• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ጸጥታ አስከባሪው” ህወሃት/ኢህአዴግ ጸጥታው ሊገመገም ነው

August 10, 2016 08:08 am by Editor 1 Comment

ከዚህ በፊት ሆኖ የማያውቅ በሚመስል ሁኔታ ኢትዮጵያ በህወሃት/ኢህአዴግ ዘመን ዓለምአቀፋዊ ዕውቅና ያገኘች አስመስሎ የሚያወራው ህወሃት “ጸጥታ አስከባሪ ነኝ” እያለ በአፍሪካ ሳይጠሩት አለሁ የሚለውን ያህል አሁን ደግሞ በተራው በአገር ውስጥ ህዝብን ጸጥታ በመንሳት ሊገመገም መሆኑ ተነገረ፡፡ “በኢትዮጵያ ሰላም ለማስከበር በሚል የህወሃት ጄኔራሎች የተባበሩት መንግሥታትን ምደባ እየጠየቁ ነው” በማለት አስተያየት ሰጪዎች ተሳልቀዋል፡፡

ከጥቂት ወራት በፊት ኢትዮጵያ በተባበሩት መንግሥታት የጸጥታ ምክርቤት ድምጽ የማትሰጥ አባል ሆና መመረጧ የህዳሴው ውጤት ነው፤ የመለስ ራዕይ ተግባራዊነት ነው፤ … በማለት ከፍተኛ ዲስኩር የነፋው፤ ከበሮ የደለቀው ህወሃት “ህዝብን ጸጥታ ነስተሃል” ተብሎ በተባበሩት መንግሥታት የምርመራ ግዴታ ተጥሎበታል፡፡ በንጉሡ ዘመን እንዲሁም በደርግ ጊዜ የጸጥታው ም/ቤት አባል በመሆን ማገልገሏ እንዳይነገር ብዙ ፕሮፓጋንዳ የሠራው ህወሃት የጸጥታው ምክርቤት የአባልነት ዘመኑ በ2017 ከመጀመሩ በፊት ይህ የገጠመው ችግር ያልታሰበ ዱብዕዳ ሆኖበታል፡፡ በመጪዎቹ የአውሮጳውያን ዓመት በጸጥታው ም/ቤት ወንበር ላይ ተቀምጦ በኤርትራና በሌሎች ወሳኝ ጉዳዮች ላይ ከማዕቀብ ጀምሮ ያሻውን ዓይነት ውሳኔ እንዲተላለፍ ዝግጅት ያደረገው ህወሃት/ኢህአዴግ የተመኘውን ወንበር በፎቶ እንዳየው በዚያው ሊቀር እንደሚችል አስተያየት ተሰጥቷል፡፡ ethiopia-security-council

የተባበሩት መንግሥታት የሰብዓዊ መብቶች ከፍተኛ ኮሚሽነር የሆኑት ዘዒድ ራድ አል ሁሴን ጄኔቭ ስዊትዘርላንድ በሚገኘው ጽ/ቤታቸው ለሬውተርስ በሰጡት መግለጫ ህወሃት/ኢህአዴግ በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ሰላማዊ ሰልፍ በወጣው ህዝብ ላይ ጥይት መተኮሱና 90 ሰልፈኞችን መግደሉ መረጃዎች ደርሰውናል ብለዋል፡፡ ይህንን ለማረጋገጥም ምርመራ ማድረግ የግድ እንደሆነ አስረግጠው ተናግረዋል፡፡ ኮሚሽነሩን የጠቀሰው የዜናው ዘገባ “የኢትዮጵያ መንግሥት ታዛቢዎች ምርመራ እንዲያደርጉ መፍቀድ አለበት” ብሏል፡፡

በሰላም ሰልፍ የወጡና የታሰሩ በሙሉ መለቀቅ አለባቸው ያሉት ኮሚሽነር ዘዒድ መርማሪዎች በአማራና በኦሮሚያ ክልሎች ሄደው ምርመራቸውን ማካሄድ እንዲችሉ ከህወሃት/ኢህአዴግ ሹሞች ጋር ንግግር መጀመሩን አስታውቀዋል፡፡

ከኢሳያስ አፈወርቅ ተቃዋሚዎች ጋር በማበር የተባበሩት መንግሥታት ልዩ ራፖርተር ዘገባ እንዲወጣና ኤርትራ ላይ ማዕቀብ እንዲጣል ጉድጓድ ሲቆፍር የነበረው ህወሃት የራሱን መቀበሪያ ራሱ ቆፍሯል በማለት አስተያየት ሰጪ ለጎልጉል ተናግረዋል፡፡ ዓለምአቀፍ የሰብዓዊ መብት ድርጅቶች በተደጋጋሚ በበቂ ማስረጃ ገዳይነቱን የመሰከሩለት ህወሃት/ኢህአዴግ፤ በዚህ የተባበሩት መንግሥታት ምርመራ ወንጀለኛ ሆኖ እንደሚገኝ ጥርጥር እንደሌላቸው በሰብዓዊ መብቶች ላይ የሚሰሩ ይናገራሉ፡፡

በአፍሪካ የተለያዩ አገራት የሰላም አስጠባቂ በመሆን ባልተጠራበት ሁሉ ወታደር እየላከ “ሰላም አስከባሪ ነኝ” ሲል የኖረው ህወሃት ሰላመ-ቢስ ብቻ ሳይሆን ጸጥታ አደፍራሽ መሆኑ ይፋ የሚደረግበት ጊዜ ላይ ነን የሚሉ ወገኖች ህወሃት የሻዕቢያን መቀበሪያ ሲያዘጋጅ ራሱ ሊቀበርበት ነው ብለዋል፡፡

የኮሚሽኑ ዘገባ ይፋ በሚሆንበት ጊዜ ሰላማዊ ሰዎችን በመግደልና በማስገደል እጃቸው ያለበትን ሁሉ ተጠያቂ እንዲሆኑ ዘገባው በማስረጃ ሰነድነት እንዲያዝ ከማድረግ ባለፈ ጥፋተኞቹን ለፍርድ የሚቀርቡበትንም አካሄድ ያመቻቻል፡፡

ያለ ዕውቀታቸውና ያለ ወታደራዊ ብቃታቸው ለሥራ ማመልከቻ እንዲረዳቸው የጄኔራልነት ሹመት የተጎናጸፉት የህወሃት ወታደራዊ ሹሞችና የቀድሞ የጦር ኃላፊዎች በሌላ የአፍሪካ አገር እንደለመዱት “በኢትዮጵያ ሰላም የለም፤ ጸጥታ ደፍርሷል፤ … የኢትዮጵያን ጸጥታ እናስከብራለን” በማለት የቅጥር ማመልከቻ እያቀረቡና ምደባ እየጠየቁ ይሆናል ሲሉ የህወሃትን ጠባብነትና ጭፍንነት የሚያውቁ ስላቃዊ አስተያየት ይሰጣሉ፡፡

ከዕውቀት ጋር ጠበኛ የሆነውና በተለይ የቁጥር ስሌት ሰለባ የሆነው ህወሃት በቁጥጥሩ ሥር ባደረገው ሚዲያ በአማራና በኦሮሞ ከተሞች የወጡትን በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩትን ሰላማዊ ሰልፈኞች “ጥቂት ጸረ ሰላም ኃይሎች” ብሎ በመሰየም ተቃውሞውን በቁጥጥር ሥር አውያለሁ ማለቱ ለግድያው ራሱ ኃላፊነት ስለመውሰዱ ምስክርነት የሰጠበት ሆኖ ለኮሚሽኑ እንደ ቀዳሚ ግብዓት እንደሚወሰድ ታውቋል፡፡

ከዚህ ጋር በተያያዘ የሰብዓዊ መብት ኮሚሽኑ ምርመራውን እንዲደርግና በህወሃት ሹሞች እንዳይታለል በተለይ በዳያስፖራ ያለው ኢትዮጵያዊ በኮሚሽኑ ላይ ግፊት እንዲያደርግ ተጠይቋል፡፡


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Comments

  1. Tesfaye amenu says

    August 19, 2016 12:18 am at 12:18 am

    Des yemell tarke new

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule