“ሕዝቡን ካፈንከው እና ከመቃወም ሌላ አማራጭ ካሳጣኸው ይፈነዳል፤ ወጣቱ በሙሉ ዓመጽ ላይ ነው፤ ትውልድ አምጿል”፡፡ “(ትግሉን) በአንድ ጥላ ሥር እያስተባበርን ነው”፡፡ የኒውዮርክ ታይምስ ጋዜጠኛ JEFFREY GETTLEMAN በኢትዮጵያ ያለው ወቅታዊ ሁኔታ በተነተነበት ጽሁፍ ላይ የጠቀሳቸው ሁለት ግለሰቦች የተናገሩት ነበር ከላይ የሰፈረው፡፡ ጋዜጠኛው ዘገባውን ሲጀምር “ኢትዮጵያ እየተሰነጣጠቀች ነውን” በማለት ይጠይቅና በሁሉም አቅጣጫ ያለውን አመለካከት ያሰፍራል፡፡ (ከዜና ዘገባው ጋር Violent Protests in Ethiopia በሚል ርዕስ የጸጥታ ኃይሎች ሰላማዊ ሰልፍ በወጣ ህዝብ ላይ የሚፈጽሙትን አሰቃቂ ግፍ እና ጨካኝ ድብደባ እዚህ ላይ መመልከቱ የግድ ይላል)፡፡ “ልማት” አካሂዳለሁ የሚለው ህወሃት/ኢህአዴግ የሕዝብን መሠረታዊ ጥያቄዎች አለመመለሱን የሚያትተው ዘገባ … [Read more...] about “ትውልድ አምጿል!”
News
ዜና
“ለባስልጣናት ለሚታዘዝ ፍ/ቤት (ቃላችንን) አንሰጥም” እነ በቀለ ገርባ
የኦሮሞ ፈደራሊስት ኮንግረስ ከፍተኛ አመራር አባላት አቶ ጉርሜሳ አያኖ፣ አቶ ደጀኔ ጣፋ፣ አቶ አዲሱ ቡላላ እና አቶ በቀለ ገርባን ጨምሮ 22 ተከሳሾች ዛሬ ልደታ ምድብ ፍርድ ቤት ቀርበው የሰጡት የእምነት ክህደት ቃል ከዚህ የሚከተለው ነው። ጉርሜሳ አያኖ፤ “ክሱ ግልፅ አልሆነልኝም እኔ ፖለቲከኛ ስሆን የመድረክ ፓርቲ-አባል ነኝ፡፡ የእኛ ፓርቲ ህገመንግስቱን ተከትሎ የተቋቋመ ህጋዊ ፓርቲ ነው፡፡ የተከሰስኩት ግን የኦነግ አባል ነህ በሚል ነው፣ እኔ እስከማውቀው አንድ ሰው የሁለት ድርጅት አባል መሆን አይችልም፡፡ ይሄ ክስ መንግስት መሬቴን አሳልፌ አልሰጥም ያለዉን የኦሮሞን ህዝብ በጅምላ አሸባሪ ብሎ እየከሰሰ ነዉ ያለው ስለዚህ ቃሌን ለዚህ ፍ/ቤት አልሰጥም፡፡” ደጀኔ ጣፋ፤ “የኢትዮጵያ ፍ/ቤት በግልፅ ህገመንግስቱን እያፈረሰ ያለ ተቋም ስለሆነ ለዚህ ፍ/ቤት ቃሌን አልሰጥም፣ … [Read more...] about “ለባስልጣናት ለሚታዘዝ ፍ/ቤት (ቃላችንን) አንሰጥም” እነ በቀለ ገርባ
“ጸጥታ አስከባሪው” ህወሃት/ኢህአዴግ ጸጥታው ሊገመገም ነው
ከዚህ በፊት ሆኖ የማያውቅ በሚመስል ሁኔታ ኢትዮጵያ በህወሃት/ኢህአዴግ ዘመን ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ያገኘች አስመስሎ የሚያወራው ህወሃት “ጸጥታ አስከባሪ ነኝ” እያለ በአፍሪካ ሳይጠሩት አለሁ የሚለውን ያህል አሁን ደግሞ በተራው በአገር ውስጥ ህዝብን ጸጥታ በመንሳት ሊገመገም መሆኑ ተነገረ፡፡ “በኢትዮጵያ ሰላም ለማስከበር በሚል የህወሃት ጄኔራሎች የተባበሩት መንግሥታትን ምደባ እየጠየቁ ነው” በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተሳልቀዋል፡፡ ከጥቂት ወራት በፊት ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ምክርቤት ድምጽ የማትሰጥ አባል ሆና መመረጧ የህዳሴው ውጤት ነው፤ የመለስ ራዕይ ተግባራዊነት ነው፤ … በማለት ከፍተኛ ዲስኩር የነፋው፤ ከበሮ የደለቀው ህወሃት “ህዝብን ጸጥታ ነስተሃል” ተብሎ በተባበሩት መንግሥታት የምርመራ ግዴታ ተጥሎበታል፡፡ በንጉሡ ዘመን እንዲሁም በደርግ ጊዜ የጸጥታው … [Read more...] about “ጸጥታ አስከባሪው” ህወሃት/ኢህአዴግ ጸጥታው ሊገመገም ነው
እነ አባይ ጸሃዬ አሜሪካ ነበሩ፤ “ኦሮሞና አማራ ተባበሩብን፤ ሰግተናል”
የትግራይ ነጻ አውጪ ግንባር ከፍተኛ አመራር አባይ ጸሃዬ፤ ሳሞራ የኑስን ጨምረው ሌሎች ከፍተኛ የህወሃት ባልደረቦቻቸውንና በመያዝ አሜሪካ አገር አጭር ቆይታ አድርገው መመለሳቸውን ጎልጉል አረጋግጧል። አሜሪካ በግል የተቃዋሚ ፓርቲዎችን በማነጋገር ውሉ ባግባቡ የማይታወቅ የሽግግር ሃሳብ ለመተግበር ማሰቧ ተሰምቷል። የሽግግር ሃሳቡ የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሃት) የያዘውን ስልጣን በተወሰነ መልኩ የሚያስቀጥል በመሆኑ ለአሜሪካ ፖሊሲ አውጪዎች ሃሳብ የሚያቀርቡ ተጽእኖ ፈጣሪዎች አሜሪካ ይህንን መሰሉን አቋም እንድትቀይር እየወተወቱ ነው። ለኦባማ አስተዳደር ፖሊሲ አውጪዎች ዕቅድ ለማቅረብ እነዚሁ ተጽዕኖ ፈጣሪዎች ዝግጅት አላቸው። ከሁለት ቀን በፊት አሜሪካ አጭር ቆይታ ያደረጉት እነ አባይ ጸሃዬ “እንወድቃለን” ብለው እንደሚሰጉ ለአለቆቻቸው አስታውቀዋል። የጎልጉል የዲፕሎማት … [Read more...] about እነ አባይ ጸሃዬ አሜሪካ ነበሩ፤ “ኦሮሞና አማራ ተባበሩብን፤ ሰግተናል”
ብአዴን እንደ ኦህዴድ ከዳ?!
በጎንደር ከተማ በበርካታ ሺዎች የሚቆጠር ሕዝብ ሰላማዊ ትዕይንተ ሕዝብ አካሄደ፡፡ አገራዊና ሕዝባዊ ጥያቄዎችን በማቅረብ በሌሎች የኢትዮጵያ ክፍሎች ለሚካሄደው ትግል ያለውን ድጋፍ ገለጸ፡፡ ስልታዊ ጥርነፋውን አልፎ ትዕይንተ ህዝብ ለማድረግ መቻሉ ብአዴን ህወሃት የሚዘውረውን ኢህአዴግ ለመክዳቱ ፍንጭ ሰጥቷል፡፡ እሁድ ሐምሌ 24፤2008ዓም በጎንደር ከተማ የተካሄደውን ሰላማዊ ሰልፍ ህወሃት/ኢህአዴግ ገና ከጅምሩ የማምከን ተግባር ለመፈጸም በርካታ የጸጥታ አባላትን በስፍራው መድቦ ነበር፡፡ ሆኖም ሕዝብ ከቀናት በፊት በተናገረው እና ራሱ ኢህአዴግ እመራበታለሁ በሚለው ሕገመንግሥት መሠረት ሰላማዊ ሰልፉን አስቀድሞ አሳውቆ፤ በአግባቡ መልዕክቱን አስተላልፎ በክብር ተመልሷል፡፡ ዓላማውን የሚያውቅና ለሚያምንበት የቆመ ህዝብ እስካለ ድረስ ኢህአዴግ ሰልፍ ቢፈቅድም ባይፈቅድም ሕዝብ ያለውን … [Read more...] about ብአዴን እንደ ኦህዴድ ከዳ?!
