ልብ ማለት ያቃተን ለምን ይሆን? የማንሰለጥነውስ ለምንድን ነው? በፖለቲካ ትግል ውስጥ ዕድሜ ገፍተን የማንበስለው እስከመቼ ነው? አድሮ ቃሪያ፣ አድሮ ጥሬ ... እንዲሉ በጫጫታ ትውልድን የምናሰቃየው ስለ ምንድን ነው? ብዙ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል። ይህ በድህነትና በችጋር የሚቃጠለው ህዝብስ ማን ያስብለት? ማን ይድረስለት? በእነማን ብርሃን ይመልከት? ማን ከጨለማ እንዲወጣ ይምራው? ሩብ ምዕተ ዓመት እንደተባላን እንቀጥል? ያሳዝናል? ያስለቅሳል፣ እጅግ ያንገበግባል ... ንስሃ የማያውቅ የአጋንንት ፖለቲካ ይሏል እኛ ነን!! ችግሩ አንድ ወገን ዘንድ ብቻ አይደለም። ችግሩ ሁሉም ዘንድ በውጭም በውስጥም ነው። በውስጥ የተመቸ የመፎካከሪያ ሜዳ የለም። እያደር ይሻላል ሲባል ጭራሹኑ ህወሃት/ኢህአዴግ ሌሎችን “አያገባችሁም” አለና አረፈው። ይህ አልበቃ ብሎ ምክንያት እየተፈለገ ማሳደድና … [Read more...] about የአጋንንት ፖለቲካ – ውጣ!!
ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፣ ሄኖክ የሺጥላ እና ሌሎች የፌስቡክ ታጋዮች!
አንዷ ያገሬ ሴት ደጋግማ ስታወራኝ ነው አንዱን የፌስ ቡክ ዝነኛ ታጋይ ያወቅሁት። እንዴት እስካሁን እንዳላየሁት ገርሞኝ በስሙ ፈልጌ ገባሁ። ጊዜየን አላጠፋሁም። ዘጋሁት። ካሁን ቀደም እንዴት የፌስ ቡክ ገጼ ላይ እንደመጣ ሳላውቀው ገጭ ብሎ ባገኘው ከፍቼ አይቸው፣ ሰምቼው... ወዲያው ነበር የዘጋሁት። ያኔ ለመጀመሪያ ጊዜ ሳየው፣ ነብያችን ድንገት ተከስተውለት ኖሮ፣ አዲስ ሙስሊም (convert) ሆኖ ነው መሰለኝ፣ ጥቂት የማውቃቸው ሙስሊም የፌስ ቡክ ወዳጆቼ፣ ላይክ አድርገው “ኢንሻላህ! ሱብሃናሁ ወተዓላ...”፣ “... እንኳን ወደ እውነተኛው እምነት መጣህ ወንድማችን...” ... ወዘተ የሚሉ ጽሁፎች ገጹ ስር ተኮልኩለው አይቼ ሳምንት ሳይሞላኝ ነው ያቺው ያገሬ ሴት ስትነግረኝ እንደገና ፈልጌ የገባሁት። ላካንስ ሰውየው (ካሁን በኋላ “ሰውየው” ስል ይኸኑ ሰውየ ነው) ባንድ ሳምንት … [Read more...] about ዶ/ር ፍስሃ እሸቱ፣ ሄኖክ የሺጥላ እና ሌሎች የፌስቡክ ታጋዮች!
RECLAIMING AN ETHIOPIA FOR ALL ETHIOPIANS
It is time to reclaim Ethiopia for all of us. I, for one, will not stand by as the country we call home is tossed to and fro in the ethnic or sectarian battlefield of the ambitions and interests of a few vying groups. The competition— rather than cooperation—continues until whomever comes out on top takes over to dominate in a recycling of dysfunction that has been repeated again and again in Ethiopia. Once in power, that ethnic or sectarian group suddenly wants to claim leadership over the … [Read more...] about RECLAIMING AN ETHIOPIA FOR ALL ETHIOPIANS
“እንኳን በሳይበር የሚደረግ ጥቃት ይቅርና የወያኔ ተገንጣይ መንግስት እስር ቤትም ከዓላማችን አላሰናከለንም”
ዘ-ሐበሻ ድረገጽ ከተመሰረተች 9 ዓመት ሆኗታል:: ባለፉት 9 ዓመታት በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታዎችን መረጃ ከሚያቀብሉ የመረጃ መረቦች መካከል አንዷ በመሆን በአማራጭነት ሚድያነት አገልግላለች:: በየዕለቱ ድክመቶቻችን በማረም ከዘመኑ ቴክኖሎጂ ጋር በመራመድ አሁንም ተመራጭና ተአማኒ ሚዲያ ለመሆን ተግተን እየሰራን ነው:: እንደሚታወቀው የዘ-ሐበሻ አዘጋጆች የሚዲያን ሥራ የጀመሩት እዚህ ስደት ላይ ከወጡ በኋላ አይደለም:: በሃገር ቤት በኢትዮጵያ ነጻው ፕሬስ ውስጥ መስዋዕትነት የከፈሉ፣ የታሰሩ፣ የተገረፉና ብዙ መስዋዕትነት በከፈሉ ጋዜጠኞች የምትዘጋጅ ድረገጽ ናት:: ዘ-ሐበሻ ድረገጽ በተለይ ዕድሜያቸው ከ18 – 45 ዓመት ክልል ውስጥ በብዛት የምትጎበኝ፣ ወቅታዊ መረጃዎችንም በፍጥነት የምታደርስ መሆኗ የሕወሓትን መንግስት ሁሌም እንዳስደነገጠች ነው:: ባለፉት 9 ዓመታት በተለይ … [Read more...] about “እንኳን በሳይበር የሚደረግ ጥቃት ይቅርና የወያኔ ተገንጣይ መንግስት እስር ቤትም ከዓላማችን አላሰናከለንም”
የትግሉ ዋና ዓላማ ለስልጣኔ ወይንስ ስልጣንን ለመያዝ?
