የፖለቲካ ስርአትና የአንድ ሀገር እድገት ቀጥተኛ የሆነ ግንኙነት አላቸዉ። አንድ አገር ትክክለኛ ባልሆነ የፖለቲካ አገዛዝ ይበለፅጋል ብሎ ማሰብ የዋህነት ነው። ሃገራችን ኢትዮጵያም የወያኔ መንግስት ባነገሰው የተዛባ አገዛዝ ሳቢያ ህዝባችን ለከፋ ችግር መዳረጉ በገሃድ የሚታይ ሃቅ ነው። ታዲያ በዚህ ወያኔያዊ የተዛባ አገዛዝ እንዴት ከችግር ልንወጣ እንችላለን? አገራችን ኢትዮጵያ ምንም እንኳ የጥንት ስልጣኔ ባለቤት ብትሆንም በአየር ንብረትም ሆነ በተፈጥሮ ሀብት ጥሩ ከሚባሉት ሀገሮች አንዷ ብትሆንም እንደ እድል ሆኖ መሪዎች ግን አልተሳኩላትም። ለምን ኢትዮጵያ የረሃብ አገር ተባለች ለምን ዜጎቿ ተደስተው በነጻነት መኖርን እንደተመኙ ህልማችዉ ከንቱ ሆነ? ብዙዎች የሞቱላት አገር አንገታቸዉ ለሰይፍ ደረታቸዉ ለጥይት የሰጡላት አገር ኢትዮጵያ በህዝቦቿ ታታሪነት አለም ያደነቃት ለምን … [Read more...] about ህዝብን በመጨቆን ሀገርን መምራት አይቻልም!
ዝምታው በዛ
አገር ሲቆረስ ድንበሩ ሲፈርስ ማንነት ታሪክ ሲሻር መሬት ሲገመስ አገር ያለ ባህር በር ስትቀር ዜጋ ማንነት በጎሳ ሲቀየር ድንበር ተቆርሶ ለባድ ሲለገስ ወገን ሲጨቆን መኖሪያ ቤቱ ሲፈርስ ሀብት ንብረቱ ተዘርፎ ከቀየው ቦታው ሲሰደድ ዜግነት ክብሩ ሲጣስ ሰብአናው ሲዋረድ በአረብ ምድር ሲገደል አንደ አንስሳ ሲታረድ ህይወት ሲቀጠፍ ሲታነቅ በገመድ ዜግነት ክብሩ ሲዋረድ ሰአብዊ መብቱ ሲናድ የመኖር ህልሙ ባዶ ሲሆን ፊቱ በአንባ ሲታጠብ ሲዋጥ በሀዘን ለስቃይ ችግር ሲዳረግ በረሀብ አለንጋ ሲገረፍ ጠኔ ሲመታው በከባድ ህመም ሕይወት ሲቀጠፍ ሀገር ወገን ሲጣራ ሰሚ ሲያጣ ሲያለቅስ መንግስት ጆሮ ሲደፈን አልሰማ ሲል ሲሆን ደንታቢስ አስከመቼ ነው ዝምታው ላገር ለወገን መድረሻው የብሶት የችግር ማብቂያው ተነሳ ወገን ህብረት አንድነት አጠንክር ጨካኝ ወያኔን … [Read more...] about ዝምታው በዛ
“ምኒልክነትን የጠየቀው” የአድዋ ድል!
