ከሁለት ሰአቱ የኢቲቪ ዜና አወጃ ተከትሎ የቀረበውን "ያልተገሩ ብዕሮች" ዶክመንተሪ በደረቁ ሌሊት ድጋሜ ስርጭቱ ተከታትየ ጨረስኩት ... ላፍታ እንደተጠናቀቀ ዝም፣ ጭጭ አልኩና በሃሳቤ በህዝብ ገንዘብ ከፍተኛ ወጭ እየተደረገባቸው የሚሰራጩትን የመንግስት የህትመት ጽሁፍና የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃንን አሰብኳቸው ... በምናብ ብዙ ርቄ ሔጀ በዶለደመ፣ ባልተገራ እና በተባውና በተገራው ብዕር ውስጥ ራሴን አትኩሮት ሰጥቸ የመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች በሃሳብ ተመላለስኩባች! ሰፊ ሽፋን ያለውን ኢቲቪና ራዲዮኑን፣ በየቀኑ እየታተሙ የሚወጡትን እነ አዲስ ዘመንን ጋዜጣንና የመሳሰሉት እሰብኳቸው ... አስቤ አሰላስየ ወደ ደረስኩበት ድምዳሜ ከማቅናቴ በፊት ግን በ"ያልተገሩ ብዕሮች" ዘጋቢ ፊልም ዙሪያ የታዘብኩትን ቀዳሚ አድርጌ የተሰማኝን ላካፍልዎ ወድጃለሁ... "ያልተገሩ ብዕሮች" … [Read more...] about የኢቲቪ “ያልተገሩ ብዕሮች” ዘጋቢ ፊልምና ያልተገራው አቀራረብ
Right Column - Primary Sidebar
ኢትዮጵያዊነት ማለት ክፍል ፩
“ ኢትዮጵያዊነት ማለት፤ ኢትዮጵያዊያንን መውደድ፣ ኢትዮጵያን ማፍቀር፤ የኢትዮጵያን መንግሥት በተገቢው መንገድ መደገፍና፤ ይህ መንግሥት የተሳሳተ መንገድ ሲይዝ መቃወም ማለት ነው። በሥልጣን ላይ ያለው ክፍል ፀረ-ኢትዮጵያዊያንና ፀረ-ኢትዮጵያ ሲሆን፤ ያንን ክፍል በማንኛውም መንገድ ማስወገድ፤ የያንዳንዱ ኢትዮጵያዊና የያንዳንዷ ኢትዮጵያዊት፤ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው። ” አብዛኛዎቻችን በየጊዜው የምናነሳው ጉዳይ፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለችበትን የፖለቲካ ሀቅና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ነው። ኢትዮጵያዊ ነኝ ወይንም አይደለሁም የሚለውን ጥያቄ አይደለም። በየቦታው፣ በተገኘው አጋጣሚ፣ በየዕለቱ በሕዝቡ ላይ የሚደረገውን በደል እናውጠነጥናለን። ኢትዮጵያዊያን ናቸው ወይንም አይደሉም የሚለው ከጥያቄያችን መካከል አይደለም። መቼም አርባ ዓመት ሙሉ፤ በአረመኔው መንግሥቱ … [Read more...] about ኢትዮጵያዊነት ማለት ክፍል ፩
የዘንዶ ሱባዔ?
መግቢያ ሱባዔ፦ በሰው፤ በቦታና በሰአት ስለሚከናወን የሶስቱም ማለትም የሰአት፤ የሰባዊነትና የመካን ድምር ነው። ሱባዔ በኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጥልቅ፤ ረቂቅና ምጡቅ ግንዛቤ አለው። በመንፈሳችንና በሥጋችን መካከል ያለውን ሚዛን አለመሰበሩንና አለማጋደሉን፤ በፈጣሪያችንና በራሳችን መካከል፤ በህዝባችንና በራሳችን መካከል ያለንን ግንኙነት የምንፈትሽበት ነው። በሩቅና በቅርብ ያለውን አካባቢያችንን ማየት የምንችልበት ተራራ ነው። ውስጣዊ ህሊናችንን የምናይበት ረቂቅ መስታወት ነው። የራቀውን አቅርቦ የረቀቀውን አጉልቶ የሚያሳየን፤ እመቀ እመቃት፡ አየረ አየራት፡ ያሉትን ሁሉ ፍጥረታት የምንፈትሽበት ተራዛሚ መነጽር ነው። ሱባዔ፦ በሰው ብቻ የተወሰነ አይደለም። በደማቸው ሞቃትነትና ቀዝቃዛነት የሚለያዩ ፍጥረታት በየደረጃቸው ሱባዔ ይገባሉ። የፍጥረታትን ቅደም ተከተል በመጠበቅ … [Read more...] about የዘንዶ ሱባዔ?
በዓሉን የበላው ደርግ “አይደለም”፣ የሰው ጅብ ነው!
እውኑን ቀርቶ ምስሉንም እንኳን አይቸው የማላውቀው[1] በዓሉ ግርማን አውቀዋለሁ። ህይወትን እና ሰውን የሚወደውን፣ ውብ ሰብዕና ያለውን በዓሉ ግርማን አውቀዋለሁ። በዓሉን፣ ሰብዓዊ እና ሞራላዊ ማንነቱን በጽሁፎቹ ውስጥ አይቻለሁ። በዓሉን አውቀዋለሁ። እናት አባት አያት፣ ቅማያት እና ቅንዝላቶቼ ሁሉ መጣፍ ቅዱስ ዳዊቱን፣ ቁራን ኪታቡን በነጋ በመሸ ቁጥር እየደገሙ እና እያነበቡ የኖሩትን ያህል፣ እኔ ደግሞ በዓሉን አንብቤያለሁ። በተለይ ኦሮማይን፣ ቢያንስ ከእጄ ከገባበት (ከ1978 ዓ.ም አጋማሽ ጀምሮ) ምናልባትም ከሶስት እና አራት ጊዜ በላይ ደጋግሜ ሙሉውን ያነበብኩትን ያህል፣ ለአምስት ወይም ስድስት አመት አካባቢ ደግሞ፣ ጧት ጧት ከእንቅልፌ ነቅቼ ከምኝታዬ በተነሳሁ እና ቤት ውስጥ በገባሁ በወጣሁ ቁጥር እንደሥሥት ልጅ ደጋግሜ እያነሳሁ በየቀኑ፣ ከጄ የገባውን አንድ ሁለት ገጽ … [Read more...] about በዓሉን የበላው ደርግ “አይደለም”፣ የሰው ጅብ ነው!
ትኩረት – ከውጪ ቋንቋዎች ለተወረሱ ቃላት
የሀገራችን ቋንቋዎች ከውጪ ቋንቋዎች በርካታ ቃላትን ወርሰዋል፡፡ ይህም ከብሉይ ዘመን ጀምሮ ይታይ የነበረ ክስተት ነው፡፡ የመወራረሱ አድማስ ስፋቱን የጨመረው ግን በአስራ ዘጠነኛው ክፍለ ዘመን መጨረሻ ላይ ነው፡፡ ከዚያን ጊዜ ጀምሮ በቀጣዮቹ አንድ መቶ ሀያ ዓመታት ውስጥ የታዩት ሀገር አቀፍና ዓለም አቀፍ ክስተቶች የሀገራችን ቋንቋዎችን ለውጪ ቋንቋዎች ተጽእኖ የበለጠ ክፍት እንዲሆኑ አድርገዋቸዋል፡፡ ታዲያ ከሶስት ሺህ ከሚልቁት የውጪ ቋንቋዎች መካከል ለሀገራችን ቋንቋዎች ብዙ ቃላትን ለማውረስ የበቁት አራቱ ብቻ ናቸው፡፡ እነርሱም ዐረብኛ፣ ፈረንሳይኛ፣ ጣሊያንኛና እንግሊዝኛ ናቸው፡፡ የቱርክ እና የጀርመን ቋንቋዎችም ጥቂት ቃላትን ለሀገራችን ቋንቋዎች አበርክተዋል፡፡ ***** ዐረብኛ በሀገራችን ቋንቋዎች ላይ ተጽእኖ ለመፍጠር የቻለው በዋናነት የእስልምና ሀይማኖት የአምልኮና … [Read more...] about ትኩረት – ከውጪ ቋንቋዎች ለተወረሱ ቃላት
ከላይ ሆነን ስናይ
በቅርቡ የኣሜሪካ ፌደራል ኣቪየሽን ኣስተዳደር (FAA) በዓለም ላይ ለበረራ ኣደገኛ የሆኑትን መስመሮች በካርታው ላይ ከቦ ኣስጠንቅቆ የነበረ ሲሆን በሪፖርቱ ላይ እንደሚታየው እነዚህን ኣደገኛ ቦታዎች በሁለት ከፍሏቸዋል። ኣንደኛው መስመር ኣደገኛነት ያለው ክልል (potentially hostile region) ሲሆን ሁለተኛው ክልል ግን በረራን ጨርሶ የከለከለ(Flight prohibited) ክልል ነው። ኣደገኛነት ኣላቸው ተብለው ኣብራሪዎች ከግምት እንዲያስገቡ የተመከሩባቸው ክልሎች ኬንያ፣ ኣፍጋኒስታን፣ ኢራን፣ ሶሪያ፣ ማሊ፣ የመን፣ ኮንጎና ግብጽ ሲናይ ናቸው። የበረራ መስመር የተከለከለባቸው ኣካባቢዎች ደግሞ ዩክሬን ውስጥ ድኒፕሮፐትሮቭስክ (ይህ ኣካባቢ በሶቪየት ዮኒየን ጊዜ የኒውክሌር ማምረቻ ተቋም የነበረበትና በኣሁኑ ሰዓት ደግሞ በራሽያ የሚደገፉ ገንጣዮች የሚንቀሳቀሱበት ክልል … [Read more...] about ከላይ ሆነን ስናይ
የሴት ልጅ ግርዛት ጎጂ ወይስ ጠቃሚ?
ጥናታዊ ጽሑፍ! በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ አንዳች ጥናት ቢጤ ማድረጌን አምና በግብረ ሰዶማዊያን ጉዳይ ላይ በጻፍኩት ጽሑፍ ሳይቸግረኝ ጠቆም በማድረጌ ብዙኃን መገናኛዎችን የሚከታተሉ ሰዎች በኢሜይልና በስልክ በአካልም ጭምር በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ ያዘጋጀሁትን ጥናታዊ ጽሑፍ ለንባብ እንዳበቃላቸው እጅግ ወተወቱኝ፤ አይ ረጅም ነው ለመጽሐፍ እንጅ ለዚህ ዓይነት መስተንግዶ አይሆንም ረዘመ ትላላቹህ ብልም ሊቀበሉኝ አልቻሉም ጨቀጨቁኝ እንግዲህ ካልተውኝ ምን አደርጋለሁ ብየ አቀራረቡን ግን ለብዙኃን መገናኛ በሚሆን ቀየርኩትና ተዛማጅ የሆነ ጠቃሚና አስፈላጊ ጉጋይ አክየበት ጽፌላቹሀለሁ ያውላቹህ፡- ይሄንን ጥናት ያደረኩት ከስድስትና ከሰባት ዓመታት በፊት ነበር፡፡ በዚህ ጥናት ከ800 ያላነሱ ሰዎች በቀጥታ በሽዎች የሚቆጠሩ በተዘዋዋሪ የጥናቴ ግብአት በማድረግ ተጠቅሜያለሁ፡፡ ጥናቴን … [Read more...] about የሴት ልጅ ግርዛት ጎጂ ወይስ ጠቃሚ?