መግቢያ በአብዛኛዎቹ የሶስተኛው ዓለም ተብለው በሚጠሩ አገሮችና፣ በጠቅላላው የካፒታሊስት አገሮች ተብለው በሚታወቁትና የሳይንስና የቴክኖሎጂየበላይነትን በተጎናጸፉት አገሮች ያለውን ልዩነት ስንመለከት ልዩነቱ እጅግ ከመስፋቱ የተነሳ እንደዚህ ዐይነቱን የተወሳሰበ ህብረተስብ ለመገንባት የብዙ መቶ ዐመታት ስራ እንደሚያስፈልገን ይታየኛል። በአጠቃላይ ሲታይ የካፒታሊስት አገሮች ይህ ዐይነቱ የዕድገት ደረጃ ላይ ደርሰው ዓለምን መቆጣጠር ሲችሉ እኛን ምን ነካን ብለን የምንጠይቅ ብዙ ላንሆን እንችላለን። እንደሚታወቀው እንደዚህ ዐይነቱን ጥያቄ ሊያነሱ የሚችሉት ሰዎች በጣም የተወሰኑና የአንድን ህዝብ ዕድል ስልጣን ከመያዝ ባሻገር ሊያዩ የሚችሉ ሰዎች ብቻ እንደሆነ መገመት ይቻላል። ያም ሆነ ይህ የእነሱን የኢኮኖሚ፣ የፖለቲካና የሚሊታሪ የበላይነትና ዓለምን መቆጣጠር ጠጋ ብለን … [Read more...] about የትግሉ ዋና ዓላማ ለስልጣኔ ወይንስ ስልጣንን ለመያዝ?
A DECEMBER 13 “DAY OF REMEMBRANCE” FOR ALL ETHIOPIANS
Today is December 13, a day which will remind the Anuak of the painful loss of their loved ones in Gambella on the same date in 2003— thirteen years ago. It is a Day of Remembrance that is not easy for the Anuak, wherever they are in the world. It is a time that brings back memories of the horrific killing of 424 Anuak in less than three days. Destruction, pillaging and other egregious human rights abuses accompanied the slaughter of these precious lives. It signaled the beginning of a … [Read more...] about A DECEMBER 13 “DAY OF REMEMBRANCE” FOR ALL ETHIOPIANS
የእምዬ ምኒልክ ውለታ
ዛሬ ታህሳስ 3 ቀን 2009 ዓ.ም. ስመ ገናናው የኢትዮጵያ ንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ አፄ ምኒልክ ከዚህ አለም በስጋ ካለፉ 103 ዓመት ሲሆናቸው አባ መላ ኃብተጊዮርጊስ ዲነግዴ ደግሞ ዘጠና አመት ሆናቸው። ዳግማዊ አጤ ምኒልክና አባ መላ በስጋ ካለፉ ወደ አንድ ክፍለ ዘመን የሚጠጋ ዘመን ቢቆጠርም ስለታላቅነታቸውና ስለአሻራቸው ግን ዛሬም ገና አውርተን አልጠገብንም። በንጉሠ ነገሥት ዳግማዊ አጤ ምኒልክ ትዕዛዝ ወደ ኢትዮጵያ ከገቡ ለኢትዮጵያውያን አስፈላጊ የሆኑ የሳይንስና የቴክኖሎጂ ውጤቶች መካከል ባቡር [1893]፣ ስልክ [1882]፣ ፖስታ [1886]፣ ኤሌክትሪክ [1889]፣ አውቶሞቢል [1900]፣ ባህር ዛፍ [1886]፣ የውሃ ቧንቧ [1886]፣ ዘመናዊ ህክምና [1889]፣ ሆስፒታል [1890]፣ የመድሃኒት መሸጫ ሱቆች [1904]፣ ባንክ [1898]፣ ገንዘብ … [Read more...] about የእምዬ ምኒልክ ውለታ
