• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“በመንግሥታችን ምክንያት አገራችን ተከፋፍላለች” ቴዲ አፍሮ

July 14, 2017 04:12 pm by Editor 2 Comments

  • ቴዲ “የአማራ ሙዚቀኛ በመሆን ቀጥሏል” ዘ ጋርዲያን
  • “ወቅቱ አደገኛ ነው፤ አሁን እኔ ቅድሚያ የምሰጠው ለኢትዮጵያ ነው” ቴዲ

የፍቅር፣ የዕርቅና አንድነትን መልዕክት በማንገብ ዘፈን ዘፍኖ ገንዘብ ከመሰብሰብና ታዋቂ ከመሆን በላይ የሚለፋው አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አዲሱ አልበሙ ከወጣ በኋላ ከእንግሊዙ ጋዜጣ ዘ ጋርዲያን ጋር ባደረገው ቃለምልልስ የኢትዮጵያን ወቅታዊ ቁልጭ አድርጎ ተናግሯል፡፡ “በመንግሥታችን ምክንያት አገራችን ተከፋፍላለች” ያለው ቴዲ “የአፍሪካ ሞዴል ነበርን” በማለትም የቀደመውን የኢትዮጵያን ታላቅነትና ክብር አስታውሷል፡፡

በቅርብ የተለቀቀውን “ኢትዮጵያ” አልበም በተመለከተና ስለ አገሩ እንዲሁም ስለ ራሱ የህይወት ፍልስፍና የዜና ዘገባ ያወጣው ዘ ጋርዲያን ቃለ ምልልሱን ያደረገው በቴዲ የመኖሪያ ቤት በመገኘት ነበር፡፡ ስለ ቴዲ የቀድሞ ሥራዎች፣ ሰው ገጭተህ ገድለሃል በሚል ክስ ተመሥርቶበት በእስር ስላሳለፈው ህይወቱ፣ አዲሱ አልበሙ በሽያጭ ቀዳሚነትን የያዘ ስለመሆኑ ወዘተ በርካታ ጉዳዮችን በዘገባው አካትቷል፡፡

“ወጣቱ ትውልድ ያለፈውን ታሪኩን በተመለከተ አጣብቂኝ ውስጥ ነው ያለው፤ (የአገራችንን) መልካም ታሪክ የማስተማር ኃላፊነት እንዳለብኝ ይሰማኛል፤ (ወጣቱ) ስላለፈው ታሪክ ስኬት ኩራት ሊሰማው ይገባል” በማለት የተናገረው ቴዎድሮስ ካሳሁን አዲሱ አልበሙ ይህንኑ የኢትዮጵያን የቀድሞ ገናናነት እንደገና በማስታወስ ለአንድነት ጥሪ የሚያደርግ ሥራ መሆኑን ተናግሯል፡፡

በእነዚህና ሌሎች የቴዲ ሥራዎች ላይ ጋዜጣው ትንታኔ ከሰጠ በኋላ ኢትዮጵያን ለመከፋፈል የኖረ ምኞት እንዳላቸው አውሮጳውያን አቅጣጫውን በመቀየር ቴዲ አፍሮን ከአጼ ቴዎድሮስ፣ ምኒልክና ኃይለሥላሴ ጋር በአንድ የዘር ቋት ውስጥ መድቦ ሲያበቃ ሁሉንም አማራ በማለት ከመሰየም አልፎ ቴዲንም የአማራ ብሔረተኝነትን ናፋቂ አድርጎ አቅርቦታል፡፡ ለዚህ አስተሳሰቡ ደጋፊ ማስረጃ ለማድረግም በቴዲ ክፍሎች ውስጥ የምኒልክ ጎራዴ፣ የኃይለሥላሴ ዘመን ሠንደቅ ዓላማና የሳቸው ፎቶ መኖሩን አብሮ አስፍሯል፡፡ ለዚህ መሰሉ ፍረጃ ቴዲ የሰጠው መልስ “ወጣቱ ትውልድ አባቶቹ ለዚህች አገር ምን እንዳደረጉ ማወቅ አለበት፤ ምኒልክ ለዚህች አገር፣ ለአንድነት እና ለጸረ ቅኝአገዛዝ መዋጋታቸው ግልጽ ነው” በማለት ኢትዮጵያዊ ምላሽ ሰጥቷል፡፡

