መግቢያ በየጊዜው ለመጻፍ ብዕሬን በመቃጣት ላይ እያለሁ እመለሳለሁ። ይህንን የማደርግበት ምክንያት በእንግሊዘኛም ሆነ በአማርኛ በየድህረ-ገጾች ላይ ተጽፈው ለንባብ የሚቀርቡ ጽሁፎች ስለማያረኩኝ ነው። ይህንን የምልበት ምክንያት እኔ ብቻ በትክክል የምጽፍ ሆኖ ስለሚሰማኝ ሳይሆን የጽሁፎቹን ዓላማ ለማወቅም ሆነ ለመረዳት ስለሚያስቸግረኝ ነው። ሁለተኛ፣ አብዛኛዎች ጽሁፎች በተወሰነ ሃሳብ ላይ ያተኮሩና በዚያው ላይ የሚሽከረከሩ አይደሉም። በሌላ አነጋገር እንድንወያይበትና እንድንከራከርበት በር የሚከፍቱ አይደሉም። ሁሉም እንደፈለገውና እንደመሰለው የሚጽፍ እንጂ ከተጨባጭ ሁኔታዎችና ከህሊና ሁኔታ በመነሳት ችግራችንን የሚተነትን አይደለም። በሶስተኛ ደረጃ፣ በአንዳንድ ድህረ-ገጾች ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በአንድ ግለሰብ ሃሳብና ርዕይ ላይ ያተኮሩ ሳይሆኑ፣ የግለሰብን ስም የሚያጎድፉ ወይም ሞራሉ … [Read more...] about ችግሩ ወያኔን በማስወገድ ብቻ የሚፈታ አይደለም!!
Right Column - Primary Sidebar
ጥቂት ስለ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ
ተግባቢና በሳል ነው፤ ረጋ ባለ አንደበቱ የሚሰማውን በጥሞና መናገር ልዩ ያደርገዋል ፡፡ እምነቱን አጥበቆ ይወዳል፤ የእስልምና ሃይማኖት የሚያዛቸውን ተግባራት (ሶላት መስገድ፣ መጾም…) ፈጽሞ ሌሎች መሰሎቹ እንዲፈጽሙ ማድረግን ያውቅበታል፡፡ ከሌሎች የእምነት ተከታዮች ጋር የመግባባቱና ከሁሉም ጋር በአብሮነት መኖሩ ባጠቃላይ ማህበራዊ ኑሮ የሚጠይቀውን ግዴታ የመወጣት ልዩ ችሎታ አለው፡፡ ከማንም ሰው ጋር የመግባባት፣ ተጫውቶ የማጫወት ክህሎት አለው፡፡ ከቀለሙ በተጓዳኝ ሀይማኖታዊ እውቀቱም የተመሰከረለት ነው፡፡ ሙስሊም ተማሪዎችን በመሰብሰብ በስነ ምግባር እንዲታነጹና ለሀገራቸው ተቆርቋሪ እንዲሆኑ ያስተምራል፡፡ በግቢው ውሰጥ ተሰሚነት ካላቸው የሀይማኖት ሰዎች አንዱ ነበር፡፡ ካሚል ሽምሱን መቀሌ ዩኒቨርሲቲ ሳለ አውቀው ነበር፤ አንድ ባችም ነበርን፤ በህግ ፋከልቲ ተደልድለን ለአምስት … [Read more...] about ጥቂት ስለ ኡስታዝ ካሚል ሸምሱ
አዲስ ዓመት ያለ ተስፋ!?
የተወደዳችሁ የአገራችን የሃይማኖት መሪዎች እንዲሁም የየእምነቱ ምዕመናን፡- ይህንን መልዕክት የምጽፍላችሁ ወንድማችሁ ይህንን ጥሪ የማቀርብላችሁ እንደ አንድ ሰብዓዊ ፍጡር ለእናንተ ሃሳቤን ለማቅረብና እንደ እምነቴ ደግሞ በጌታችን የሱስ ክርስቶስ ባለኝ እምነትም ጭምር ነው። ይህንን ስል ሌሎች እንደ እኔ ዓይነት እምነት የሌላችሁን የሃይማኖት መሪዎችና ተከታዮች ያገለልኩ መስሎ እንዲሰማችሁ ወይም ከእኔ ጋር ተመሳሳይ እምነት በሌላችሁ ላይ ጫና ለማድረስ በጭራሽ ምኞቴ እንዳልሆነ አስቀድማችሁ እንድታውቁልኝ እፈልጋለሁ። የራሴን መግለጼ እንደ አንድ ሰብዓዊ ፍጡር እና እንደ አንድ ኢትዮጵያዊ ማንነቴን አሳውቄ ሃሳቤንም በዚያው መልኩ እንድትረዱልኝ ከማድረግ አኳያ ነው። ኢትዮጵያ በምንላት አገራችን ሁላችንም የተለያየ ሃይማኖት እንከተላለን፤ እንደየ እምነታችንም የአምልኮ ሥርዓታችንን … [Read more...] about አዲስ ዓመት ያለ ተስፋ!?
