አፄ ቴዎድሮስ ያሠሩትን መድፍ (ሴባስቶፖል) ወደ ተራራው አናት ለማውጣት እየተጣደፉ ነው። እሳቸው ጭምር በጉልበት እያገዙ ሲገፋ ውለው ረፋዱ ላይ ከሰፈር ደርሰው ሲመለሱ አንዱ መድፉን ከሚገፉት ተለይቶ ወደ ሰፈር ሲወርድ መንገድ ያገኙትና ቆም ብለው ወዴት ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ? ብለው ይጠይቁታል። “ወደ ሰፈር፣ ወደ ሰፈር እየወረድኩ ነው ንጉሥ ሆይ!” “ምነው ደህናም እማይደለህ?” “ጣቴን ድንጋይ ቀርጥፎኝ ነው ንጉሥ ሆይ!”፤ ትንሽዋን ጣቱን በጨርቅ ነገር ጠቅሎ አንከርፏል። “ና እስቲ! ቀረብ በልና የተጎዳኸውን አሳየኝ”፤ ሰውየው ንጉሡ ጋ ቀርቦ የቋጠራትን ጨርቅ ፈቶ ጣቱን ሲያሳይ ንጉሡ ትንሽ ጭረት ቢጤ ብቻ ያያሉ። “ሌላ ቦታም ተጎተሃል እንዴ?” “የለም! ይሄው ብቻ ነው።” “እና! ይቺን ቁስል ናት! ብለህ ነው ሥራ ትተህ የምትሄድ?” “ይችኑስ ቢሆን በማን ልላካት … [Read more...] about የነጻነት ትግል መጀመሪያው የቀና ልቦና ባለቤትነት ነው
Uncategorized
መቶ ብር ከየት ወዴት?
ትናንት ኣመሻሽ ላይ፤ ከYohanes Molla ጋር ተቀጣጥረን ተገናኘን ፡፡ካልዲስ ገብተን እኔ ኣንድ ፍንጃል ቡና ሳዝዝ ፤ ዮሀንስ ሲያቀብጠው ኣንድ ቡና እና የባራክ ኦባማን ጆሮ የሚያህል ቦምቦሊኖ ኣዘዘ፡፡ በመጨረሻ ኣስተናጋጂቱ የእዳችንን ደረሰኝ ኣምጥታ ጠረጴዛው መሀል ላይ ኣኖረችው ፡፡እሱ እኔ እስክከፍል ሲጠብቅ እኔ እሱ ይከፍላል ብየ ስጠብቅ ካብ ለካብ እየተያየን በጣም እረጅም ጊዜ ተጎለትን፡፡ በመካከሉ የኢትዮጵያን ማህበራዊና ፖለቲካዊ ርእሰ ጉዳይ ጨርሰን "ፌንጣ ስንት እግር ኣላት? ስድስት ነው ኣራት?" በሚል ጉንጭ ኣልፋ ክርክር ተጠመድን፡፡ ወሬ ኣልቆብን ካጠገባችን ከተቀመጡ ተስተናጋጆች ወሬ እየተበደርን ስናወራ ቆየን፡፡ በመጨረሻ ካፌው ጭርር ብሎ ኣስተናጋጆች እንድንወጣላቸው እግራችን ስር መጥረጊያ ኣስገብተው ይጠርጉ ጀመር፡፡ ድንገት በብሄረሰቦች ላይ የሚነገረው ቀልድ … [Read more...] about መቶ ብር ከየት ወዴት?
“ከሞቱት ያልሞትነው!”
'' ….. የለቅሶና የብዙ ዋይታ ድምፅ በራማ ተሰማ፤ ራሔል ስለ ልጆችዋ አለቀሰች፤ ልጆችዋ ስለሞቱባት መጽናናት እምቢ አለች።…." /ማቴዎስ 2፡18/ ኮንፊሽየስ ወደ ጫካ በመሄድ ግዜውን ማሳለፍ ይወድ ነበር ይባላል። ከዕለታት እንድ ቀን እንደተለመደው ወደ አንድ፤ ከአካባቢው 'ርቆ ወደሚገኝ ጫካ አመራ። ከሰዓታት ጉዞ በኋላ ጥቅጥቅ ባል ጫካ ውስጥ እንደደረሰ ለማርፍ ሲሞክር የገጠመው፤ የተለመደው የወፎች ዝማሬና የአበባወችና የዛፎች ውብ ማዕዛ ሳይሆን እጅግ አሳዛኝ ፣ የለቅሶና የሲቃ ድምጽ ነበር። ኮንፊሽየስ የሰማውን ማመን እያቃተው ወደዚያው አመራ፤ ወደ ድምጹ እየተጠጋ ሲሄድ፤ አንዲት ሴት ሳሩን እየነጨች መሬቱን እየቧጨረች የ ''ኤሎሄ'' ዋይታ ታስተጋባለች። ራሱን ለመቆጣጠር እየሞከረ ቀስ እያለ ተጠጋት። ሊያጽናናትም ሞከረ። ግን የምትጽናና ሴት ሁና አላገኛትም። ይሁን እንጂ በዚህ … [Read more...] about “ከሞቱት ያልሞትነው!”
