ፊቱ አሸቦ መስሎ፣ እንደደነገጠ፣ ተጎልጉሎ ወጥቶ፣ ዓይኑ እንደፈጠጠ፣ ባንኮኒው ጋ ሄዶ፣ ቢራውን ጨበጠ። የሆነውን እንጃ! ሁኔታው ያስፈራል፣ እንባው በጉንጩ ላይ፣ አቋርጦ ይፈሳል አልቅሶ ሲበቃው፣ ውጪ እየሰለለ፤ ያየውን በውስጡ፣ እያሰላሰለ፣ ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ። ወደ ተናጋሪው፣ አፍጠን እያየን፤ እንደልማዳችን፣ ዝም ተባባልን። ሰውዬው ቀጠለ፣ ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ! ዘለው ያልጠገቡ፣ እህል የተራቡ፣ አገር የተቀሙ፣ ፍትሕ የተጠሙ፣ አንድ ፍሬ ናቸው! ገና እንዳገኟቸው፣ ከበው ይዘዋቸው፣ መሣሪያ አስጠግተው፣ ወደ ግንባራቸው፣ ጭንቅላታቸውን ... ፈረካከሷቸው። እያለ ሲናገር፣ ሰውዬው ሲቆጣ፣ ሲያለቅስ ሲያማርር፣ እኔም ልክ እንደሱው፣ በዓይኖቹ ገብቼ፣ አንገቴን አቅፌ፣ በሁለት እጆቼ፣ ጉልበቴ እየራደ፣ ነፍሴ … [Read more...] about የዛ ሰውዬ ድምጽ . . .
ለጀግናው አትሌት ስንብት!
. . . በዚያ ቀውጢ ጊዜ - በዚያ ቀውጢ ዘመን፣ ከአገር በራቀበት - የደስታ ሰመመን፤ ያገር ፍቅር ስሜት - መገለጫ ፈርጦች፣ ብቸኛው አማራጭ - የደስታችን ምንጮች፣ ነበሩን! ነበሩ! “አረንጓዴ ጎርፎች”. . .፤ እንዲህ እንደዛሬው - ሳይዘምን ዘመኑ፣ ያለም መገናኛ - ሳይራቀቅ ኪኑ፣ ዩ ቲዩብ፣ ኢንተርኔት፣ ስማርት ፎን..ሳይኖር፣ ዜና መቀበያው - ራድዮናችን ነበር፤ “. . . ክቡራትና ክቡራን ውድ አድማጮቻችን..”፣ የኦሎምፒክ ውጤት፣ ልክ እንደደረሰን፣ እናስደምጣለን...”፤ በለሆሳስ ሙዚቃ መሳሪያ ቅንብር መሻገሪያ ዜማ፣ ከተራራ ጫፍ ላይ፣ ወይ ከሰማየ-ሰማያት ከሩቅ እሚሰማ፣ “የኛ ነው ድሉ-ድሉ፣ የኛ ነው ድሉ-ድሉ፣ በርቱና ታገሉ..”፤ አገር ትንፋሽ አጥሮት - ጸጥ-ረጭ ብሎ፣ ዐይኖቹን ጎልጉሎ - ራድዮን ላይ … [Read more...] about ለጀግናው አትሌት ስንብት!
በማወቅና በማድረግ እውነትን መኖር?