“ወጥቼ ስመለስ የዐሥራ ሦስት ዓመት ልጄ አስክሬን ቤት ጠበቀኝ” የአወዳይ ከተማ ነዋሪ ወ/ሮ ኢፍቱ አብደላ
በኦሮሚያ ክልል በተለያዩ ዞኖችና ወረዳዎች ላለፉት ዘጠኝ ወራት ሲካሄድ የነበረው ተቃውሞ ባለፉት ሁለት ሳምንታት በድጋሚ ማገርሸቱንና የሰባትና የ13 ዓመት ዕድሜ ያላቸው ሕፃናትን ጨምሮ በርካቶች እየተገደሉ መሆኑን የኦሮሞ ፌደራሊስት ኮንግረስና ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ። “ወጥቼ ስመለስ የዐሥራ ሦስት ዓመት ልጄ አስክሬን እቤት ጠበቀኝ” ያሉ የአወዳይ ከተማ ነዋሪም ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። ተቃውሞው በምስራቅ እና ምዕራብ ሐረርጌ፣ በምዕራብ አርሲና በምዕራብ ሸዋም እንዳለ ነዋሪዎቹ ይናገራሉ። በምስራቅ ሐረርጌ አወዳይ ከተማ ነዋሪ እንደሆኑ የገለጹት አቶ መሐመድ አብዱራህማን “የዐስራ ሦስት ዓመት ልጄ ተገሎብኛል፤ ቀብሩ ላይ መገኘትም አልቻልኩም” ይላሉ። በምስራቅ ሐረርጌ የሰላምና መረጋጋት ኃላፊ ኢንስፔክተር ግርማ ገላን በበኩላቸው ሞቱ ስለተባሉት ሰዎች የተጣራ መረጃ … [Read more...] about “ወጥቼ ስመለስ የዐሥራ ሦስት ዓመት ልጄ አስክሬን ቤት ጠበቀኝ” የአወዳይ ከተማ ነዋሪ ወ/ሮ ኢፍቱ አብደላ
በጎንደር የተነሳው አመጽ እየሰፋ ነው!
በጎንደር የሰዎች ህይወት ከማለፉ በተጨማሪ ሕዝብ የማያምንባቸውንና ከትግራይ ተገንጣይ ቡድን ጋር ግንኙነት አላቸው ባላቸው ንብረቶች ላይ ርምጃ መውሰዱ ታውቁዋል። ማክሰኞ ሊነጋጋ አካባቢ ተነሳ የተባለውን ህዝባዊ ተቃውሞ ለመቀላቀል ወደ ጎንደር ያመሩ ወገኖችም መበራከታቸው እየተሰማ ነው። ለዓመጹ ውጤታማነት የዘር ትግል ሳይሆን ኅብረብሔራዊ እንቅስቃሴ እንደሚበጅ ተገለጸ። አመጹ የተቀሰቀሰው የማንነት ጥያቄ ባነሱና "እኛ አማራ እንጂ ትግሬ አይደለንም" በሚል የተነሳውን ጥያቄ ከውጤት ለማድረስ ከተመረጡት የኮሚቴ አባላት መካከል አራት የሚሆኑትን ከትግራይ የመጡ ነፍጥ አንጋቾች ከያዟቸው በኋላ እንደሆነ ለኢሳት በድምጽ ማብራሪያ የሰጡ አረጋገጠዋል። ከዚያም ኮሎኔል ዘውዱ ደመቀን ለመያዝ ሙከራ ተደረገ። ይህን ጊዜ ኮሎኔሉ "በሬን አልከፍትም ጥዬ እወድቃለሁ" በማለት ሊያስሯቸው ከመጡት ሃይሎች … [Read more...] about በጎንደር የተነሳው አመጽ እየሰፋ ነው!
የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር “እየቀለለ” ነው!
ጠቅላላ ወጪው 475 ሚሊዮን ዶላር እንደሆነ የተነገረለት የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር በብልሽት ምክንያት ግማሽ ያህል ባቡሮቹ እንደማይሰሩ ተነገረ፡፡ የባቡሩ ፕሮጀክት ከመጠናቀቁ በፊት ሥራው እንዲጀመር ህወሃት/ኢህአዴግ ግፊት አድርጎ ነበር፤ የቀላል ባቡር ፕሮጀክት የፖለቲካ ውሳኔ ነው፤ ቀላል ባቡሩ “እየቀለለ ነው” ተብሏል፡፡ ማክሰኞ ዕለት የተሰማው ሸገር ሬዲዮ ስማቸውና ድምጻቸው እንዳይገለጽ የፈለጉ መረጃ አቀባዮቼ አደረሱኝ ባለው መሠረት ከተጀመረ ዓመት ያልሞላው የአዲስ አበባ የቀላል ባቡር ሥራ “እየቀለለ” መሆኑን ተናግሯል፡፡ ለአገልግሎት ከተመደቡት 41 ባቡሮች ውስጥ በሥራ ላይ የሚገኙት 28ቱ ብቻ መሆናቸውን መረጃ አቀባዮቹን ጠቅሶ ሬዲዮው አስረድቷል፡፡ ሃያ አንዱ ባቡሮች በብልሽት ምክንያት አብዛኛውን ጊዜያቸውን የሚሳልፉት በጥገና እንደሆነ፤ የመለዋወጫ ችግር ደግሞ ይበልጥ … [Read more...] about የአዲስ አበባ ቀላል ባቡር “እየቀለለ” ነው!
