የህወሃት/ኢህአዴግን የሰብዓዊ መብቶች ይዞታና አጠቃላይ አስተዳድርን የሚወቅስ የህግ ረቂቅ ዛሬ በዩናይትድ ስቴትስ የሕግ መምሪያ የውጭ ጉዳዮች ኮሚቴ ፊት ቀርቦ በሙሉ ስምምነት አልፏል። ከውሳኔው በላይ የአሜሪካ ወዳጅ በመሆን ሕዝብን ለመከራና ስቃይ ሲዳርግ የኖረው የኢህአዴግ አገዛዝ በአሻባሪነቱ ከሚወገዘው ሒዝቦላ እና ከሰሜን ኮሪያ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይ ጋር በእኩል ቀርቦ መታየቱ “የአሜሪካና ኢህአዴግ ወዳጅነት ወዴት?” አስብሏል፡፡ በዕለቱ ዘጠን አጀንዳዎች ለውሳኔ የቀረቡ ሲሆን የኢትዮጵያን ጉዳይ ጨምሮ የአውሮጳ ህብረት ሒዝቦላን አሸባሪ ድርጅት በማለት እንዲጠራው፤ የሰሜን ኮሪያን የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት በተመለከተ ከዚህ በፊት የወጣው እንደገና እንዲተገበር፤ ኬኒያ ነጻና ፍትሐዊ ምርጫ እንዳታካሂድ፣ በቬኒዙዌላ ያለውን የሰብዓዊ፣ ኢኮኖሚያዊ፣ ፖለቲካዊና ማኅበራዊ ቀውስ … [Read more...] about የህወሃት/ኢህአዴግ ሰብዓዊ መብቶች ረገጣ ከሒዝቦላና ሰሜን ኮሪያ ጉዳይ ጋር በሙሉ ድምጽ ውሳኔ አገኘ
Politics
“በመንግሥታችን ምክንያት አገራችን ተከፋፍላለች” ቴዲ አፍሮ
ቴዲ “የአማራ ሙዚቀኛ በመሆን ቀጥሏል” ዘ ጋርዲያን “ወቅቱ አደገኛ ነው፤ አሁን እኔ ቅድሚያ የምሰጠው ለኢትዮጵያ ነው” ቴዲ የፍቅር፣ የዕርቅና አንድነትን መልዕክት በማንገብ ዘፈን ዘፍኖ ገንዘብ ከመሰብሰብና ታዋቂ ከመሆን በላይ የሚለፋው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አዲሱ አልበሙ ከወጣ በኋላ ከእንግሊዙ ጋዜጣ ዘ ጋርዲያን ጋር ባደረገው ቃለምልልስ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ቁልጭ አድርጎ ተናግሯል፡፡ “በመንግሥታችን ምክንያት አገራችን ተከፋፍላለች” ያለው ቴዲ “የአፍሪካ ሞዴል ነበርን” በማለትም የቀደመውን የኢትዮጵያን ታላቅነትና ክብር አስታውሷል፡፡ በቅርብ የተለቀቀውን “ኢትዮጵያ” አልበም በተመለከተና ስለ አገሩ እንዲሁም ስለ ራሱ የህይወት ፍልስፍና የዜና ዘገባ ያወጣው ዘ ጋርዲያን ቃለ ምልልሱን ያደረገው በቴዲ የመኖሪያ ቤት በመገኘት ነበር፡፡ ስለ ቴዲ የቀድሞ … [Read more...] about “በመንግሥታችን ምክንያት አገራችን ተከፋፍላለች” ቴዲ አፍሮ
እምዬ ምኒልክ የኢትዮጵያ መሐንዲስ!