ጨለማው ሳምንት
ወጣት እየሩሳሌም አስፋው እንደወትሮው ቴሌቭዥን ከፍታ እየተመለከተች ነው። ብርቱካንማ ቱታ የለበሱና፣ እጆቻቸው የፍጢኝ የታሰሩ ወጣቶች በአሸባሪዎች ታጅበው ሲጓዙ ያሳያል ቴሌቭዥኑ። ለእርድ ከተሰለፉት ወገኖች ፊት ለፊት ላይ ያለው የእየሩሳሌም ወንድም ነበር። ሌላኛው ወንድሟም ከበስተኋላ ተሰልፏል። እያሱ ይኩኑዓምላክ እና ባልቻ በለጠ፤ ሁለቱም በዚያች ቅጽበት ክቡር ነብሳቸውን በግፈኞች ተነጠቁ። ከሁሉም የከፋ የሚያደርገው ደግሞ ወዳጅ ዘመዶች የነዚህን ወገኖች አስከሬን አግኝተው ለመቅበር እድል እንኳን ባለማግኘታቸው ነው። የሁሉንም ልብ የሚሰብር ክስተት! "ወንድሞቼ ያልፍልኛል ብለው ከቤት እንደወጡ እዚያው በበረሃ ቀሩ።" ትላለች እየሩሳሌም። እትብታቸው የተቀበረባትን ሃገር ለቀው ሲወጡ ጣሊያን ለመግባት ነበር ዕቅዳቸው። አውሮፓን አልመው ቀዬአቸውን ለቅቀው የወጡ እነዚህ ወጣቶች … [Read more...] about ጨለማው ሳምንት
በጋሞ ጎፋ ፖሊስ በህዝብ ላይ የጭካኔ እርምጃ ወሰደ
በጋሞ ጎፋ ዞን ምዕራብ አባያ ወረዳ አልጌ ቀበሌ ፖሊስ በንፁሃን ላይ የጭካኔ እርምጃ መውሰዱን የአካባቢው ነዋሪዎች ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በአባያ ሀይቅ ዙሪያ በእርሻ ስራ ላይ የተሰማሩት ነዋሪዎች መሬት ትንባሆ ለሚያለማ ባለሀብት እንደተሰጠባቸው መነገሩን ተከትሎ የአካባቢው ሽማግሌዎች ከሶስት ጊዜ በላይ ለክልሉ አስተዳደር ማመልከቻ ቢያስገቡም መልስ ሊያገኙ እንዳልቻሉ ገልጸዋል፡፡ የክልሉ አስተዳደር ምንም አይነት መልስ ባይሰጥም የዞኑ አስተዳደር "መሬቱ ትንባሆ ለሚያለማ ባለሀብት ተሰጥቷል" የሚል ውሳኔ በማስተላለፉ ነዋሪዎቹ ይህን የዞኑን አስተዳደር ውሳኔ እየተቃወሙ ይገኛሉ፡፡ ይህን የህዝቡን ተቃውሞ ተከትሎም ፖሊስ በአባያ ነዋሪዎች ሰፈር እየመጣ እያስፈራራ እንደሚመለስ ነዋሪዎቹ ገልጸዋል፡፡ የካቲት 30/2007 እንደተለመደው ፖሊስ ነዋሪዎቹን ለማስፈራራት ወደ ሰፈር … [Read more...] about በጋሞ ጎፋ ፖሊስ በህዝብ ላይ የጭካኔ እርምጃ ወሰደ
በኢትዮጵያ ዝሆኖችም “ተሸብረዋል”
ኢህአዴግ በሥልጣን በቆየባቸው 25 ያህል ዓመታት ውስጥ በኢትዮጵያ ከሚገኙ መቶ ዝሆኖች ውስጥ ከዘጠና በላይ የሚሆኑት ሞተዋል፣ ወደ ጎረቤት አገር ተሰድደዋል፣ የደረሱበት አይታወቅም፣ . . . ሲሉ የዓለም የመገናኛ ብዙሃን ዛሬ (አርብ) ዘግበዋል፡፡ የዝሆኖችን ግድያ ለማስቆም በሚል የብአዴኑ ደመቀ መኮንን ከዝሆን ጥርስ የተሰራ ስድስት ቶን የሚመዝን ጌጣጌጥ እንዲቃጠል እሣቱን በለኮሱበት ጊዜ ኢህአዴግ በአገዛዝ በቆየበት 25 ዓመታት ውስጥ የኢትዮጵያ ዝሆኖች ቁጥር ከ90በመቶ በላይ ለምን ሊቀንስ እንደቻለ የተናገሩት ነገር የለም፡፡ ኢህአዴግ ከቻይና ጋር ከተፋቀረበት ጊዜ ጀምሮ የዝሆን ቀንድ ንግድ እየተጧጧፈ እንደሄደ የሚናገሩ ጥቂቶች አይደሉም፡፡ በዚህም “ጮማ” ንግድ ውስጥ ቢጂንግን፣ ሲንጋፖርን፣ ታይላንድን፣ … መመላለሻቸው ያደረጉ ቱባ ባለሥልጣናትና ደላሎቻቸው ይጠረጠራሉ፡፡ … [Read more...] about በኢትዮጵያ ዝሆኖችም “ተሸብረዋል”
ጸረ- ወያኔው ትግል ይፋፋም!