የሕይወትን እውነትና ትክክለኛ ትርጉም ተረድተን በሰላምና በፍቅር ለመኖር የሚያስችል የአእምሮ መታደስ ለማድረግ የሚከተለውን ላካፍላችሁ፡ ከሁሉ አስቀድሜ ልረሳው የማልችለውን መልካም ባህላችንን ተጠቅሜ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሰን እላለሁ፤ እኔም ከሃገር፣ ከቤተሰብ፣ ከዘመድና ከጓደኛ ተለይቼ ባህሉንና ወጉን ጠንቅቄ ከማላውቀው ሕዝብ ጋር በእኛ አቆጣጠር ባለፈው ታሕሳስ 16 ቀን 2009 ዓ/ም የፈረንጆችን የገና በአል አክብሬ አሁን ደግሞ የእኛን ታሕሳስ 29 ቀን 2009 ላይ ከኢትዮጵያውያንና ከኤርትራውያን ወገኖቼ ጋር ለማክበር በዝግጅት ላይ ነኝ፤ እዚህ ላይ የቀን ልዩነት ቢኖርም የመከበሩ ዋና ዓላማና የቀኑ ባለቤት የሆነው ግን አንድ ነው፤ እሱም ከድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው በመሆን በሰው ልጆች መካከል በመመላለስ “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” ለማለት ድፍረት እንዲሆነን “አማኑኤል” … [Read more...] about በማወቅና በማድረግ እውነትን መኖር?
The TPLF Hired a Rubbish Writer to Defend it against Prof. Al Mariam
With an open mind, I read an article titled “TEACHING ALMARIAIM HOW TO WRITE” on the Aiga Forum website, the Tigrayan People’s Liberation Front’s (TPLF’s) mouthpiece. The article was written by Yenieta A, who claimed that Ethiopian political writers don’t know how to write. To make his point, he used Professor Al Mariam’s commentary titled “Ethiopia: Cry! Cry Freedom the Beloved Country!” as his example because he thinks Al Mariam is the worst kind of political writer. To help him to improve … [Read more...] about The TPLF Hired a Rubbish Writer to Defend it against Prof. Al Mariam
የምሥራች ነፃነት ላጣው
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን «እስመ ናሁ እዜንወክሙ ዐቢየ ዜና ፍሥሓ…» « ትልቅ የምሥራች ዜናን እነግራችኋለሁ..»ሉቃ ፪፦፲-፲፬፤ ነገር ከሥሩ ውኃ ከጥሩ እንዲሉ የምሥራች ህገ ወንጌልን ለመታወጅ ያበቃውን ስንመረምር ፤ እግዚአብሔር አምላክ በጥንተ ፍጥረት የሰውን ልጅ ወደዚህ ምድር ፈጥሮ እንዲያስተዳድረው ከማድርጉ አስቀድሞ፤የሚተዳድርበትን የሥነ ፍጥረት ህግ አዘጋጀለት፤ ሥጋዊ አካሉ እንዳይዝል የሚያርፍበት ሌሊት ተሐድሶ የሚነሣበት መዓልትን ሰጠው፤ በጨረሯ ሙቀትን በነጸብራቋ ብርሃንን፤ በክበቧ ደስታን የምታጎናጽፈውን የሥሉስ ቅዱስ ተምሳሌት የሆነችውን ጨለማን የምታስወግደውን ፀሐይን አደለው። በልቶ የሚያረካውን ምግበ ሥጋን ሰጠው፤ በጥላው የሚጠለልብትን አበቦችን ዓይቶ በመንፈሱ የሚረካበትን ዕፀዋትን፤ አትክልትና አዝርዕትን የየብስ መደሰቻ መዝናኛውን … [Read more...] about የምሥራች ነፃነት ላጣው
“ሐሩርም ይሁን በረዶ እኔ ከማሸነፍ የሚገታኝ አንዳች ኃይል የለም” – “Yifter the Shifter”!