የህወሃቱ ሹም ራሳቸውን በራሳቸው ካዱ
በአዲስ አበባ ከተማ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሀና ማርያም፣ ፉሪ፣ ማንጎ ጨፌ ሌሎች በክፍለ ከተማው ስር ባሉ መንደሮች ከቤት መፍረስ ጋር በተያያዘ የሰው ሕይወት መጥፋቱ ይታወሳል፡፡ ሁለት ፖሊሶችና አንድ የወረዳው ሥራ አስፈጻሚ ህይወታቸው እንደጠፋ በይፋ ቢነገርም የዚያኑ ያህል ከዚህ ጋር በተያያዘ የተለያዩ መረጃዎች እየወጡ ይገኛሉ፡፡ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ባቀናበረው መረጃ ላይ እንዳመለከተው “መኖሪያ ቤቶቹ ይፈርሳሉ በመባሉ ከአካባቢው ነዋሪዎች የተወሰኑት አቤቱታ እያቀረቡ ባለበት ወቅት የመንግስት አፍራሽ ግብረኃይሎች ቤቱን ለማፍረስ የመብራት ትራንስፎርመር መንቀል እንደጀመሩና በዚህ መካከል ከፍተኛ ግጭት እንደተፈጠር ነዋሪዎች ይናገራሉ”። ከላይ በተጠቀሱት አካባቢዎች የመኖሪያ ቤቶች በዶዘር በሚፈርሱበት ወቅት ወንዶች በአካባቢው እንዳይጠጉ መከልከሉን ነዋሪዎች ይናገራሉ። ከተነሳው ግጭት … [Read more...] about የህወሃቱ ሹም ራሳቸውን በራሳቸው ካዱ
“ሪፎርም [ተሃድሶ] በገዥዉም በተቃዋሚዉም የግድ ያስፈልጋል”
ከጥቂት ቀናት በፊት “ሀገር አለኝ!! ወገን አለኝ!!” በማለት በፌስቡክ ገጹ ላይ ይህንን የለጠፈው የአንድነት ፓርቲ አመራር አቶ ሃብታሙ አያሌው በጠና ታምሞ በኮማ ውስጥ ይገኛል፡፡ “እዉነት እዉነት እላችሁአለሁ ስቃይና መከራ የምቀበልላት ብቻ ሳትሆን የምሞትላት ሀገር አለችኝ!! "ዘጠኝ ሞት መጣ ቢሉት አንዱን ግባ በለዉ" ከሚል ጀግና ህዝብ ተወልጄ በእስካሁኑ ስቃይ ጉልበቴ አይዝልም። እንድበረታ ዛሬም ከጎኔ ላልተለያችሁ ቃሌ ይሄ ነዉ። አመሰግናለሁ” ነበር ያለው! የትግል አጋሩ ዳንኤል ሺበሺ (Daniel Shibeshi) በጥቂት ሰዓታት በፊት በፌስቡክ ገጹ ላይ ከላይ የሚታየውን የሃብታሙን ፎቶ አድርጎ ያሰራጨው ጽሁፍ እንዲህ ይላል፤ “በሀብታሙ አያሌው ጤና መታወክ፣ እየተረባበሻችሁ ላላችሁ ሁሉ በያላችሁበት ሆናችሁ ፀሎታችሁን ቀጥሉበት። አሁንም በኮማ ውስጥ ነው ያለው። ለውጥ … [Read more...] about “ሪፎርም [ተሃድሶ] በገዥዉም በተቃዋሚዉም የግድ ያስፈልጋል”










![“ሪፎርም [ተሃድሶ] በገዥዉም በተቃዋሚዉም የግድ ያስፈልጋል”](https://staging.goolgule.com/wp-content/uploads/2016/06/habtamu-300x225.jpg)