“ … ወታደር ባለመሆኔ የጦርነቱን ውሎ ማተት አያምርብኝም፡፡ ያም ሆኖ የአድዋ ድል ዛሬ ብርቅ በሆኑብን ሁለት እሴቶች ረድኤት የተገኘ ይመስለኛል፡፡ እኒህ ሁለት እሴቶች መተባበርና መደማመጥ ናቸው፡፡ ጣልያኖቹ በጊዜው ወደ ጦርነት ሲገቡ ተስፋቸውን የጣሉት በመድፍና በጠመንጃቸው ሳይሆን ኢትዮጵያውያን ዝነኛ በነበሩበት የውስጥ መቆራቆስ ላይ ነው፡፡ የትግራይ ቅልጥም ሲመታ ሸዋ ያነክሳል ብለው አላሰቡም፡፡ በርግጥም በክፍለ ሀገሮች ውስጥ የተለያዩ ሽኩቻዎች ነበሩ፡፡ እኒህን ሽኩቻዎች አስረስቶ ኢትዮጵያውያንን ሁሉ ለአንድ አላማ ማሠለፍ ምኒልክነትን ይጠይቃል፡፡ “መደማመጥ ያልሁትን ላሳይ፡፡ አባ ዳኘው ከዛሬው የይስሙላ ፓርላማችን በተሻለ ሁኔታ ለልዩነቶች ቦታ የሚሰጥ ተንቀሳቃሽ ምክር ቤት በጦርነቱ ወቅት መፍጠር ችለዋል፡፡ ፀሐፌ ትእዛዝ ገብረሥላሴ በውጊያው ዋዜማ የነበረውን ሁኔታ እንዲህ … [Read more...] about “ምኒልክነትን የጠየቀው” የአድዋ ድል!
ሕወሃትና የኢትዮጵያዊነት ገጽታው
ባለፈው የካቲት 11 2006 የህወሃት ምስረታ በአል ሲከበር ጠ/ሚንስትር ሀይለማርያም ደሳለኝ ያደረጉትን ንግግር ሲጀምሩ የትግራይ ሀዝብ ከአስከፊው ብሄራዊ ጭቆናና ፋሽስታዊ ስርአት ጋር ተናንቀው … ብለው ነበር እናም በርግጥ የህወሀት የትግል መስመር እና አለማ ምን ነበር? አሁን እንደሚባለው ኢትዮጵያን ከአስከፊው የደርግ ስርዐት ለመታደግ ወይስ በአንድ ወቅት መለስ ዜናዊ እነደተናገሩት “የድህነት ጠበቃ የነበረውን ደርግ” አሸንፎ ብልጽግና ለማምጣት? ሕወሐት የተመሰረተበትን አላማ የሚገልጽ የህወሀት ማኒፌስቶ (በ 1968 የታተመ መጸሔት) ለዚህ ጥሩ መልስ አለው ሰነዱ ላይ በግልጽ እንደተቀመጠው አጠቃላይ የህወሀት አላማ እና መድረሻ “የጨቋኟ አማራ ብኄርን” ጭቆና ለማስወገድ እና የትግራይ ሪፓብሊክ ማቋቋም ነው፡፡ ስለኢትዮጵያ እድገትም ሆነ የወደፊት አላማ ያስቀመጠው የልማት እቅድ … [Read more...] about ሕወሃትና የኢትዮጵያዊነት ገጽታው
የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና …
"የኢትዮጵያ ሃየር መንግድ ለአፍሪካ ኩራት ነው" ሲባል ከቃላት መፈክርነት ባለፈ የአውነትም ኩራት ስለመሆኑ ጥርጣሪ የሚያድርባቸው ዜጎች እንደሚኖሮ እገምታለው፡፡ ይሁን እንጂ የኢትዮጵያ አየር መንግድ በረዥም ታሪኩ ውስጥ ከሌሎች የአፍሪካ አገሮች በአንፃራዊነት በተቋሙ ውስጥ ስማቸው እጅግ የገነነ ብቁ አብራሪዎች፣ የቴክኒክ ባለሙያዎች (ግራውንድ ቴክኒሻን) እና ድጋፍ ሰጪ ሰራተኞች በአብዛኛው በኢትዮጵያዊያን የተሞላ ነው፡፡ ለዚህም ነው የአፍሪካ ኩራት ለመባል የበቃው፡፡ ይህ ኩራት እና አድናቆት ከታላቁ አፍሪካዊ የነፃነት ታጋይ ኔልሰን ማንዴላ ጀምሮ ጥቂት በማይባሉ አፍሪካዊያን ዘንድ ተቀባይነት ያገኘ ነው፡፡ በተጨማሪም የኢትዮጵያ አየር መንገድ ሎሜ፣ማላዊ እና ቶጎ በመሳሰሉ የአፍሪካ አገሮች ከፍተኛ አክሲዮን ሼር በመግዛት እያስተዳደረ እና እያንቀሳቀሰ ይገኛል፡፡ እንዲሁም የተለያዩ … [Read more...] about የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና …
ጀግናውና ከሀዲው ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራ
ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራ በረዳትነት የሚያበረውን ቦይንግ 767 አውሮፕላን አቅጣጫ ቀይሮ ስዊዘርላንድ የፖለቲካ ጥገኝነት በመጠየቅ ካሳረፈ ወዲህ የዓለም አቀፍ የብዙኃን መገናኛውን ትኩረት ይዞ ቆይቷል፡፡ ከዚህ ድርጊት በኋላም በሁለቱም ጎራ ያሉ አካላት ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራን በተመለከተ የተለያየ መላምት ትችትና ነቀፋ ሲሰነዝሩበትና ሲሰናዘሩበት ሰንብተዋል፡፡ የሕዝብ ወገን የሆነው ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራን ጀግና ነው አርበኛ ነው ሲለው “መንግሥት” እና ደጋፊዎቹ ደግሞ ከሀዲ ነው ብለውታል፡፡ እነኝህ ሁለቱም አካላት ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራን በየበኩላቸው ያሉትን ለመሆኑ የየራሳቸውን ማስረጃ የሚሏቸውን ነገሮች በመግለጽ ላይ ናቸው፡፡ የሕዝብ ወገን የሆነው ክፍል ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን ጀግና ነው የሚሉበትን ምክንያት ሲጠቅሱ በአገዛዙ ተማሮ … [Read more...] about ጀግናውና ከሀዲው ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራ
“ግብረሰዶማውያን ከተፈጥሮ ውጪና አጸያፊ ናቸው”
የዑጋንዳው ፕሬዚዳንት ዩዌሪ ሙሴቪኒ “አከራካሪ” ሲባል የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊ ህግ በፊርማቸው አጸደቁ፡፡ ግብረሰዶማውያንን “ከተፈጥሮ ውጪ የሆኑ” እና “አጸያፊ” ሲሉ ገልጸዋቸዋል፡፡ ግብረሰዶማዊነት በምዕራቡ ዓለም አማካኝነት ወደ አፍሪካ እየተስፋፋ የመጣ ነው ብለዋል፡፡ ለበርካታ ዓመታት አከራካሪ ሆኖ የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊነት ሕግ ትላንት ዑጋንዳ አጽድቃለች፡፡ ከምዕራቡ ዓለም እና ሰዶማዊነት የመብት ጉዳይ እንደሆነ ከሚከራከሩ ተቋማት የደረሰባትን ውትወታ ወደ ጎን በማለት ዑጋንዳ በሕግ ማጽደቋ የበርካታ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ሽፋን የሰጡበት ርዕስ ሆኗል፡፡ የሕጉን መጽደቅ አስመልክቶ ጥቂት ዑጋንዳውያን ተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ሲሆን በርካታዎች ደግሞ ድጋፋቸውን ለፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡ ሕጉን በፊርማቸው ያጸደቁት ዩዌሪ ሙሴቪኒ ሲኤንኤን ላይ ለቀረበላቸው ጥያቄ ሲመልሱ … [Read more...] about “ግብረሰዶማውያን ከተፈጥሮ ውጪና አጸያፊ ናቸው”