ከሠላሳ ሰባት ዓመት በፊት የተካሄደው የሞስኮ ኦሊምፒክ ሲነሣ ቀድሞ የሚመጣው የሚወሳው ረዥም ርቀት ሯጩ ምሩፅ ይፍጠር ነው፡፡ የድል ቁርጠኝነት የተሞላበት አሯሯጡ የመላው ዓለምን ምናብ ሰንጎ መያዙ አይረሳም፡፡ በሞስኮ ኦሊምፒክ በሁለቱ ርቀቶች በ5,000 ሜተርና በ10,000 ሜትር ለተቀናቃኞቹ ዕድል ሳይሰጥ ተፈትልኮ የሮጠበትና ያሸነፈበት መንገድ ‹‹ይፍጠር ዘ ሺፍተር›› (ማርሽ ለዋጩ ምሩፅ - አካለ ማርሹ ምሩፅ) የተባለበትን ዳግም ያረጋገጠበት ነበር፡፡ በሞስኮ ድሉ ከተመሰጡና አርአያ ከሆነላቸው መካከል በወቅቱ የሰባት ዓመት ልጅ የነበረው ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ውድድሩን በትራንዚተር ሬዲዮ ጆሮውን ደቅኖ ሲከታተል አንድ ቀን የርሱን ዱካ እንደሚከተል አልሞ ነበር፡፡ ኢትዮጵያን የኦሊምፒክ ብርሃን ከዘጠና ሦስት ዓመት በፊት የዳሰሰው በፓሪስ ኦሊምፒክ አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኰንንና የክብር … [Read more...] about “ሐሩርም ይሁን በረዶ እኔ ከማሸነፍ የሚገታኝ አንዳች ኃይል የለም” – “Yifter the Shifter”!
“ኢትዮጵያን አፈራርሰን ኦሮሚያን እንገነጥላለን”
“ሀገር አጥፊው አረም በሀገሬ ሲስፋፋ፣ ሁሉም ተዳከመ የሚያርመው ጠፋ፣ የጊዜ ጉዳይ ነው እኔ አለቆርጥም ተስፋ፣ ሀገሬ ነው የሚል ኢትዮጵያዊ ሁሉ፣ ጥቃቱ ይሰማው ሲቆረስ አካሉ።” ከሊቀ ማዕመራን አበባው ይግዛው “ወይ ሀገሬ” ከሚለው ግጥም የተወሰደ። የአውሮፓ ቅኝ ገዥዎች አፍሪካን እንደ ቅርጫ ሥጋ ለመቀራመት በተነሱበት ወቅት በተለያዩ ሀገሮች እገራቸውን ያስገቡት በሀይማኖት አስተማሪነት ሰም የቄስ ካባ አልብሰው የመረጃ (ሰላይ) ሰዎቻቸውን በመላክ ነው። ማርቲን ሉተር የተባለው የተባለው የጀርመን የሀይማኖት ሊቅ እ.ኢ.አ. በ1517 የካቶሊክ ሃይማኖት መሻሻል አለበት በሚል ያቀረበው ፅንሰ ሃሳብ ተቀባይነት አግኝቶ ዛሬ ሉተራን የሚባል የፕሮቴስታንት ሃይማኖት ዋናው ቅርንጫፍ እንዲፈጠር አድርጓል። እዚህ ላይ የሉተራን ቤተ ክርስቲያን፣ የጀርመንና የኦሮሞ የሉተራን ቤተክርስቲያን … [Read more...] about “ኢትዮጵያን አፈራርሰን ኦሮሚያን እንገነጥላለን”
ለማንነታችን መከታ ያልሆነን፣ ለመጠቃታችን ምክንያት እየሆነ ነው!
ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር ዘረኛው የትግሬ ወያኔ አገዛዝ በሕዝባችን ላይ፣ በተለይም በዐማራው ነገድ ላይ የሚፈጽመው የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በ«አርበኞች ግንቦት 7» እያመካኘ ነው። ለዚህም ምክንያት የሆነው አርበኞች ግንቦት ሰባት፣ በሚቆጣጠረው የብዙኃን መገናኛ ያላደረገውን አደረኩ፣ ያላዘመተውን ወታደር አዘመትኩ፣ «የክተት አዋጁ ፊሽካ ተነፋ»፣ በሁሉም ሕዝባዊ እንቢተኝነት እንቅስቃሴዎች እኔ አለሁበት፣ የምመራው እኔ ነኝ፣ የሚለው ወሬ ቀድሞ መነዛቱ ነው። ወሬው በትንሽ ተግባር ቢደገፍ ኖሮ ባልከፋ። ክፋቱ ምንም ዓይነት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሳይጀምር፣ ኤርትራ በረሃ ከትሟል የሚባለው ፋኖ፣ የተከዜን ወንዝ ሳይሻገር፣ የወያኔ አገዛዝ አንገሽግሾት ባመቸውና በመሰለው መንገድ ጥይት የተኮሰውን ሁሉ የእኔ ነው ማለቱ፣ «ለወያኔ ሊበሏት ያሰቧትን … [Read more...] about ለማንነታችን መከታ ያልሆነን፣ ለመጠቃታችን ምክንያት እየሆነ ነው!