ህወሃት “ተቃዋሚዎችን” በዓመት ሦስቴ ደጄን ከረገጣችሁ ይበቃችኋል አላቸው
በጥልቅ እየታደስኩ ነው የሚለው ህወሃት/ኢህአዴግ በየቀኑ በጥልቅ መበስበሱን እና ለመታደስ ፈጽሞ የማይችል መሆኑን የሚመለክቱ ተግባራትን ሲፈጽም እየታየ ነው፡፡ የትግራይ ተወላጆችን ወደኋላ በማድረግ ከመድረኩ በማውጣት የፊት ገጾች እንዲሆኑ ከትግራ ውጭ ያሉ ግለሰቦችን በማስቀመጥ ሥራውን በምክትሎቻቸው የትግራይ ተወላጆች እንዲሠራ እደረገ ነው፡፡ የፖለቲካ ምህዳሩን አሰፋለሁ፣ አሳታፊ እሆናለሁ፣ … እያለ የፖለቲካ አመራሮችን፣ ጋዜጠኞችን፣ የተቃዋሚ ኃይላትን ያስራል፤ ሕዝቡን ያሰቃያል፣ ይገድላል፡፡ አዲስ አድማስ ተቃዋሚ ፓርቲዎች በዓመት ሦስት ጊዜ ፓርላማ ገብተው በውይይት እንዲሳተፉ ለማድረግ ማኑዋል እየተዘጋጀ መሆኑን በመጥቀስ “ተቃዋሚዎች፤ ሳንመረጥ ፓርላማ አንገባም አሉ” በሚል ርዕስ የዘገበው እንዲህ ይነበባል፤ መንግስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች በዓመት ሦስት ጊዜ ፓርላማ ገብተው … [Read more...] about ህወሃት “ተቃዋሚዎችን” በዓመት ሦስቴ ደጄን ከረገጣችሁ ይበቃችኋል አላቸው
ዛዲግ አብርሃ – የነገሪ ሌንጮ “ምክትል”?
አምልኮተ መለስ የተጠናወተውና የህወሃት አባል የሆነው ዛዲግ አብርሃ "የጥልቅ ተሃድሶ" ውጤት ተብሎ የተመደበው የነገሪ ሌንጮ ምክትል ሆኖ በሃይለማርያም ደሳለኝ መሾሙን Ethiopia Observer ዘግቦታል። ኦሮሞው ሌንጮ በአፈቀላጤነት በየሚዲያው ፊቱን ሲያስመታ የድርጅት ሥራውን የሚያከናውነው መለስን ማንነቴ ነው መንፈሴን ይቀሰቅሰዋል የሚለው ህወሃቱ ዛዲግ ይሆናል። ከዚህ በፊት ስለ መለስ የተናገረውን እዚህ ላይ ማንበብ ይቻላል። "ጥልቅ ተሃድሶ" በጥልቅ መበስበስ ይቀጥላል! ጎልጉል … [Read more...] about ዛዲግ አብርሃ – የነገሪ ሌንጮ “ምክትል”?
የጣና በለስ ታሪካዊ የልማት ፕሮጀክት፤ ከመፈራረስና ውድመት እስከ መሸጥ
የጣና በለስ ፕሮጀክት አጭር ታሪክ የጣና በለስ ፕሮጀክት ልማታዊ ግቦች/ህልሞች ምን ነበሩ? የጣና በለስ ፕሮጀክት በአፄው ስርዓት ተጠንስሶ፥ በደርግ አብቦ፥ በህወሀት/ኢህአዴግ እንዴትና ለምን ፈራረሰ? ዛሬ በጣና በለስ ላይ የተጋረጠው አዲስ እና አስደንጋጭ አደጋስ ምንድን ነው? መፍትሄውስ? መግቢያ የአባይ ተፋሰስ ኢትዮጵያ ውስጥ ካሉት ተፋሰሶች የላቀ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ፋይዳ ያለው ልዩ ቦታ በመሆኑ በርካታ ጥናቶች ተደርገውበታል። የመጀመርያው የአባይና ጣና ዳሰሳ ጥናት የተካሄደው በእንግሊዞች ነበር። ቀጣዩ ዝርዝርና ጥልቅ ጥናት የተካሄደው በአጼ ኃይለሥላሴ ልዩ ጥያቄ ሲሆን ምክንያቱም አወዛጋቢው የእንግሊዝና ጣልያን በ1925 ዓ.ም የተፈራረሙት ውል ነበር። ይህ የወራሪ ሃይሎች ውል ጣልያን ኤርትራ የሚገኘውን ቅኝ ግዛቷንና ሶማሌ ያለውን ቅኝ … [Read more...] about የጣና በለስ ታሪካዊ የልማት ፕሮጀክት፤ ከመፈራረስና ውድመት እስከ መሸጥ