የወያኔን ጸረ-ዴሞከረሲያዊንት ለማስረገጥ ሐቁ ሞልቶ መፍስስ ከጀመረ ብዙ ዓመታትን አስቆጠረ። ወያኔ ለህግ የበላይነት ይገዛል ብሎ ማስብ ከእባብ እንቁላል እርግብ እንደመመኘት ይሆናል ብንል ማጋነን አይሆነብንም። ወያኔ ክፍጥረቱ ጀምሮ እሰክዛሬ ድረስ ከሐቅ ተጣልቶ፣ ሀሰተን አንግሶ፣ ጥላቻን ተላብሶ በማደናገርና በማወናበድ ፓሊሲ የተመራ በመሆኑ አሁንም እድሜውን ጨርሶ በማብቂያው አዝማሚያ ያላደገበትን፣ ያልለመደውን ፍትህና ዴሞከርሲያዊ ባህሪ እንዲያሳይ ልንጥብቅ ከቶ አይግባም። (ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about ጸረ- ወያኔው ትግል ይፋፋም!
“እግዚአብሔር ያሳየዎ: ክርስቶስ ያመልክተዎ!”
እግዚአብሔር በሚያሳየው ክርስቶስ በሚያመለክተው መስመር የማይሰለፍ፤ በቡድንና በጥቅም በተራቆተ ስሜት ተሳስሮና ተለባብሶ የሚኖር ህብረተሰብ፤ ከራሱ በሚፈልቅ ስሜት ወይም ከውጭ በሚመጣ ግፊት ከመጠፋፋት ቢያመልጥም፣ ከመለያየት ማምለጥ ፈጽሞ አይችልም። ክርስቶስም “እርስ በርስዋ የምትለያይ አገር ሁሉ ትጠፋለች። እርስ በርሱ የሚለያይ ከተማ ወይም ቤት አይቆምም” (ማቴ 12።5)በማለት አስጠንቅቋል። ፍረዱብን እያሉ ተቆራኝተው ሰሞኑን ወደኛ በቀረቡት በማህበረ ቅዱሳንና በአባማትያስ መካከል የተከሰተው ይህ ነው። (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about “እግዚአብሔር ያሳየዎ: ክርስቶስ ያመልክተዎ!”
ንዋየ ሙሾ
ዋይ ! ዋይ ! (በሙሾ ዜማ ይውጡት) ንዋይ ዋይ! ዋይ! ንዋይ ንዋይ ሞተ አሉ በቁሙ ንዋይ ሞተ አሉ በቁሙ ጨለመችበት ዓለሙ (2) ንዋይ በንቁላል ተመታ ንዋይ በንቁላል ተመታ ሊዘፍን መጥቶ በማታ (2x) ዋይ! ዋይ! ንዋይ ዋይ! ዋይ! ንዋይ ምን ይላት ይሆን ለሚስቱ ምን ይላት ይሆን ለሚስቱ በንቁላል ገምቶ ደረቱ (2) ጀግናው ፈረሰ ለሆዱ ጀግናው ፈረሰ ለሆዱ እንደ አሜሪካን ልማዱ (2) ኡ ውይ … ( ረገዳ ) ኡ ውይ … ኡ ውይ … ዋይ ! ዋይ ! ንዋይ ዋይ! ዋይ! ንዋይ በጨፈረበት መሬት በጨፈረበት መሬት ተቀበለበት ውርደት (2) ጥላው ሄዳለች በፊትም ሚስቱ ጥላው ሄዳለች በፊትም ሚስቱ ለወለደችው ይብላኝ ለናቱ ዋይ! ዋይ! ንዋይ ዋይ! ዋይ! ንዋይ ምነው ምነው ምነው ምነው ንዋይ (በለዘብታ የድምጽ … [Read more...] about ንዋየ ሙሾ
Getting to know me better
I am in the process of weaning myself from my daily dose of reading about the madness of Woyane. It is not easy. After over two decades of being visually, mentally and spiritually assaulted regarding the evil nature of the Tigray peoples liberation front I am desperately trying to go cold turkey. There was no one spared from informing me everything about the all-powerful, omnipotent Woyane and its evil ways. Even the ‘venerable’ VOA was caught spinning. It wasn’t not long ago that I used to … [Read more...] about Getting to know me better