ዓላማ ይዞ የተነሳ የሚመስለው ጋዜጣ ግን ኢትዮጵያ ውስጥ 88 ቋንቋዎች የሚነገሩ ቢሆንም ቴዲ ግን “የአማራ ሙዚቀኛ በመሆን ቀጥሏል” በማለት ቴዲን በዘር ሣጥን ውስጥ ከቶታል፡፡ በመቀጠልም “ከታዋቂዋ የአማራ ድምጻዊት ሒሩት በቀለ” ጉልበቶች ላይ ቁጭ ብሎ እሷ ስትዘፍን ያዳምጥ እንደ ነበር ማስታወሱን ዘግቧል፡፡ ይህ የጋዜጣው ዘገባ አገላለጽ የቀደሙትንም ሆነ አዲሶቹን የኢትዮጵያ ድምጻዊንን በህወሓት/ኢህአዴግ የዘር መስፈሪያ ውስጥ አስገብቶ ለማጥበብ የሞከረ ሆኖ ማግኘታቸውን ለጎልጉል አስተያየታቸውን የሰጡ ገልጸዋል፡፡

ጋዜጣው በማጠቃለያው የቴዲ ሙዚቃ ቅንብሮች ከኢትዮጵያና ከዳያስፖራው ባለፈ መልኩ በዓለምአቀፍ መድረክ ላይ የማይሰሙ መሆናቸውን ከገለጸ በኋላ ምክንያቱንም ሲያስረዳ ቋንቋውም ሆነ የሙዚቃው ስልት ኢትዮጵያዊ በመሆኑ ነው ብሏል፡፡ ከዚህ አልፎም ቴዲን ከሙላቱ አስታጥቄና መሐሙድ አህመድ ጋር በማነጻጸር የቴዲ ሥራዎች እንደ ሁለቱ አርቲስቶች ለምዕራባውያን አድማጮች ቅቡል አለመሆናቸውን ላነሳው ሃሳብ እንደ ተጨማሪ ማድመቂያ አቅርቧል፡፡ ለዚህ ግን የቴዲ ምላሽ “ወቅቱ አደገኛ ነው፤ አሁን እኔ ቅድሚያ የምሰጠው ለኢትዮጵያ ነው” ብሏል፡፡

እንደ ሃሳብ፤ ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ቴዎድሮስ ካሳሁን ኢትዮጵያዊ ድምጻዊ እንደሆነ ያምናል፡፡ በዚህ የ “ዘ ጋርዲያን” ዘገባ ላይ ቴዲን የአማራ አርቲስት ተድርጎ የቀረበው ሃተታ አግባብነት አለው ብለን አናምንም፡፡ የቴዲ አፍሮ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ለዚህ የተዛባ አቀራረብ ማስተካከያ ይሆን ዘንድ በተለይ ለ “ዘ ጋርዲያን” ምላሽ ቢሰጥ ሃሳብ እናቀርባለን፡፡ (Photograph: Mulugeta Ayene AP)


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News, Politics Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. አለም says

    July 15, 2017 04:17 pm at 4:17 pm

    ውድ ጎልጉል፣ ቶም ለተሰኘ ለ”ዘ ጋርድያን” ጸሐፊ ሁለት ጊዜ ማብራርያ ጽፌ ሁለቱንም ጊዜ ሠርዞታል። የመጀመሪያ ቅሬታዬ በሙዚቃው ዓለም ጥላሁንን አለማንሳት አይቻልም የሚል ነው። ሁለተኛው የአገራችንን ታሪክ አለማወቁ መሐሙድ አማራ ሙዚቀኛ አይደለም፤ በአማርኛ ግን ይዘፍናል። በትግርኛ ቢዘፍን አድማጭ 100 ሺህ ሰው አይሞላም [ከትግራይ 4 ሚሊዮን ሕዝብ ሁሉም ሬዲዮ አለው ሁሉም ያደምጣል ካላልን በስተቀር]። በወላይትኛም፣ ወዘተ። አማርኛ ብዙ ሰው የሚሰማው ስለሆነ፣ ከገበያም አንጻር። በበአንጻሩ ዴጃቩ እና አባዲ ለተባሉት ሠፊ መድረክ ሰጥቶአቸዋል። ለ ዘ ጋርድያን ዋና አርታኢ ቅሬታ ማቅረብ ይኖርብናል።

    Reply
    • Editor says

      July 15, 2017 04:57 pm at 4:57 pm

      መልካም ብለዋል አለም። ሌሎችም የርስዎን አርአያነት ቢከተሉ የሚበጅ ይመስለናል። ከሁሉ በላይ ግን የቴዲ አፍሮ የሕዝብ ግንኙነት ክፍል ጋዜጣውን ቢያነጋግር የተሻለ መፍትሔ ያመጣል ብለን እናምናለን።

      ጊዜዎን ወስደው ስለላኩልን አስተያየት እናመሰግናለን።

      የጎልጉል አርታኢ

      Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule