• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?

June 7, 2017 06:38 am by Editor 1 Comment

አቶ አሰፋ ጫቦ ከአርባ ዓመታት በላይ ከዘለለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ ጎልተው የታዩ ሰው ነበሩ። እንዲሁም ሊጽፏቸው የፈለጓቸውን ነገሮች የራሳቸው በሆነ የአፃፃፍ ስልት የሚያቀርቡ፣ ስለነበሩ በዚሁ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ ሞገስና ውዳሴ አትርፈዋል። በቅርቡም የትዝታ ፈለግ የሚባል መጽሐፍ አሳትመው ሕዝብ እንዲያነበው አድርገዋል።

የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በአቶ አሰፋ የፖለቲካ ሕይወት ወይም ስነጽሁፋቸውን ለመቃኘት ሳይሆን የአሟታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ቬሮኒካ መላኩ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ ተመርኩዞ የተነሳ ነው።

ቬሮኒካ መላኩ በጽሑፋቸው አቶ አሰፋ ከመሞታቸው በፊት በነበሩ ቀናት ውስጥ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኙ እንደነበር በመገልጽ ለቦርከና ድረገጽ ባለቤት ወደ ደረሰው መልዕክት ይንደረደራሉ። በመልዕክቱም ግሪጎሪ ማኬንዚ የተባሉ ሰው አቶ አሰፋን እንደሚያውቁ ሁለቱም ዓለም በቃኝ እስር ቤት አብረው ታስረው እንደነበርና ጓደኛሞችም እንደነበሩ የአቶ አሰፋን ኢሜይል እንደሚፈልጉ ጭምር ገልጸው ከአውስትራሊያ አሜሪካ በሚመጡ ጊዜ ሊያገኟቸው እንደሚፈልጉ ይጽፋሉ። የቦርከና ድረገጽ አዘጋጅም ይሄንንኑ መልዕክት ለአቶ አሰፋ ይልካሉ። አቶ አሰፋም ማኬንዚን እንደሚያውቁትና ሊያገናኙትም እንደሚፈልጉ ገልጸው መልስ ይሰጣሉ። ከዛ በኋላ ግሪጎሪ ማኬንዚ እና አቶ አሰፋ በተጀመረው መስመር ተጉዘው ይገናኛሉ። በዳላስ ከተማ በሚገኝም አንድ የጣሊያን ሬስቶራንት አብረው ራት ይበላሉ። ለሦስት ሰዓት ያህል ሲጨዋወቱ ካመሹም በኋላ ለሌላ ጊዜ ቀጠሮ ይዘው ይለያያሉ።

አቶ አሰፋ ከራት በፊት የተነሱት በሚመስለው ፎቶ ላይ ጥሩ ሁኔታና ጤንነት ይታይባቸው ነበር ያሉት ቬሮኒካ፤ በማግስቱ ጠዋት ግን ሆስፒታል እንደገቡ፣ የምግብ መመረዝ ሕመም እንዳጋጠማቸው እና ይሄንኑ ለግሪጎሪ ማኬንዚም እንደጻፉ፤ ከዛ በኋላ ግን አቶ አሰፋ ከሆስፒታል ሕይወታቸው አልፎ እንደወጡ፤ አብሮ ራት የበላው እንግዳ ግን ምንም እንዳልሆነ በመግለጽ የአቶ አሰፋ ሕልፈተ ሕይወት ድረስ ያለውን ጉዳይ በዚህ ይቋጫሉ።

ከዚህ አያይዘው ለአቶ አሰፋ ሞት ምክንያት ይሆናሉ የሚሏቸውን ነገሮች ያነሳሉ። የአገር ውስጥና የውጪ አገር የፖለቲካ ድርጅቶች ጋር ሽኩቻ እንደነበራቸው፣ የድርጅቶቹንም እኩይ ባህሪና ሴራ አጋልጠው እንደጻፉ፣ ወደፊትም እንደሚጽፉ፤ ቅራኔያቸው ከነሱ ብቻ ሳይሆን ከእጀ ረዥሙ ከሲ.አይ.ኤ.ም (CIA) ጋር እንደነበርና እሱንም ከማጋለጥ ወደ ኋላ እንዳላሉ። በዚህም ምክንያት የፖለቲካ ድርጅቶቹ ወደፊትም ሕዝብ የማያውቀው ጉዳያችንን ያወጣብናል ብለው እንደሚፈሯቸው CIAም ትንሽም ሆነ ትልቅ ጠላት ንቆ እንደማይተው ገልጸው፤ የገዳይና የተገዳይ ድራማ የሚመስል ነገር በአቶ አሰፋ ሞት እንደሚታይ ጥርጣሬያቸውን አስፍረዋል።

ጸሐፊዋ ተቆርቆሪነታቸውን ገልጸው ይህንንን መጻፋቸው ባያስወቅሳቸውም፤ ከዛ በኋላ ግን እሳቸውም ሆኑ ቤተሰብና ወዳጅ፣ አንባቢም ሆነ ሰሚ፣ ወቃሽም ሆነ ተወቃሽ አንዳቸውም ጉዳዩን ሳያነሱት ወራቶች መቆጠር ጀመሩ። ቬሮኒካ ሄንን ለመጻፍ ብቻ ሲሉ የጻፉ ስላልሆነ ከዛ በኋላ የተሰማ ወይም የተደረሰበት ነገር ካለ ቢጽፉልን መልካም ነበር። ጥርጣሬን ብቻ ጥለው ሲጠፉ ግን፤ ጥርጣሬአቸው ሌላ ጥርጣሬና ጥያቄዎች ሊያስከትል በቃ።

ለመሆኑ ቬሮኒካ ከራት በፊት ይመስላል ያሉትን የአቶ አሰፋን ፎቶ የት አዩ? አቶ አሰፋ ለግሪጎሪ ማኬንዚም የጻፉት ደብዳቤ መኖሩን በምን አወቁ? ጽሑፉንስ ያየው ማነው? እንግዳውስ ጤና መሆኑ የታወቀው እንዴት ነው? ሌላው በጥርጣሬ ውስጥ የወደቁት የፖለቲካ ድርጅቶችን ቤሮኒካ ያነሱትን ለመጠየቅ አልሻም። አፍም ብዕርም ያላቸው በመሆኑ እሱን ለነሱ ትቼ የምጠይቀውን ተጨማሪ ጥያቄ ላንሳ።

የአቶ አሰፋ ቤተሰብ ስለአሟሟታቸው የሚያውቀም ምንድነው? ሐኪምስ በምን ምክንያት እንደሞቱ ያረጋገጠበት መረጃ ምን ይላል? በርግጠኝነት የተነገርው የምግብ መመረዝስ ከምን ተነሳ? ራት ከበሉት ምግብ ከሆነ የበሉበትን የኢጣሊያን ሬስቶራንትን ስለዚሁ ጉዳይ የጠየቀ የለም ወይ? አብሮ ራት የበላው እንግዳስ ስለጉዳዩ ምን ተናገረ? እነዚህና እነዚህን የመሳሰሉን ጥያቄዎች ዓይን አፍጠው የተቀመጡ በመሆናቸው ቬሮኒካም ሆኑ ሌሎች ጉዳዩ ያገባናል የምትሉ ካላችሁ መልስ ስጡ። ተገድለውም ከሆነ “ተገደሉ”፤ የግዜሩን ሞት ሞተውም ከሆነ “ሞቱ” በሉን። አንባቢን ከጥርጣሬ ውስጥ ስለከተታችሁት የአቶ አሰፋ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ ማለቱ አይቀርም።

ቸር ይግጠመን!

ወለላዬ ከስዊድን ለጎልጉል ልከውት የታተመ።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Politics, Social Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Al says

    June 17, 2017 07:28 pm at 7:28 pm

    Veronica is TPLF planted cyber task force creating confusion, spreading hate and weaken the vibrant diaspora. Open your eyes people.

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule