የትግሬ ወያኔ በኃሣብ፣ በዕቅድ እና በተግባር ፀረ-ዐማራ፣ ፀረ-ኢትዮጵያ እና ፀረ-ኢትዮጵያዊ የሆነ ድርጅት መሆኑን ከተፈጠረበት ጊዜ ጀምሮ ያረጋገጠው ሃቅ ነው። ሠሞኑንም ከመገናኛ ብዙሃን የሚደመጠው «የትግራይ ድንበር አል-ውሃ ድረስ ነው» የሚለው ወሬ የዚሁ የሚጠበቀው የትግሬ-ወያኔ ተከታይ እርምጃ እንደሆነ አያጠያይቅም። ኢትዮጵያን የማፈራረሱ የንድፈ-ኃሣብ መሠረት የተጣለው በተለያዩ የውጭ ኃይሎች እንደሆነ ይታወቃል። ከእነዚህ መካከል ሮማን ፕሮቻዝካ የተባለው የኦስትርያ-ሐንጋሪ መሥፍን (Baron Roman Prochazka) ወጥነት ባለው መንገድ አዘጋጅቶ ያሠራጨው መጽሐፍ ዋና ተጠቃሽ ነው። የሮማን ፕሮቻዝካ መጽሐፍ ኢትዮጵያ በፋሽስት ጣሊያን በተወረረችበት በ፲፱፻፳፰ ዓ.ም. (1935 G.C.) በጀርመንኛ ቋንቋ «Abessinien: die schwarze Gefahr» በሚል ርዕስ፣ … [Read more...] about ምን እየጠበቅን ነው?
Right Column - Primary Sidebar
ግልጽ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት
እጅግ ለተከበሩ ለብፁዕ አቡነ ብርሃነ-ኢየሱስ ደምረው ሱራፌል የኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት፤ የኢትዮጵያ ጳጳሳት ጉባኤ ፕሬዚዳንትና የምሥራቅ አፍሪካ የካቶሊክ ቤ/ክ ማሕበር ሊቀ መንበር፤ አዲስ አበባ፤ ኢትዮጵያ። በመጀመሪያ፤ ለብፁዕነትዎ የሚገባ እጅግ ከፍ ያለ የአክብሮት ሰላምታ አቀርባለሁ። በተጨማሪም፤ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በደህና፤ በክብርና በሞገስ አደረሰዎ በማለት መልካም ምኞቴን በትሕትና እገልጻለሁ። በመቀጠልም፤ ሰሞኑን የ1.228 ቢሊዮን የካቶሊክ እምነት ተከታዮች ባላት የካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን፤ እጅግ የተከበሩ ብፁዕ ሊቀ ጳጳሳት (ካርዲናል) ሆነው በመሾምዎ፤ እንኳን ደስ አለዎ በማለት፤ ለዓለም ሰላምና ለክርስቲያን አንድነት የሚያደርጉት ጥረት በቸሩ አምላክ ተራዳኢነት እንዲሳካልዎ ልባዊ ጸሎታችንን በትሕትና እናቀርባለን። የብፁዕነትዎ … [Read more...] about ግልጽ ደብዳቤ ለኢትዮጵያ ካቶሊካዊት ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳሳት
“ልማት ስለሌለ ልጆቻችን ስደተኞች ሆነዋል”
የከምባታ ህዝብ ሆን ተብሎ መሰረተ ልማት እንዳይገነባለት በመደረጉና በተራድኦ ድርጅቶች የተሰሩት መሰረተ ልማቶች ስራ ላይ እንዳይወሉ በደኢህዴን ከፍተኛ አመራሮች እየተፈፀመበት የሚገኘውን በደል በመቃወም የካቲት 3/2007 ዓ.ም በዱራሜ ከተማ ደማቅ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረጉን የከምባታ ህዝቦች ኮንግረንስ ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርዴሎ ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በሰልፉ ወቅትም ነዋሪዎቹ መንግስት ለአካበቢው ምንም አይነት ትኩረት ባለመስጠቱ 10 ከተሞች ላይ መብራት በራሳቸው ገንዘብ ማስገባታቸውን፣ ትምህርት ቤቶችን ራሳቸው እንደሰሩ፣ ቴሌኮሚኒኬሽን የተዘረጋው በህዝቡ ወጭ መሆኑን፣ መንግስት ሰራሁት ያለው ውሃ ከሶስት ሳምንት በኋላ መበላሸቱ ሙስና እንደተበላበትና እንዳልተሰራ እንደሚያምኑ ቅሬታቸውን ገልጸዋል፡፡ ሰልፈኞቹ "ልማት ስለሌለ ልጆቻችን ስደተኞች ሆነዋል፣ ስራ አጥተው … [Read more...] about “ልማት ስለሌለ ልጆቻችን ስደተኞች ሆነዋል”
በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ዲፕሎማቶች የስደተኞችን ሻንጣ ዘረፉ!