ለስምህ ስም ሁነው
ከሚለጥፍብህ ከአፉ እንደመጣ ሚሻለውን መርጠህ ለራስህ ስም አውጣ ሺ ጨዋ ብትሆን ሚልዮን ጥንቁቅ ሰው ሰው በሰውነትህ የሚልህ ስላለው በችሎታህ መጠን ኪሎህን መዝነህ ጭማሪ መጠሪያ ስም ስጠው ለራስህ ሚጠራህ ከጠፋ አንተ ባወጣኸው በተግባር ታይና ለስምህ ስም ሁነው። … [Read more...] about ለስምህ ስም ሁነው
ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ በጀርመን ተካሄደ
እ.ኤ.አ. በፌብሯሪ 22, 2014 ዓ.ም. የኢትዮጵያ ህዝብ አብዮታዊ ፓርቲ (ኢ.ሕ.አ.ፓ) በኑረንበርግ ከተማ በጠራው የሩብ ዓመት መደበኛ ስብሰባ የድርጅቱ አባላትና ጥሪ የተደረገላቸው ወገኖች በተገኙበት በደማቅ ሁኔታ ተካሄደ። የድርጅቱን የሩብ ዓመት እንቅስቃሴ ሪፖርት በማቅረብ የዕለቱን ፕሮግራም ያስጀመሩት የድርጅቱ የፕሮፖጋንዳና የህዝብ ግንኙነት ተጠሪ አቶ በየነ መስፍን ሲሆኑ በወቅታዊ የሀገራችን ጉዳይ ላይም የፓናል ውይይት ተደርጓል።በተለይም የወያኔ መንግስት በማናለብኝነት ከመጋረጃ ጀርባ በዳር ድንበራችን ላይ እያደረገ ያለውን ቁማር ከማውገዝ ባሻገር ይህንን ታላቅ ሀገራዊ ክህደት በተጨባጭ በተግባር ለመቀልበስ ምን ይደረግ በሚለው ዙሪያ ሰፊና ጥልቅ ሃሳቦች የተንሸራሸሩ ሲሆን በቅርቡ የአማራ ክልል ምክትል ፕሬዝደንት አቶ አለምነው መኮነን የአማራ ህዝብን የሚያንቋሽሽ ፀያፍ … [Read more...] about ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ በጀርመን ተካሄደ
‘‘ፋሽዝም’’ በኢትዮጵያ!
ኢትዮጵያ በወያኔ ፈላጭ ቆራጭ ቡድናዊ አገዛዝ ስር ከወደቀችበት እነሆ ሁለት አስርተ ዓመታት ነጐዱ። ወያኔ ስልጣን ላይ ሲወጣ ካለፈው የተሻለ የዲሞክራሲ ለውጥ ይመጣል የሚል በብዙ ሰዎች ዘንድ የተስፋ ጭላንጭል ተጥሎለት ቢኖርም “ጅብ እስኪነክስ ያነክስ” እንዲሉ ስልጣናቸውን ካደላደሉ በኋላ ግን ተስፋ የተጣለለትን ዲሞክራሲ ደብዛውን በማጥፋት “ከፋፍለህ፣ በሆዱ ይዘህ፣ አሸብረህ፣ አደናግረህ፣ አናቁረህና አደንዝዘህ ግዛ” የሚለውን ሌሎች አምባገነን መንግስታት የሚከተሉትን የጡንቻ አገዛዝ ዘይቤ የዲሞክራሲ ሽፋን በመስጠት ዘላለማዊ ስልጣናቸውን ለማጠናክር ሲሉ በበለጠ ሲጠቀሙበት መቆየታቸው የአደባባይ ሚስጢር ሆኖ ቆይቷል። በአገራችን ኢትዮጵያ በሥልጣን ላይ ያለው የወያኔ አገዛዝ በዓለም ዙሪያ በተለያየ ዘመን ወደ ሥልጣን ከመጡት መሰል ፀረ-ሕዝብ መንግሥታት ቢብስ እንጂ በምንም መልኩ … [Read more...] about ‘‘ፋሽዝም’’ በኢትዮጵያ!