አዲስ አበባን የተጫናት ፍልሰት
ዕቃ የጫኑ ታክሲዎችና ሌሎች መኪናዎች በሚያራግፉባቸው ማቆሚያዎች ሰብሰብ ብለው ሮጠው ዕቃ ማውረድ፣ ከሚጫንበት ስፍራም መጫን የለት ተዕለት ሥራቸው ነው፡፡ አሠሪዎች በተለይም በግንባታው ዘርፍ ያሉት የቀን ሠራተኞችን ከሚወስዱበት መገናኛ፣ ሃያሁለት፣ መሪ ሳሪስ አየር ጤናና ሌሎችም ሥፍራዎች በጠዋቱ ተሰባስበው መታየታቸው አመሻሽ ላይም በየሃይገሩና ባሱ ተጨናንቀው ወደየማደሪያቸው መጓዛቸውም እንዲሁ፡፡ ታዳጊ አዋቂ ሳይል በየገበያ ስፍራው የሸክም አገልግሎት ለመስጠት የሚሯሯጡትም ጥቂት አይደሉም፡፡ በመልካም አስተዳደር እጦትም ይሁን ከራስ በመነጨ ፍላጐት ትምህርት አቋርጠውና በእርሻውም ሆነ በሌላው የሚያግዙዋቸውን ቤተሰቦቻቸውን ትተው ወደ አዲስ አበባ የሚነጉዱት የየክልሉ ነዋሪዎች ተበራክተዋል፡፡ በዋና ዋና መንገዶች፣ በአደባባዮችና በትራፊክ መብራቶች፣ በእምነት ሥፍራዎች በማሳለጫ … [Read more...] about አዲስ አበባን የተጫናት ፍልሰት
ESFNA Held its 31st Tournament at FIFA Legalized Field
“A good leader can engage in a debate frankly and thoroughly, knowing that at the end he and the other side must be closer, and thus emerge stronger. You don't have that idea when you are arrogant, superficial, and uninformed” said Nelson Mandela, the late anti–apartheid icon. On an American football (football) field, the ESFNA held its 31st soccer tournament at San Jose City College (SJCC), San Jose, California. According to Wikipedia, “during the 1970s, SJCC was a major training hub for … [Read more...] about ESFNA Held its 31st Tournament at FIFA Legalized Field
የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌዴሬሽን 12ኛው ዓመታዊ በዓል በምዩኒክ ከተማ ጀርመን ተጠናቀቀ
የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌዴሬሽን 12ኛው ዓመታዊ በዓል በምዩኒክ ከተማ ጀርመን ክጁላይ 30 ቀን 2014 ዓ..ም. እስከ ኦገሰት 2 ቀን 2014 ዓ.ም በፕሮግራሙ መሰረት ተካሂዶ ተጠናቁኣል፡፡የተለያዩ ስፖርታዊ ዝግጅቶች የአዋቂዎች 28 ቡደኖች ሲዝጋጁ 25ቱ በ1ኛ ዲቪዚዮንና ሰባቱ ደግሞ በ2ኛ ድቪዚዮን ሲመደቡ፤ በ1ኛው ድቪዚዮን 25ቱ ቡደኖች በኣራት ግሩፕ እንዲከፈሉ ተደርገዋል፡፡ በሁለተኛው ድቪዚዮን ሰባቱ ቡድኖች በሁለት ግሩፕ ሆነው ተዘጋጅተዋል፡፡ሁለት ቡድኖች እንዳልመጡና እነርሱም ስዊድንና ኢትዮ ፍራንስ መሆናችው ተነግሯል፡፡ (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about የኢትዮጵያውያን የስፖርትና ባህል ፌዴሬሽን 12ኛው ዓመታዊ በዓል በምዩኒክ ከተማ ጀርመን ተጠናቀቀ










