". . . ገብረሕይዎት በመንግሥት እና የህዝብ አስተዳደር መፅሃፉ መቅድም ላይ እንዲህ ይላል፤ «ሕዝቦችን ሁሉ የሚፈጥር አንድ አምላክ ነው። ይህም አምላክ የምንለው የሕዝቦች ፈጣሪ ሕዝቦችን ሁሉ ትክክል አንድ አድርጎ ፈጥሮ ላኗኗራቸውና ለልማታቸው የሚያስፈልጋቸውን ነገር ሁሉ ከሙሉ ፈቃድና ስልጣን ጋር በእጃቸው ሰጥቷቸዋል። ስለዚህ ማናቸውም ህዝብ ቢለማም ቢጠፋም በገዛ እጁ ነው። ሕዝብ የሚጠፋበት አንዳንድ ምክንያት ቢያገኝ ያውም ምክንያት በአንዳንድ ሰው ቢመካኝ ትክክል አይደለም። የልማትን መንገድ ለማግኘት የሚጥር ሕዝብ ቢገኝ በአንዳንድ ክፉ ሰው ምክንያት ሊጠፋ አይችልም። እንዲሁም ደግሞ የልማትን መንገድ ለማግኘት የማይጣጣር ሕዝብ በአንዳንድ ደህና ሰው ኃይል ልማት ሊያገኝ አይችልም።» ይህ የገብረሕይዎት ተጠይቃዊ ሀሳብ ኢትዮጵያ ያለችበትን ወቅታዊ ሁኔታ ለመመርመር ሲጠቀመን … [Read more...] about የሽግግር ሃሳብ
Opinions
የኔ ሃሳብ
የዐማራ ድምፅ ሬድዮን እንርዳ
በአሁኑ ዘመን በኢትዮጵያ ውስጥ ሁሉ ነገር እያለው ሁሉንም ያጣ ዜጋ ዐማራው ነው ቢባል የተጋነነ ነው ሊባል አይችልም። በግልጽ እንደሚታወቀው፣ ዐማራው ቋንቋው አማርኛ ነው። ይህንን ቋንቋውን ከሌሎች የኢትዮጵያ ጎሣዎች ቋንቋዎች ጋር አጣጥሞ በማሳደግ ለሁሉም ኢትዮጵያዊ የጋራ መግባቢያ እንዲሆን አበርክቷል። ይሁን እንጂ፣ በአሁኑ ጊዜ የአማርኛ ቋንቋ ለዐማራው ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ተለይቶ መከበሪያው መሆኑ ቀርቶ መጠቂያው ሆኗል። በአማርኛ ቋንቋ የሚጻፉት፣ በሬድዮ እና በቴሌቪዥን የሚቀርቡት ዝግጅቶች በአብዛኛው ማለት ይቻላል፣ ዐማራው የሚወገዝባቸው፣ የሚዋረድባቸው እና የሚኮነንባቸው እየሆኑ ከመጡ ዓመታትን ተሻግረው ዘመናት ተቆጥረዋል። ስለሆነም ዐማራን እና አማርኛን በጠላትነት ፈርጀው የጥፋት ተግባራቸውን ለፈጸሙና ለሚፈጽሙ ኃይሎች አጸፋውን በመስጠት፣ የአማርኛ ቋንቋም ሆነ የዐማራ ነገድ … [Read more...] about የዐማራ ድምፅ ሬድዮን እንርዳ
በጅዳ ሽሜሲ በር ላይ ወድቃለች የተባለችው እህት ጉዳይ!
ከትናንት ጅዳ ውስጥ በጠና ታማ እሷና ልጇ አደጋ ላይ አሉ ስለተባ ለችው እህት እየተሰራጨ ያለው መረጃ ደርሶኛል። መረጃውን በዝርዝር ያገኘሁት ከሊያ ሾው ነበር፣ ታመመች የተባለችውን እህት በቪዲዮ የተደገፈ መረጃ እንደደረሰኝ ወደ ጅዳ ቆንስል ደውዬ ለማጣራት ሞክሬ ነበር! በጅዳ ቆንስላ መረጃ ለማግኘት ከባድ እየሆነ መጥቷ ል፣ አንዳንዶች ኃላፊዎች ከዚህ ቀደም በማቀርባቸው ተጨባጭ ሂሶች አኩርፈው መረጃ ላለመስጠት ስልካቸውን ይዘጉብኛል፣ አንዳንዶች ደግሞ መረጃም ሆነ ጥያቄ ለመመለስ ፈቃደኛ አይደሉም! እጅ አዙር በሆነ መንገድ የጅዳ ቆንስል መረጃው እንዳልደረሰው ተነግሮኛል! ይህች እህት በሽሜሲ ጊዜያዊ እስር ቤት በር ላይ ተጥለላች መባሉን ሰምቸ ወደ ቦታው የሚያጣራልኝ የስራ ባልደረባዬን ልኬም ነበር፣ ዛሬ ረፋድ ላይ በር ላይ ተዟዙሮ የወደቀ ሰው አለመኖሩን አረጋግጦልኛል! ይህን … [Read more...] about በጅዳ ሽሜሲ በር ላይ ወድቃለች የተባለችው እህት ጉዳይ!
የወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ማንነት
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ወርቅነህ ገበየሁ በፓልቶክ ክፍል ቀርቦ የኦሮሞ ተወላጅ መሆኑን አስረግጦ ተናግሯል። ካፈርኩ አይመልሰኝ ነገር። አንድ ሰው ከመሬት ተነስቶ ከዚህ ዘር ነኝ የማለት የተጠበቀ ነው። የዘር ቆጠራን ያመጡት ራሳቸው ስልጣን ላይ ያሉት ዘረኞች ናቸው እንጂ እኛ አይደለንም። ዛሬ የራሳቸው ቃል እስረኛ የሆኑ ይመስላል። ጥያቄው ዘሩን በገዛ ፈቃዱ የመቀየር ጉዳይ አይደለም። ተቃውሞው ሹመቱ ላይም አይደለም። በዘር ያመጡት የስልጣን ኮታ ዘሩ ባልሆነ ግለሰብ ሲደለደል - ጉዳዩን ለሚያውቁት ንቀት እና ስድብ ይሆናል። ወርቅነህ የኦሮሞ የገዳ ሥርዓት በሚፈቅደው "ጉዲፈቻ" እና "ሞጋሳ" ባህል መሰረት ወደ ኦሮሞነት ተቀይሮ ከሆነ ግልጽ ይሁን። ካልሆነ ግን የእሱን ማንነት የሚገልጸው ዶክመንት ተመልክቶ ፍርድ መስጠቱ ይበጃል። ለስድስት ዓመታት በድህንነት ሲሰራ በርካታ ንጹሃን … [Read more...] about የወርቅነህ ገበየሁ ወልደኪዳን “ነገዎ” ማንነት
የኢትዮጵያን ወቅታዊ ችግርና የመፍትሄ አቅጣጫ በሚመለከት የተሰጠ መግለጫና የሰላም ጥሪ
የኢትዮጵያን ችግር የመፍትሄ መንገድ በሚመለከት "ኢትዮጵያን ለማዳን እንነጋገር" በሚል ርእስ ቀደም ሲል አንድ የሰላም ጥሪ ማቅረባችንን እናስታውሳለን። መልእክቱም ባጭሩ ይህች ታላቅ ሀገር የገጠማት ችግር ሊፈታ የሚችለው በመሪዎቿና በልዩ ልዩ የተቃውሞ ጎራ በተሰለፉ የራሷ ልጆች ብቻ መሆኑን፤ መፍቻ መንገዱም ውይይትና ንግግር መሆኑን፤ ጊዜውም አሁን መሆኑን የሚያመላክት ነበር። ለዚህም ሁሉም ወገኖች ቢያንስ በችግሩ ላይ ለመነጋገር መስማማት እንዳለባቸው በመጠቆም ለሰላማዊ ውይይት እንዲተባበሩና ሃሳባቸውን እንዲገልፁልን አሳስበንም ነበር። ጥሪውን የተመለከቱ ድርጅቶችና ግለሰቦች የሰጡንን በጎ ምላሽና ማበረታቻ በምስጋናና በአክብሮት ተቀብለናል፤ ደስ ብሎናልም። የሰላም ውይይት ወደሰላም በር የሚወስድ ጠቃሚ ስልት መሆኑን በማመን ድርጅታችን ላቀረበው የውይይት መድረክ ዝግጅት ሃሳብ … [Read more...] about የኢትዮጵያን ወቅታዊ ችግርና የመፍትሄ አቅጣጫ በሚመለከት የተሰጠ መግለጫና የሰላም ጥሪ
የአሜሪካ ምርጫ:- ዶናልድ ትረምፕ ወይስ ሂለሪ ክሊንተን?