መልካም አዲስ ዓመት!
የታሪክ አምድ ነባራዊ፣ ምድረ-ህይወት ፍልስፍና፣ መውጣት መውረድ፣ የዓለም ህግ፣ የተፈጥሮ ገጽ ሆነና፣ ጊዜ ክፉ፣ ጊዜ ደጉ..፣ እጥፍ-ዘርጋ፣ ዘመም-ቀና..፣ አንዴ ጽልመት..፣ አንዴ ብርሃን..፣ ባለታሪክ፣ ባለዝና፤ ስትወድቂ..፣ ስትነሺ..፣ በዘመናት ጉዞሽ ሂደት፣ ለዚህ ደረስሽ፤ እልልልል! ሁለት ሺ ሰባት ዓመት! (ሙሉውን ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about መልካም አዲስ ዓመት!
ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር ስብሰባ ባደረገበት ወቅት ሳሞራ የኑስ ህወሃትን ለብሰው፣ ህወሃትን አጥልቀው (ጫማቸውና ሌላው አይታይም እንጂ) ህወሃትን ሆነው ታይተዋል፡፡ “ተጋብዘው ነው” ለማለት ለምትፈልጉ እንትኖች መልሱ ህወሃት ላይ ተጋብዘው ከተገኙ ወደፊት እንደ ሰማያዊ፣ መድረክ፣ ወዘተ ያሉ ተቀናቃኝ ፓርቲዎች በሚያደርጉት ስብሰባ ላይ የፓርቲዎቹ አርማ ያለበት ባርኔጣ አድርገው ይገኛሉ ማለት ነው - የተነፈሰ ሃሳብ ነው፡፡ ሳሞራ ህወሃትን ሲያይ ዋለ ተቃዋሚ ፓርቲ የት ነሽ እያለ ከነጠላው ፉከራ መልስ - “ሕገመንግሥቱ” ያለጥርጥር ተጥሷል፤ ይህ ከሆነ ደግሞ “ሕገመንግሥቱንና ሕገመንግሥታዊ ሥርዓቱን በኃይል ለመናድ …” በሚል ክስ መመሥረት አለበት ማለት ነው፡፡ ይህ ሲሆን ተከሳሽ “አሸባሪ” ሊባል ነው፡፡ ከዚያ ተከሳሽ ወደ … የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር … [Read more...] about ሳሞራ ወይስ ሕወሃት “ሕገመንግሥቱን” የጣሱት? ወይስ ሁለቱም?
ጀርመን አገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና የግብጽ ኮፐቲክ ቤተክርስቲያን የጋራ ሲኖዶስ አቋቋሙ!
በጀርመን የኦርየንታል (የመካከለኛው ምስራቅ) ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያናት አንድ የጋራ ሲኖዶስ ለመመስረት ስለፈለጉ፤ ትላንት የኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያን የመጀመሪያውን እርምጃ ወስደዋል። በዚህም መሰረት ጳጳስ አንባ ዳሚያን (የኮፐት ኦርቶዶክስ) እና ሊቀጳጳስ ሙሴ (የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ) ውል ተፈራርመዋል። በኮፕት ገዳም የውል ሰነድ ፊርማ፤ ሊቀጳጳስ ሙሴ (2. ከገራ ወደቀኝ) እና ጳጳስ አንባ ዳሚያን (የመካከለኛው ) (ከመሃል) ፊረማቸውን በውሉ ሰነድ ላይ አስቀመጡ። በዚሁ ጊዜ በቦታው የነበሩ፤ አባ ዳዊት ሙሳ ከግብጽ እንዲሁም የገዳሙ ጎብኝ እንግዶች/ካቶሊኮች/ ሞሲኞር ፔተር ፎን ሸታይኒትጽ (ከግራ) እና ዲያቆን ክርስቶፍ ፐሪንስ ቤተልሄም (ከቀኝ) እንዲሁም ሚዛን ገብሩ (ሁዋላ ከግራ) ማግዳሌና ግርማ፤ ሳራ ኪዳኔ እና ሞገስ ተሾመ … [Read more...] about ጀርመን አገር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንና የግብጽ ኮፐቲክ ቤተክርስቲያን የጋራ ሲኖዶስ አቋቋሙ!