በኢንተርኔት መቋረጥ 9 ሚሊዮን ዶላር፣ በሞባይል ኢንተርኔት ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር ኪሣራ!
ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጅና ከዚያ በፊት በነበረው ሁኔታ የኢንተርኔት መቆራረጥና መታገድ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት ማድረሱ የተጠቀሰ ሲሆን ባለፈው አንድ ዓመት አገሪቱን 9 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማሣጣቱን የአሜሪካው ብሩኪንግስ ኢንስቲቲዩት ይፋ ያደረገው ጥናት አመልክቷል። ዴልዮት የተባለው ዓለማቀፍ አማካሪ ተቋም በበኩሉ፤ የሞባይል ኢንተርኔት መዘጋት ሀገሪቱን በቀን 5 መቶ ሺህ ዶላር እያሳጣት ነው ብሏል። በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ተቃውሞና ግጭቶች መከሰታቸውን ተከትሎ የኢንተርኔት አገልግሎቶች መቆራረጥ፣ ሃገሪቱን በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ አሳጥቷል ብሏል - ዴልዮት። የኢንተርኔት አገልግሎት መቃወስ የኢኮኖሚ እድገቱን እንዲቀዛቀዝ አድርጓል ያለው "አፍሪካን ቢዝነስ"፤ ፈጠራዎች እንዳይበረታቱ፣ የገቢ ታክሶች በአግባቡ እንዳይሰበሰቡና ነጋዴዎች … [Read more...] about በኢንተርኔት መቋረጥ 9 ሚሊዮን ዶላር፣ በሞባይል ኢንተርኔት ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር ኪሣራ!
ሚዲያ አለኝ ተብሎ የሰው ስብዕና ላይ ክተት አይታወጅም
ሚዲያ እንደ ሰዎች አረዳድ የሚሰጠው ደረጃና አቅም የተለያየ ቢሆንም ያለ አንዳች ማመንታት “ኃይል” ወይም ኃይል ያላቸው መገልገያ መሆኑ ጥርጥር የለውም። ሁሉም ሚዲያ “የሕዝብ” መሆናቸውን ቢገልጹም ፍጹም ነጻና ገለልተኛ ሆነው አይታዩም። ወደ አገራችን ሚዲያ ስንመጣ በውጭ ያሉትም ሆኑ በአገር ቤት፣ የግል የሚባሉትም ሆነ የመንግሥት የራሳቸው ወገንተኛነትና መንሸዋረር ይታይባቸዋል። ይህ እውነት ባደጉት አገሮችም ቢሆን ረቀቅ ባለ መልኩ የሚዘወተር ነው። ከሁሉም የሚቀፈው ግን ፍጹም ጭፍንነት ነው። ምክንያቱም በጭፍንነት ውስጥ አንድ ሰው ከተነገረውና ከተሞላው በቀር አሻግሮ ማየት አይችልምና ነው። “መቃብር ቆፋሪው እና የሬሳ ሳጥን ሻጩ የሚለው ተውኔት የተሰረቀ ነው” የማለት አዝማሚያ በሚስተዋልበት ስሜት የተጀመረ ቃለ ምልልስ። ሲጠናቀቅም የተለያዩ ጉዳዮች ውስጥ ትገባለህ “የባከንክ ነህ” … [Read more...] about ሚዲያ አለኝ ተብሎ የሰው ስብዕና ላይ ክተት አይታወጅም