መግቢያ የዛሬ ስምንት ዐመት ባራካ ኦባማ ለፕሬዚደንትነት ምርጫ ለውድድር ሲቀርቡ፣ ከፕሪመሪው ጀምሮ የነበረውን የምርጫው ሂደት እዚህ አውሮፓ ሆነን በየሰዓቱ ሁኔታውን በጥብቅ እንከታተል ነበር። በማያጠራጥር መልኩ የብዝዎቻችን ፍላጎትና አድልዎ ለባራክ ኦባማ ቢሆንም፣ ባራክ ኦባማ ያንን አስቸጋሪ የፕሪመሪ ውድድር አልፈውና ተፎካካሪዎቻቸውን አሸንፈው የዲሞክራቲክ ፓርቲውን በመወከል ለፕሬዚደትነት ምርጫ ይቀርባሉ ብሎ የገመተ አልነበረም። የመጨረሻ መጨረሻ ወይዘሮ ሂለሪ ክሊንተን በአሸናፊነት በመውጣት ፓርቲያቸውን በመወከል የሪፓብሊካን ፓርቲን ከሚወክለው ጋር ለውድድር ይቀርባሉ የሚል ግምት ነበረን። አሁንም ቢሆን የኢንስቲቱሽናል ሬሲዝምነትና አጠቃላይ ሬሲዝምነት በነገሰበት በአሜሪካን ህብረተሰብ ውስጥ አንድ ጥቁር አሜሪካዊ ለፕሬዜደንትነት ምርጫ በመወዳደር በአሸናፊነት ይወጣል ብሎ … [Read more...] about የአሜሪካ ምርጫ:- ዶናልድ ትረምፕ ወይስ ሂለሪ ክሊንተን?
The changing face of Ethiopia
The US elections are over and I have not met anyone happy with the outcome. All the dirty linen was washed in public and the winner was the one with the most stain. The opinion polls malfunctioned spectacularly. I followed the election process as told by what is called the ‘liberal’ media. Huffington Post, Slate, The New Yorker among many convinced me it was going to be a ride in the park for Secretary Clinton. HP even gave the Democrats a 91.5% percent of winning the Presidency. In case you … [Read more...] about The changing face of Ethiopia
“ነጻነት ሰው ከመሆን የሚገኝ መብት ነው”
ግዛው ለገሰ በጣም መሠረታዊና አንገብጋቢ፣ ጊዜያዊም ጉዳዮችን አንሥቷል፤ በበኩሌ ጉዳዮቹን በማንሣቱ በጣም እያመሰገንሁት አስተያየቴን በአጭሩ እንደሚከተለው አቀርባለሁ፡፡ ‹‹ህወሓት የተቋቋመው በአማራ ጥላቻ ነው፡፡ ይህን ሀቅ ሳይቀበሉ ስለነፃነት ማታገል አይቻልም፡፡ ነፃነት ደግሞ የዜግነት መበት እንጂ የወል መብት አይደለም፡፡ ነፃነት በማንነት ትግል አይገኝም፡፡›› ግዛው በጣም መሠረታዊ ነጥብና ሀሳብ አቅርበሃል፤ ነገር ግን ድብልቅልቁ ወጣብኝ! መነሻ፡--‹‹ሕወሀት የተቋቋመው በአማራ ጥላቻ (ላይ?) ነው፤›› ከዚህ ትነሣና፡-- ‹‹ይህንን ሀቅ ሳይቀበሉ ስለነጻነት ማታገል (መታገል?) አይቻልም፤›› ትላለህ፡፡ እንደምረዳው ግልጽ ያልሆነልኝ ግዛው ሁለቱን ዓረፍተ ነገሮች እርስበርሳቸውና እያንዳንዳቸውን ከነጻነት ጋር ያቆራኛቸው እንዴት ነው? የሚል ነው፤ በእኔ አስተሳሰብ ምንም … [Read more...] about “ነጻነት ሰው ከመሆን የሚገኝ መብት ነው”
“HILLARY WINS” መስፍን በዙ
* የጅብ ችኩል … መቸም ይህ የአሜሪካ ምርጫ ከቅስቀሳው እስከ ትራምፕ ምርጫ ትዝታው ብዙ ነው፣ በመጨረሻው ቀንና በምርጫው ውጤት ቀን የሆንነው ግን በጣም ያጓጓና ልዩ ትዝታ ይዞ ያለፈ አጋጣሚ ነው፣ ለብዙዎቻችን ... የማልረሳውን የእኔን ትዝታ ከትዝብት ጋር ላጋራችሁ ... "እውነትን እንጂ ውሸትን አናስተናግድም!" የሚል መርህን ይዘው ከሚንቀሳቀሱት የቲጂ ቲቪ አዘጋጅ ጋዜጠኛ መስፍን በዙ "HILLARY WINS" "ሄለሪ አሸነፈች!" የሚል አንድ አስገራሚ ሰበር መረጃ ከሌሊት 3:34 Am ተሰራጭቶ ደረሰኝ። HILLARY WINS ከሚለው መረጃ ስር "ቲጂ ቴሌቪዥን ጠዋት ላይ የምርጫ ጣቢያዎቹን ጎብኝቶ ባገኘው መረጃ መሰረት ሄለሪ የአሜሪካ 45ኛ ፕሬዚደንት ሆነው ተመርጠዋል" በሚል የሚያትተው መረጃ አስገራሚ ነበር፣ መረጃው ለሄለሪ ደጋፊ ደስታ፣ ለትራምፕ ደጋፊ ሀዘንም ነበር ... … [Read more...] about “HILLARY WINS” መስፍን በዙ
ይድረስ ለጀዋር መሃመድ
Brotherly advice to Ethiopian Friends በሚል ርእስ በፌስቡክ ገጽህ ለኢትዮጵያውያን ወንድሞችህ የሰጠህውን ምክር አነበብኩት። ጽሁፍህን ሳነብ የመጀመሪያ ባለመሆኑና በፌስቡክ አስተያየቶችህ ላይ ስለምከታተልህም ሃሳብህን ለመረዳት ብዙም አልቸገረኝም። በተለይ ወጣት ኢትዮጵያውያን ወደ ከፍተኛ የፖለቲካ አስተሳሰብ መድረክ መምጣት ለሃገራችን የሚኖረውን ዘላቂ ጠቀሜታ የምገነዘብ በመሆኑ ጀዋር የፖለቲካ ተንታኙ ወጣት እየተባለ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ ቀርበህ ሃሳብ ስትሰጥ ከአምስትና ስድስት አመት በላይ አውቅሃለሁ። ወጣቱ ጀዋር በዚሁ ከቀጠለ በሃገራችን ኢትዮጵያ ጥሩ ፖለቲከኞችን ልናፈራ እንችላለን የሚል ጽኑ እምነት ነበረኝ። በተለይም የኢትዮጵያ ብሄር ብሄረሰቦች ችግር የሚፈታው በኢትዮጵያ ዲሞክራሲ ፍትህ እና እኩልነት የሚያመጣ ስርአት በመገንባት ነው። የኦሮሞም … [Read more...] about ይድረስ ለጀዋር መሃመድ










