥሯል፡፡ በተለያዩ ሁኔታዎች ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት “በመልካም አስተዳደር” ዙሪያ ሰሞኑን በተደረገው ግምገማ ጥቂት የደቡብ ተወካይ ነን የሚሉ ግለሰቦች አማራውን በብሄር እና የኦርቶዶክስ እምነት ተከታዮችን በሃይማኖት በመከፋፈል የከፈቱት የስም ማጥፋት ዘመቻ ጅዳ እና አካባቢዋን ስጋት ውስጥ ከቷል። በተለይ እራሱን “ወገን ለወገን” እያለ የሚጠራው በአቶ ሰመሩ እና ወ/ሮ ሙሉካ የሱፍ የሚመራው የቆንስላ ቡድን የተካሄደውን ግምገማ ተከትሎ በቆንስላው … [Read more...] about ጅዳ ቆንስላ ጽ/ቤት የመሸገው “ወገን ለወገን” ቡድን አፍራሽ ተግባሩ ቀጥሎበታል
“ማንነት እንጂ ብሔር የለኝም!” አቤል ዋበላ
". . . እኔ ማዕከላዊ በነበርኩኝ ጊዜ አንድ ቀን የተደበደብኩት ብሔርህን ተናገር በሚል ነው። እኔ አዲስ አበባ ነው ተወልጄ ያደኩት። እናትና አባቴ ከሁለት ብሔር ነው የመጡት አንድ ብሔር መርጬ እኔ የዚህ ብሔር አባል ነኝ የምለው ብሔር የለኝም . . . ብሔሮችን አልጠላም. . . እኔ ጥቅል ማንነት ነው እንጂ የሚገዛኝ የአንድ ብሄር ማንነት ታርጋ የግድ ሊለጠፍብኝ አይገባም . . . መጨረሻ ላይ ከመርማሪው ጋር ተማምነን ብሔር የለውም ብሎ ባዶ አድርጎት ነው የተለያየነው . . ." ከዞን 9 ጦማሪያን ውስጥ አቤል ዋበላ ከእስር ከተፈታ በኋላ ከSBS ራዲዮ ጋር ባደረገው ቃለ መጠይቅ ላይ የተናገረው። ቃለ ምልልሱን ለመስማት ይጫኑ። … [Read more...] about “ማንነት እንጂ ብሔር የለኝም!” አቤል ዋበላ
እኔ እንዳዳመጥኩት
መቼም ሰው ይናገራል። እኔ ደግሞ ጆሮ ፈጥሮብኛልና እሰማለሁ። የምሰማውና የማዳምጠው ግን ይለያያል። ባለፈው ሰሞን ቁጥር 00 ሰውዬ ሲናገሩ ሰማሁ፣ “የዛሬ አሥር አመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን” ብለው ሲናገሩ ሰማሁ። እና አዳመጥኩ፣ “የዛሬ አሥር አመት ከ80 ሚሊዮን በላይ ኢትዮጵያውያን ሥራ እናስይዛለን፣ ምክንያቱም አሁን እየቀጠርናቸው ያለነው ቻይናውያን፣ ህንዳውያን፣ ብራዚላውያን፣ ወዘተርፈዋውያን . . . የዛሬ አሥር አመት ኢትዮጵያውያን ይሆናሉ፣ በቁጥርም ከ 80 ሚሊዮን በላይ ይሆናሉ” ብዬ አዳመጥኩ። ያገሬ ህዝብ ደግሞ የቀን ሥራ እንኳን ሳይቀር እየተቀማ ለቻይና ሲሰጥበት፣ ተግቶ ይጸልያል። “የባሰ አታምጣ” እያለ። እኔ ደግሞ አዳምጣለሁ፣ “የባሰ አታምጣ”ን መሥማት ደከመኝ “የተሻለ አምጣ” የሚል ናፈቀኝ” ብዬ። ሌላ ጊዜ ደግሞ ሌላው ቁጥር … [Read more...] about እኔ እንዳዳመጥኩት