አጼ ምኒልክ በሕይወት ዘመናቸው የሰሯቸውን ድንቅ ተግባራት በደማቅ ብእርና ብራና የተከተቡ ናቸው! 1835 ዓ.ም. -------------ወፍጮ (በ1835ዓም ገደማ የሸዋው ንጉሥ ሣህለሥላሴ ነበሩ በውሃ የሚሥራ ወፍጮ ያስተክሉት ሆኖም በደረሰባቸው ተቃውሞ ሳይሳካላቸው ቀረ:: ተቀውሞውን አሸንፈው ምኒልክ በ1893ዓም አዲስ ወፍጮ አስተከሉ) 1882 ዓ.ም. -------------ስልክ 1886 ዓ.ም. ------------ፖስታ 1886 ዓ.ም. ------------ባህር ዛፍ 1886 ዓ.ም. ------------ገንዘብ 1886 ዓ.ም. ----------የውሃ ቧንቧ 1887 ዓ.ም. -----------ጫማ 1887 ዓ.ም. --------------ድር 1887 ዓ.ም. -------------የሙዚቃ ት/ቤት 1887 ዓ.ም. ----------የፅህፈት መኪና 1889 ዓ.ም. … [Read more...] about እምዬ ምኒልክ የኢትዮጵያ መሐንዲስ!
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! “ክፋት” – በሁሉም መስክ!!
መርዛማ ፍሬ 11፡ የታሪክ መቃብር! በስሜት በሚነዳ የዘውግ ፖለቲካ ውስጥ ታሪክ ትልቅ ማገዶ ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ታሪክ አካታችነት ባለው መልኩ በአጎልባች ሚና (ብሔራዊ ተዋፅዖ) መፃፍ እየተገባው ምክንያታዊነትን አስመንኖ የልዩነት ሃረጎችን ብቻ በመምዘዝ በየአቅጣጫው የሚፃፍ መሆኑ ከተካረረ ሙግት ሊፀዳ አልቻለም። መዋቅራዊ ድጋፍ ባለው መልኩ የታሪክ ሙግቱ እየተካረረ በመምጣቱ ብሔራዊ ርዕይ ርቆን የመንደር አጥር እስከመስራት ደርሰናል። ደርግ በየትኛውም ያህል መጠን አምባገነንና ጨፍጫፊ ሆኖ ቢገኝም የኢትዮጵያን ታሪክ ሲንቅና ሲያንቋሽሽ አልተገኘም። ከቶውንም ለብሔራዊ ርዕይ መፍጠሪያነት እንደግብዓት ተጠቅሞበታል። ከመነሻው ጀምሮ ኢትዮጵያዊ ስሜትን (የጋራ ማንነትን) በመካድ ራሱን ብቸኛ የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጭ ግንባር አድርጎ የሰየመው ህወሓት፣ የአገሪቱን የረዥም ጊዜ ታሪክ … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! “ክፋት” – በሁሉም መስክ!!
የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?
አቶ አሰፋ ጫቦ ከአርባ ዓመታት በላይ ከዘለለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ ጎልተው የታዩ ሰው ነበሩ። እንዲሁም ሊጽፏቸው የፈለጓቸውን ነገሮች የራሳቸው በሆነ የአፃፃፍ ስልት የሚያቀርቡ፣ ስለነበሩ በዚሁ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ ሞገስና ውዳሴ አትርፈዋል። በቅርቡም የትዝታ ፈለግ የሚባል መጽሐፍ አሳትመው ሕዝብ እንዲያነበው አድርገዋል። የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በአቶ አሰፋ የፖለቲካ ሕይወት ወይም ስነጽሁፋቸውን ለመቃኘት ሳይሆን የአሟታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ቬሮኒካ መላኩ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ ተመርኩዞ የተነሳ ነው። ቬሮኒካ መላኩ በጽሑፋቸው አቶ አሰፋ ከመሞታቸው በፊት በነበሩ ቀናት ውስጥ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኙ እንደነበር በመገልጽ ለቦርከና ድረገጽ ባለቤት ወደ ደረሰው መልዕክት ይንደረደራሉ። በመልዕክቱም ግሪጎሪ ማኬንዚ የተባሉ ሰው አቶ አሰፋን እንደሚያውቁ ሁለቱም ዓለም በቃኝ እስር … [Read more...] about የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች — የአንድ ጎጥ የበላይነትና የመበታተን አደጋ!
