• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ለሁላችንም የሚበጅ የተባረከ የእርቅ አስተሳሰብ

September 14, 2014 02:42 am by Editor 1 Comment

እንግዲህ ያረጀ የአመፅ ታሪክ ከመድገም፤ ከውጭ አገር መፍትሔ ከመኮረጅና፤ እልከኛና አንገተ ደንዳና ሆነን ለአዲሱ ጤናማ ኢትዮጵያዊነት አስተሳሰብ የማንመች ከመሆን ይጠብቀን።

በአይነቱ ኢትዮጵያዊ የሆነውንና የኛው በኛው ለኛው ሆኖ የሚያኮራንን አዲስ የእርቅና የመግባባት ስሌትን መፍጠር እንችላለን የሚል አስተሳሰብ ይኑረን። እንቆቅልሻችንን እንፍታና የአገር ልጅነት ግዴታችንን በታማኝነት እንወጣ። በተቃራኒ የፖለቲካ አስተሳሰብ የተከፋፈልን ህዝብ ብንሆንም፦ ጥላቻና ንቀትን አስወግደን፤ ሁለቱም ጎራ (መንግስትና ተቃዋሚ) በጡንቻ መጠቀምን እንደ ኋላቀርነት ለመቁጠር የሚያስችል ብስለትና ድፍረት ይታይብን።

በብዙ የተለያየ ባህልና ቋንቋ የበለፀግን ህዝብ ነን። የምንከባበርበትና በእኩልነት የምንተያይባት አዲሲቷን ኢትዮጵያ በልዩነታችን እንደ አንድ ቤተሰብ በመሆን ለመገንባት እንድንችል ትህትናና ፍቅር ይብዛልን። በእርቅና በመግባባት ጥበብ ፈውስን ለምድራችን ማምጣት እንችላለን የሚል አመለካከት ምርጫችን ይሁን። ከልብ ተሳስረን እውነተኛውን ማንነታችንን እንድናውቅና እንድንለማመድ በአዲስ መንፈስ ዛሬ እንነሳ።

የተለያየ ሀይማኖት የምንከተል ህዝብ ብንሆንም አንዳችን የሌላኛውን ሀይማኖት የምናከብር ህዝብ ነን። ከዚህም ባለፈ መልኩ ሁላችንም የሁላችንም የሆነችውን ኢትዮጵያን ፈጣሪ እንዲባርካት የዘወትር ፀሎታችን ይሁንልን። የኢትዮጵያም አምላክ ተአምር ሊያሳየን ይቻለዋል የሚል ግንዛቤ ያቀራርበናል ደግሞም ተስፋችንን ያለመልማል።

በፊታችን ያለውን የአዲስ ዓመት ጉዞ በቀና አስተሳሰብ እንጀምር። ይቻላል እንበል። ዋጋ ያስከፍላል እንጂ የማይቻል ነገር የለምና። ወደ ልባችን እንመለስና በይቅርታ ሌላውን ለመድረስ እንዘርጋ። አስተዋዩና ታጋሹ ፍቅር በምድራችን እንዲያሸንፍ እንፍቀድለት! እባክዎን ስለ እርቅ የተዘጋጀውን ባለ አምስት ነጥብ ብቻ የዳሰሳ ጥናት ወደዚህ ድህረ ገፅ በመሄድ ይሳተፉ።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. dereje says

    October 21, 2014 07:43 pm at 7:43 pm

    እዚህ ፎቶ ላይ የምናያቸው ልጆች ሙሉ በሙሉ የሀበሻ መልክ አላቸው። እንግዴህ እነዚህን ልጆች ምናቸውን አይተንና ለይተን ነው? አንቺ ኦሮሞ ነሽ፤ አንቺ ትግሬ ነሽ ፣እንቺ አማራ ነሽ ፣አንቺ አፋር ነሽ……ወዘተ የምንላቸው? ሁሉም እኮ ሀበሾች ጥቁሮች ናቸው። ሁሉም እኮ የድሀ ልጆች ናቸው። ሁሉም ድሀ ሆኖ እኛ ወርቅ ነን ሌላው አናሳ ነው ከተባባልን ከዝንጀሮ ቆንጆ የሚሉት ተረት ሊመጣ ነው። ዋነኛው ጠላታችን እኮ ድህነት ነው።ጎሣን የሚወስነው እኮ ያደግንበት አካባቢ እንጂ ወላጅ አይደለም። ይህ እውነት ደግሞ አቶ መለስ ካሉት ” ጎሣ ወይም ዘር በአባት ይወሰናል” ካሉት አባባል ጋር ይጋጫል። ከእውነት ጋር የሚጋጭ ደግሞ ራሱ ይስበራል እንጂ እውነትን ሊቀይራት አይችልም። ለዛም ነው ከእውነት ጋር የተጋጨው የኢህአድግ የዘረኝነት አካሄድ ህዝቦችን እያጋጨ ያለው። እናም ኢህእዲግ ይህ አካሄዱ ትክክል ስላይደለ ይህ አካሄዱን ትቶ ክሌሎች ጋር ቢማከር አገራችን ውጤታማ ትሆናለች።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule