የዚህች ጦማር ዋና ዓላማ፡ “ያዲስ አበባው ሲኖዶስ የግብጽ ቤተ ክርስቲያን ከቀሩት አኀት አብያተ ክርስቲያናት ተነጥላ ከሀያ በላይ ስህተት ሰርታለችና ትመርመር የሚል ክስና ወቀሳ አቀረበ” ብሎ ሀራ ዘተዋህዶ ባቀረበው ዜና፤ ግራ የተጋባችሁ ክርስቲያኖች፤ “በአኀት አብያተ ክርስቲያናት ሐዋርያዊ ትውፊት አንጻር እንዴት ትመለከተዋለህ“ ብላችሁ ላቀረባችሁልኝ ጥያቄ ለመመለስ ነው። ይህ የቀረበው ሀሳብ የሀራ ዘተዋህዶ ድረ ገጽ ፈጠራ ከሆነ፡ ”አባት ሆ ይ!እኔ በአንተ አንተ በእኔ እንዳለህ እነርሱም በእኛ አንድ ይሆኑ ዘንድ”(ዮሐ 17፡ 21“)በሚለው ክርስቶሳዊ ቃል፤ አንድነታቸውን አጽንተው በኖሩት በአኀት አብያተ ክርስቲያናት ላይ እየዘመተ ነው ማለት ይቻላል። ምናልባትም ከጥንት ጀምሮ እነዚህን ጥንታውያት አብያተ ክርስቲያናትን ለማጥፋት የሚታገሉት የሰባልዮስ ወይም የአርዮስ ተከታዮች ሊሆን … [Read more...] about አሣ ጎርጓሪ ዘንዶ አወጣ
አስናቀ እንግዳ ይድረስህ ምስጋና
አስናቀ እንግዳ ገና ከጠዋቱ፡ ጎህ እንደቀደደ፡ ገና በማለዳ ከቆላ ከደጋ ተሸክሞ ዕዳ ከደቡብ ከሰሜን ከምዕራብ ከምሥራቅ ዘልቆ በመደዳ ለሀገሩ ለቀዬው ሰው እንዳይሆን ባዳ አበው ያወረሱት ታሪክ እንዳይጠፋ መላውን ዕድሜውን ያለ ቀና ደፋ ሀሰትን ኮንኖ፡ ሀቅን ይሚያፋፋ ምዝበራን ተጋፍጦ፡ ለሕዝብ የተዋጋ አልገዛም ያለ ላምባገነን መንጋ ሕይወቱን አስተምሮ፡ ሕይወትን የኖረ ንዋይ፡ ሀብት፡ ዝና ከቶ ያላፈቀረ የዕድሜ ባለጸጋው ጀግናው የእንግዳ ልጅ ይድረስህ ምስጋና ከዚህ ካሲምባ ደጅ ከዘመድ ከወዳጅ። ያገር ፍቅር ስሜት ውስጡን እየበላው የወገኑ ብሶት እያብከነከነው የሰንደቁ ክብር እያንገበገበው ኢትዮጵያ ታሪኳ ተከብሮ እንዲኖር አንድነቷ ጸንቶ እንዲሆነን ማገር ሉዓላዊነቷ ጸንቶ እስከዘላለም የሕዝቧ አንድነት እንዲኖር እስካለም ታግሎ ያታገለ፡ መካሪ … [Read more...] about አስናቀ እንግዳ ይድረስህ ምስጋና
የሻለቃ ዳዊት የዋሽንግተን ሲያትል ንግግር በሞረሽ ዕይታ!