የኤርትራ ጉዳይ
ለብዙ ኢትዮጵያዊያን፤ የኤርትራ ከኢትዮጵያ መገንጠልና የአገነጣጠሏ ሁኔታ፤ የውስጥ አካላችንን ያኔም፣ አሁንም እያንጠረጠረው ነው። በርግጥ በየኪሳችን ያለ የየግል ንብረት ስለተነጠቀብን አይደለም። በኤርትራ መገንጠል የቀረብን የግል ጥቅም ስለነበረም አይደለም። የሀገር ጉዳይ፤ ከንብረት፣ ከአባትና እናት፣ ከኑሮ የበለጠ ክብር የምንሠጠው ነው። በወቅቱ የቅርብ ጓደኛዬ የነበረ ኤርትራዊ፤ በኤርትራ መገንጠል ፍንደቃው ጊዜ አልሠጥህ ብሎት፤ መኖሬንም ረስቶ፤ ለሳምንታት ከወገኖቹ ጋር ሲጨፍር ከረመ። በመጨረሻም ቀን ቀንን እየወለደ፤ ሳንገናኝ ብዙ ጊዜ አለፈ። መራራቅ መራራቅን ነውና የሚያስከትለው፤ በየጎጣችን ተሸጉጠን፤ በመካከላችን የነበረው ጓደኝነት፤ ጊዜን መቀራረብ አላድሰው አለና ጠፋ። በርግጥ እኔም መላዕክ አልነበርኩም። ልክ ያለሁበት ቤት እንደተቃጠለ፤ በግል ሰው እንደበደለኝ፤ ብሽቀት … [Read more...] about የኤርትራ ጉዳይ
Saluting the greatest Ethiopian “Masinko” man and dissident artist Shambel Belayneh
“Enlighten the people generally, and tyranny and oppressions of body and mind will vanish like evil spirits at the dawn of the day.” -TJ Behold, he is daring, he is a rebel and the fearsome black lion is roaring. “Endyaw zerafewa endeyaw zerafewa, Ye Gondern meret ye humeran meda, Tedanegbet enji mech dagnebet bada. Wede temari bet temeleshi kine, Wendoch kewalubet ewelalhu ene.” Millions of his fans often say Shambel Belayneh is the undisputed successor to the late legendary … [Read more...] about Saluting the greatest Ethiopian “Masinko” man and dissident artist Shambel Belayneh
Je Suis ኢትዮጵያዊ!
ከብሄር ፖለቲካ እንውጣ! የተባበረችውን ኢትዮጵያን እንገንባ! በሁለተኛው የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ ስብሰባ ላይ ጠቅላይ ሚንስትር ኣቶ ሃይለማርያም ደሳለኝ ሲናገሩ ኣገራችንን የሚበትኑ ኣጥፊ ዘሮች ያሏቸውን ሶስት ጉዳዮች ኣነሱ። ኣንደኛው ጠባብነት፣ ሁለተኛው ትምክህተኛነት፣ ሶስተኛው በሃይማኖት ሽፋን የሚራመድ ኣክራሪነት ናቸው ኣሉ። በመሰረቱ እነዚህን ጉዳዮች ኣቶ ሃይለማርያም ለመጀመሪያ ጊዜ ያነሷቸው ጉዳዮች ኣይደሉም። በ”ኢህዓዴግ” ውስጥ ብዙ ጊዜ የሚነሱ ሁሌም ሲባሉ የነበሩ ናቸው። ኣቶ ሃይለማርያም ኣዲስ ነገር ኣልተናገሩም። ለማናቸውም ግን እነዚህ ኣደገኛ ዘሮች ከየት መጡ? ኣገሪቱንስ ወዴት እየወሰዱ ነው? በርግጥ ከብሄር ፖለቲካው ኣዝማሪዎች ኣልፎ ወደ ታች ወርዶ የኔብጤው ተራው ህዝብ ኣካባቢ እነዚህ ዘሮች ጎልተው እየታዩ ነው ወይ? የሚለው ጉዳይና ኢትዮጵያ በምግብ … [Read more...] about Je Suis ኢትዮጵያዊ!
Guddaa saalpaa fariddi guniddaan dhessa
ማስታወሻ፡- ቀጥሎ የምታነቡትን ጽሑፍ በፍቃዱ ኃይሉ በአማርኛና በኦሮምኛ ቋንቋዎች ለአንባቢያን እንዲደርስለት ለነገረ ኢትዮጵያ የላከው ነው፡፡ Dhumnii jaarraa kudha saglaffaa dhuma yeeroo Awuroopaanoonnii ardii Afrikaa hirachuuf murtteeffatan ture. Mootootnii awuuroopaa kan ga’ee isaanii yoommuu fudhatan, ga’een Xaaliyaanii naannawa Itiyoophiyaa tuuree.Weerartoonnii Awuroopha sababni weerarreef ‘’ummata Afrikaa hirriba irra damaqsiinee qaroomsuufii’’ yoo jedhan illee dhugaan yeeroo sanaa garuu kanarraan adda.Sababnii weeraraa innii guddaan … [Read more...] about Guddaa saalpaa fariddi guniddaan dhessa