ራሳቸውን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር” ብሎ በመሰየም የትግራይን ሕዝብ ሽፋን በማድረግ፤ “የምታገለው ለአንተ ነጻነት ነው” በማለት፤ መልሶ እታገልለታለሁ ያለውን ሕዝብ ያስጨፈጨፈው፣ ያስራበው፣ የግፈ ሰለባ ያስደረገው፣ … ራሱን ህወሓት እያለ የሚጠራው የወንበዴዎች ቡድን የኢትዮጵያን የሥልጣን መንበር ከተቆናጠጠ በኋላ የትግራይ ሰዎችን በሌላው ኢትዮጵያዊ ለማስጠላትና “ስም ለማሰጠት” እንዲሁም ለማጠልሸት ባለፉት 26ዓመታት ሲሰራ ቆይቷል። እነዚህ በኮ/ሎ ጎሹ ወልዴ አነጋገር “የሰከረ ርዕዮትዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ የተጠመቁ፣ እንኳንስ 50 ሚሊዮን ህዝብ ያላት አገር ቤተሰብን የመምራትና የማስተዳደር ተሞክሮ የሌላቸው፣ …” የኢትዮጵያን ሃብት እየዘረፉ በትግራይ ኢንቨስት በማድረግ፣ የትግራይ ተወላጆችን የተለያዩ … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች — የአንድ ጎጥ የበላይነትና የመበታተን አደጋ!
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመንግሥት ውሸት፣ የሃይማኖት ተቋማት ውድቀት፣ … (ክፍል ሦስት)
የትግራይ ሕዝብ “ነጻ አውጡኝ” ብሎ ሳይሰይማቸው፣ ሳይመርጣቸው፣ ሳይጠይቃቸው፣ ራሳቸውን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር” ብለው የሰየሙ ወንበዴዎችና ሽፍቶች የምኒልክ ቤተመንግሥት ከገቡ 26 ዓመታት ተቆጥረዋል። በቂም፣ በበቀል፣ በክፋትና በኢሞራላዊ ተግባራት የተሞሉ፤ ኢትዮጵያዊ መሆናቸው ፈጽሞ የሚያጠራጥር፤ ማንነታቸው ይህ ነው ተብሎ የማይታወቅ፤ በሐሰት ስም ከበረሃ እስከ ቤተመንግሥትና ዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የታዩ፤ በሐሰት ፕሮፓጋንዳ የትግራይን ሕዝብ ያስጨፈጨፉ (ሐውዜንን ይጠቅሷል)፤ ሲነሱ አንዳች ገንዘብ ያልነበራቸው መናጢዎች በበረሃ የድሃ ረሃብተኛ እህል ዘርፈው በመሸጥ፤ ሥልጣን ከያዙ በኋላ ደግሞ የኢትዮጵያን ሐብት ሙልጭ አድርገው ዘርፈው ሲያበቁ “የራሳችን ንብረት ነው” በማለት ኤፈርት የሚባል የወንበዴዎች ሃብት ማከማቻ ቋት የፈጠሩ፤ ከበረሃ እስከ መንግሥታዊ ሥልጣን … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመንግሥት ውሸት፣ የሃይማኖት ተቋማት ውድቀት፣ … (ክፍል ሦስት)
“ሲሾም ያልበላ… ድሮ ቀረ” — [የግንቦት 20 ወግ]
አንጀት አርስና አንገት አስደፊ አስተያየት አንጀታቸው ካረረ ሽማግሌ። በመስሪያ ቤታችን የግንቦት 20 በዓልን እያከበርን ነው። ክቡር ሰብሳቢው ድምፃቸውን ከፍ አድርገው ብዙ የበዙና የተባዙ የለውጥ ማሳያዎችን ሲናገሩ ቆይተው በመጨረሻ እንዲህ አሉ፡- "...ባጭሩ ከግንቦት 20 ድል በኋላ ተቆጥሮ የማያልቅ ብዙ ለውጥ አምጥተናል። በተለይም ኪራይ ሰብሳቢነትን በመታገል ረገድ ሙስና በማኅበረሰቡ ዘንድ ነውር ሆኖ እንዲታይ አድርገናል። ሁላችሁም እንደምታውቁት ድሮ ድሮ... "ሲሾም ያልበላ ሲሻር ይቆጨዋል"... እየተባለ በድፍረት ይነገር ነበር። ይህ ማለት ሲሾሙ መብላት ሲሻሩ ላላመቆጨት ወሳኝ መሆኑን ኅብረተሰቡ አምኖበት ነበር። አሁን ግን ይህ አባባል እየቀረና እየተረሳ ነው። ይህም የትግል ውጤት ነው።" ሰብሳቢው ይህንን በክብር እየተናገሩ እያለ ጋሽ ደፋሩ እጃቸው ላጥ! አድርገው አወጡ። … [Read more...] about “ሲሾም ያልበላ… ድሮ ቀረ” — [የግንቦት 20 ወግ]