ሰዎች መልካም ሢሠሩና ሲናገሩ ማመስገን፣ መጥፎ ሢሠሩና ሲናገሩ ደግሞ መምከርና መገሰጥ ተገቢ ነው። ምንጊዜም ሁሉም ሰው ሕይዎቱን ሙሉ ስሕተት ብቻ እየሠራ አይኖርም። መልካም ነገሮችም ይሠራል። ልዩነት የሚኖረው የትኛው ሥራው ነው የሚያመዝነው? መልካሙ ወይስ መጥፎ የሚለውን መመዘኑ ላይ ነው። በዚህ ረገድ የሻለቃ ዳዊትን ሥራዎች መዝኖ፤ የማሞገሱም ሆነ የመውቀሱ ተግባር፣ እርሳቸውን የሚያውቁ፣ አብረዋቸው የሠሩ፣ የትaምህርትና የሥራ ባልደረቦቻቸው ተግባር ይሆናል። ሞረሽ ወገኔ ዐማራ ድርጅት ለዐማራ ነገድ ድምፅ ለመሆን የበኩሉን ድርሻ በመወጣት ላይ ያለ ድርጅት ነው። ስለዚህ ሻለቃውን በዚህ ንግግራቸው፣ ላለፉት 5 ዓመታት ሲጮኽባቸው የነበሩ አንኳር ጉዳዮችን እያነሱ፣ ዐማራውን ሲያወግዙ፣ በጠላትነት ፈርጀው የዘር ፍጅት በፈጸሙ ግለሰቦችና ስብስቦች ፊት በኩራት ቆመው በመናገራቸው ከልብ … [Read more...] about የሻለቃ ዳዊት የዋሽንግተን ሲያትል ንግግር በሞረሽ ዕይታ!
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! “ክፋት” – በሁሉም መስክ!!
መርዛማ ፍሬ 11፡ የታሪክ መቃብር! በስሜት በሚነዳ የዘውግ ፖለቲካ ውስጥ ታሪክ ትልቅ ማገዶ ሆኖ ቀርቧል። የኢትዮጵያ ታሪክ አካታችነት ባለው መልኩ በአጎልባች ሚና (ብሔራዊ ተዋፅዖ) መፃፍ እየተገባው ምክንያታዊነትን አስመንኖ የልዩነት ሃረጎችን ብቻ በመምዘዝ በየአቅጣጫው የሚፃፍ መሆኑ ከተካረረ ሙግት ሊፀዳ አልቻለም። መዋቅራዊ ድጋፍ ባለው መልኩ የታሪክ ሙግቱ እየተካረረ በመምጣቱ ብሔራዊ ርዕይ ርቆን የመንደር አጥር እስከመስራት ደርሰናል። ደርግ በየትኛውም ያህል መጠን አምባገነንና ጨፍጫፊ ሆኖ ቢገኝም የኢትዮጵያን ታሪክ ሲንቅና ሲያንቋሽሽ አልተገኘም። ከቶውንም ለብሔራዊ ርዕይ መፍጠሪያነት እንደግብዓት ተጠቅሞበታል። ከመነሻው ጀምሮ ኢትዮጵያዊ ስሜትን (የጋራ ማንነትን) በመካድ ራሱን ብቸኛ የትግራይ ህዝብ ነፃ አውጭ ግንባር አድርጎ የሰየመው ህወሓት፣ የአገሪቱን የረዥም ጊዜ ታሪክ … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች! “ክፋት” – በሁሉም መስክ!!
አንድነት ከማን ጋር? አንድነት ለምን? አንድነት መቼ?
ዐማራው በባህሉ፣ በሥነ-ልቦናውና በፖለቲካ ታሪኩ እንዲሁም በሚጋራቸው የወል ዕሴቶቹ፣ በእሱነቱና በኢትዮጵያዊነቱ መካከል የተሰመረ ልዩነት ባለመኖሩ፣በዘር ጠላትነት ተፈርጆ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ሲፈጸምበት ፣ወንጀሉ በሁሉም ኢትዮጵያዊ ላይ የሚፈጸም ነው በማለት፣ለምን? እንዴት? ብሎ ለመጠየቅ ከሁለት ዓሥርተ ዓመታት በላይ እንደፈጀበት በግልጽ ይታወቃል። ይህም ዘረኛው የትግሬ ወያኔ ቡድንና አጋሮቹ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ዐማሮች ከምድረ ኢትዮጵያ እንዲጠፉ ሠፊ ዕድልና አጋጣሚ እንዲያገኙ ረድቷቸዋል። ይህን ያህል ቁጥር ያለው ከትግሬ፣ ከሶማሌ፣ ከጉራጌ፣ ከሲዳማ፣ ከወላይታ ቢጠፋ ሁሉም የነገዱ አባሎች ጠፉ ማለት ነበር። ዐማራው ይኸን ያህል ቁጥር የሰው ኃይል ጠፍቶበት፣ ምንም ያልመሰለው ከጣና ሐይቅ በጭልፋ ውኃ የመቀነስ ያህል ሆኖ በመታየቱ፣ የሁሉንም የዐማራውን ነገድ ጆሮ … [Read more...] about አንድነት ከማን ጋር? አንድነት ለምን? አንድነት መቼ?
የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?
አቶ አሰፋ ጫቦ ከአርባ ዓመታት በላይ ከዘለለው የኢትዮጵያ የፖለቲካ ጉዳይ ውስጥ ጎልተው የታዩ ሰው ነበሩ። እንዲሁም ሊጽፏቸው የፈለጓቸውን ነገሮች የራሳቸው በሆነ የአፃፃፍ ስልት የሚያቀርቡ፣ ስለነበሩ በዚሁ ሥራቸው በብዙዎች ዘንድ ሞገስና ውዳሴ አትርፈዋል። በቅርቡም የትዝታ ፈለግ የሚባል መጽሐፍ አሳትመው ሕዝብ እንዲያነበው አድርገዋል። የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በአቶ አሰፋ የፖለቲካ ሕይወት ወይም ስነጽሁፋቸውን ለመቃኘት ሳይሆን የአሟታቸውን ሁኔታ በተመለከተ ቬሮኒካ መላኩ ባቀረቡት ጽሑፍ ላይ ተመርኩዞ የተነሳ ነው። ቬሮኒካ መላኩ በጽሑፋቸው አቶ አሰፋ ከመሞታቸው በፊት በነበሩ ቀናት ውስጥ በጥሩ ጤንነት ላይ ይገኙ እንደነበር በመገልጽ ለቦርከና ድረገጽ ባለቤት ወደ ደረሰው መልዕክት ይንደረደራሉ። በመልዕክቱም ግሪጎሪ ማኬንዚ የተባሉ ሰው አቶ አሰፋን እንደሚያውቁ ሁለቱም ዓለም በቃኝ እስር … [Read more...] about የአቶ አሰፋ ጫቦ ሞት ጉዳይ ምን ደረሰ?
አውቀን እንታረም
ደራሲ፤ አቢይ አበበ (ሌ/ጄኔራል) ቅኝት፤ መስፍን ማሞ ተሰማ ዓለም ገና ልጅ ናት አውራጃዋም ደግሞ አርጅቶ የሚሞተው ሰው ብቻ ነው ቀድሞ ብዙ አሳልፋለች ብዙዎች ተክታ የሁሉንም ምግባር በየተራው አይታ። ሌ/ጄ አቢይ አበበ እንዲህ ሆነ፤ ርዕሱን አነበብኩና ደራሲውን ስመለከት ሌተናንት ጄኔራል ይላል። የህትመት ዘመኑ ደግሞ 1955 ዓ/ም። ባለሁበት ዘመን ውስጥ ሆኜ ሳሰላው እንግዲህ መፅሀፉ ከታተመ ግማሽ ምዕተ ዓመት አልፎታል። ህትመቱስ? አስቀድሞ አሥመራ በ”ኢል ፖሊግራፊኮ ሶ. አ” ማተሚያ ቤት የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ክፍለ ሃገር ኤርትራ ዋና ከተማ ሲሆን እርግጥ ከ12 ዓመት በሁዋላ በ1967 ዓ/ም (ዘመነ ፅልመት) አዲስ አበባ በቼምበር ማተሚያ ቤት በድጋሚ ታትሟል። ስለምን ዘመነ ፅልመት አልነው 1967 ዓመተ ምህረትን? አንባቢ ቅኝቱን አስጀምሮ ካስጨረሰህ ምላሹን … [Read more...] about አውቀን እንታረም
ሁለት የኢትዮጵያ ሴት ሯጭ ስፖርተኞች በኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ያሳዩት ጋጠወጥ ባሕሪና ፖለቲካዊ ምርጫ!