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመሬት ነጠቃና ስደት (ክፍል ሁለት)
የዛሬ 26 ዓመት ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ብሎ የሰየመ የወንበዴዎችና የሽፍታዎች ስብስብ በምዕራባውያን አንጋሾቹ ታግዞ የምኒልክን ቤተመንግሥት ከተቆጣጠረ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ ሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ቃላት እንደ እሣት እየተፉ ታሪክ ፈጽሞ ሊረሳው የማይችለውን ንግግር ያደረጉት ድንቅ ኢትዮጵያዊ ነበሩ – ኮ/ሎ ጎሹ ወልዴ!! ስለ ኤርትራ መገንጠል እና ስለ ህወሃት የአስፈጻሚነት ተግባር የቀድሞው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ የትንቢት ያህል፤ ሳግ እየተናነቃቸው ይህንን ነበር የተናገሩት፤ “… ሆን ተብሎ በተቀነባበረ እቅድ ህወሃት አዲስ አበባን እንዲቆጣጠር የተወሰነው ውሳኔ አሳዛኝና ከቶውንም ሊታመን የማይችል ነው። የሰከረ ርዕዮትዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች – የመሬት ነጠቃና ስደት (ክፍል ሁለት)
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! (ክፍል 1)
የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) የተባለ የወንበዴዎች ስብስብ በምዕራባውያን አንጋሾቹ ታግዞ የምኒልክን ቤተመንግሥት ከተቆጣጠረ ከጥቂት ጊዜያት በኋላ በዩናይትድ ስቴትስ ሕዝብ ተወካዮች ምክርቤት ቃላት እንደ እሣት እየተፉ ታሪክ ፈጽሞ ሊረሳው የማይችለውን ንግግር ያደረጉት ድንቅ ኢትዮጵያዊ ነበሩ – ኮ/ሎ ጎሹ ወልዴ!! ስለ ኤርትራ መገንጠል እና ስለ ህወሃት የአስፈጻሚነት ተግባር የቀድሞው የኢትዮጵያ የውጭ ጉዳይ ሚ/ር ኮሎኔል ጎሹ ወልዴ የትንቢት ያህል፤ ሳግ እየተናነቃቸው ይህንን ነበር የተናገሩት፤ “… ሆን ተብሎ በተቀነባበረ እቅድ ህወሃት አዲስ አበባን እንዲቆጣጠር የተወሰነው ውሳኔ አሳዛኝና ከቶውንም ሊታመን የማይችል ነው። የሰከረ ርዕዮትዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ የተጠመቁ፣ እንኳንስ 50 ሚሊዮን ህዝብ … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! (ክፍል 1)








![“ሲሾም ያልበላ… ድሮ ቀረ” — [የግንቦት 20 ወግ]](https://staging.goolgule.com/wp-content/uploads/2015/01/eprdfs-economic-policy-233x300.jpg)