ይህ ትችት የኔን ጽሑፍ በሚያስተናግዱ እንደሚለጠፍ ባውቅም፤ ለሌሎቹ ተቃዋሚ ድረገፆች በሙሉ ተልኳል። ቢያወጡት አስተማሪ ነው። ብዙዎቹ ግን እንደማያውጡት ጥርጣሬ አለኝ። ምክንያቱም የፖለቲካ መሪዎቻቸውና ድርጅቶቻቸውን ጨምሮ በዚህ ትችት ስለተካተቱ ወገንተኛነታቸው ከሉጓም በበለጠ ይስባቸዋል። ለማንኛወም ለታሪክ ልኬአለሁ። አሁን ወደ ርዕሱ ልግባ። በትግርኛ በምንመስለው ምሳሌ ልጀምር፡ {ዝፀገባ ደራሁስ ምስ ፀኻድም ማሕበር ይኣትዋ} “የጠገቡ ዶሮዎች ከጭልፊቶች ጋር ማሕበር ይገባሉ” ይባላል። ሁለቱ ዓለም አቀፍ የሴቶች እውቅ ሯጮች ከጭልፊቶች ጋር ማሕበር መግባቱ ምርጫቸው አድርገው ይሆናል። የጭልፊቶቹ እና የዶሮዎቹ ማሕበር የሚቆየው ዕድሜ አብረን የምናየው ይሆናል። ሰሞኑን በአጋጣሚ “ዩቱብ” ድረገጽ ላይ አንድ ማሕደር ለመፈተሽ ጎራ ስል ድንገት ያላሰብኩበትን እና አስደንጋጭ … [Read more...] about ሁለት የኢትዮጵያ ሴት ሯጭ ስፖርተኞች በኢትዮጵያ ሰንደቅዓላማ ያሳዩት ጋጠወጥ ባሕሪና ፖለቲካዊ ምርጫ!
Many into one Africa, one into many Africans
“I know no national boundary where the African is concerned. The whole world is my province until Africa is free.” - Marcus. M. Garvey. The expression of many identities is seen as the celebration of diversity and a legitimate vehicle for claims to political and other forms of rights. The resolution of diverse identities into compound /combined identities and unities is often suspect bearing the implication that rights and diversity might be sacrificed in the process of bringing about a new … [Read more...] about Many into one Africa, one into many Africans
የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች — የአንድ ጎጥ የበላይነትና የመበታተን አደጋ!
ራሳቸውን “የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር” ብሎ በመሰየም የትግራይን ሕዝብ ሽፋን በማድረግ፤ “የምታገለው ለአንተ ነጻነት ነው” በማለት፤ መልሶ እታገልለታለሁ ያለውን ሕዝብ ያስጨፈጨፈው፣ ያስራበው፣ የግፈ ሰለባ ያስደረገው፣ … ራሱን ህወሓት እያለ የሚጠራው የወንበዴዎች ቡድን የኢትዮጵያን የሥልጣን መንበር ከተቆናጠጠ በኋላ የትግራይ ሰዎችን በሌላው ኢትዮጵያዊ ለማስጠላትና “ስም ለማሰጠት” እንዲሁም ለማጠልሸት ባለፉት 26ዓመታት ሲሰራ ቆይቷል። እነዚህ በኮ/ሎ ጎሹ ወልዴ አነጋገር “የሰከረ ርዕዮትዓለም የሚከተሉ፣ በብሄርና በጎሳ ፖለቲካ ላይ የተተከሉ ጠባብ ቡድኖች፣ በስታሊናዊ መርህ የተጠመቁ፣ እንኳንስ 50 ሚሊዮን ህዝብ ያላት አገር ቤተሰብን የመምራትና የማስተዳደር ተሞክሮ የሌላቸው፣ …” የኢትዮጵያን ሃብት እየዘረፉ በትግራይ ኢንቨስት በማድረግ፣ የትግራይ ተወላጆችን የተለያዩ … [Read more...] about የ“ግንቦት 20” ሃያ መርዛማ ፍሬዎች — የአንድ ጎጥ የበላይነትና የመበታተን አደጋ!