ከአንድ አመት በፊት የሳውዲ አረቢያ መንግስት በህገወጥ መንገድ የሚኖሩ የውጭ ሃገር ዜጎች ግዛቱን ለቀው እንዲወጡ ያስቀመጠው የግዜ ገደብ መጠናቀቁን ተከትሎ አያሌ ኢትዮጵያውያን ጅዳ እና ሪያድ ከተማ ወደሚገኙ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግቢ መጉረፋቸው ይታወሳል። በወቅቱ ከነበረው ስርዓት አልበኝነት ህይወታቸውን ለመታደግ አቅሙ የቻለ ጎረምሳ ልብሶቹን በሻንጣ አጭቆ እግር አውጭኝ ሲል አይን ያልገለጹ ህጻናት ልጆቻቸውን በወጉ መሰብሰብ ያልቻሉ እናቶች ለክፉ ቀን ትሆነኛለች ብለው ገዝተው ያስቀመጡጥን ወርቅ እና የተለያዩ ጌጣጌጦቻቸውን የያዘች አነስተኛ ሻንጣ አንጠልጥለው ከቀማኞች ይታደገናል ወዳሉት በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ቅጠር ግቢ በማቅናት ለተውሰኑ ቀናቶች በመጠለል ሻንጣዎቻቸው በካርጎ ጭነት እንደሚላክ ቃል ተገብቶላቸው ብጣሽ ጨርቅ እንኳን ሳይዙ ባዶ እጃቸውን ወደ ሃገር … [Read more...] about በጅዳ የኢትዮጵያ ቆንስላ ጽ/ቤት ዲፕሎማቶች የስደተኞችን ሻንጣ ዘረፉ!
“ፍቅር እስከ መቃብር” በሰሜን ዋልታ
ዶክተር ሬዶልፍ ክኑት ሞልቨር (Reidulf Knut Molvær) የ77 ዓመት ኖርዌጂያዊ አዛውንት ናቸው። ዋና ሙያቸው የሥነ ጥሑፍ፣ የቋንቋ፣ የታሪክና የማህበራዊ ሳይንስ ተመራማሪነት ነው። በአማርኛ ሥነ ጽሁፍና ቋንቋ ጥናት ከሎንዶን ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት ድግሪያቸውን ያገኙ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ 14 ኬንያ ውስጥ ደግሞ 6 ዓመታትን ባለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ በመሥራት አሳልፈዋል። የትዳር ጓደኛቸው ኬንያዊት ሲሆኑ፣ አራት ልጆችም በጋራ አፍርተዋል። ከልጆቻቸውም መካከል አንዱ የሕክምና ዶክተር፣ ሁለቱ ኢንጂነሮች ሆነዋል። ዶ/ር ሞልቨር ለፍልስፍና ማስትሬት ድግሪያቸው መመረቂያ አዘጋጅተውት የነበረው ጥናታቸው ቀዳሚውን እውቅና አስገኝቶላቸው የነበረ ነው። ይህን ጥናታቸውን “ልማድና ለውጥ በኢትዮጵያ - Tradition and Change in Ethiopia: Social and … [Read more...] about “ፍቅር እስከ መቃብር” በሰሜን ዋልታ
ላልቀረልን ሀገርንና ሕዝብን የመታደግ ትግል ተነሡ!
ሥልጣንን ይዞ ሀገርንና ሕዝብን ለማሥተዳደር ሁለት የትግል አማራጮች አሉ፡፡ በሀገራችን ሁለቱም ዓይነቶች በሚገባ ይታወቃሉ ተሞክረዋልም፡፡ አንደኛው ሕዝብ በሚያደርገው ምርጫ የመንግሥትነት ሥልጣንን መያዝ መሠረቱ ያደረገው ሰላማዊ የትግል አማራጭ ሲሆን፡፡ ሁለተኛው ደግሞ ይህ ሰላማዊ የትግል አማራጭ ዝግ ሲሆን ወይም ሊሠራ በማይችልበት ጊዜ በሕዝብ ላይ በኃይል የተጫነን አንባገነን አገዛዝን በኃይል ለማስወገድ የሚደረግ የኃይል እንቅስቃሴዎችን መሠረቱ ያደረገ የትጥቅ ወይም የዐመፅ የትግል አማራጭ ነው፡፡ እስኪ ሰላማዊው የትግል አማራጭ በዘመነ ወያኔ ምን እንደሚመስል በአጭሩ ዕንይ፡፡ ወያኔና ምርጫ፡- በዘመነ ወያኔ ምርጫ እየተባለ ለአራት ጊዜያት ያህል በሕዝብና በሀገር ላይ ከባድ ቀልድና ሹፈት ሲቀለድና ሲሾፍ ሲፌዝ ተቆይቷል አሁን ደግሞ ለአምስተኛ ጊዜ እየተሾፈና እየተቀለደ … [Read more...] about ላልቀረልን ሀገርንና ሕዝብን የመታደግ ትግል ተነሡ!
The Charities and Societies Proclamation and its impact on human rights and women’s rights activism in Ethiopia
Four years after a draconian law stymied the work of civil society associations in Ethiopia, it has remained imperative to search for ways and means of the public making its input towards ensuring its entitlement to human rights, needs satisfaction and human development Ethiopia passed the Charities and Societies Proclamation (CSP), (No.621/2009), in February 2009 to regulate the work of civil society organizations in the country. This Law classified Ethiopian organizations into Charities or … [Read more...] about The Charities and Societies Proclamation and its impact on human rights and women’s rights activism in Ethiopia
Xenophobic attacks escalate as feeling of hatred sweeps South Africa
“In Russia, bread riots led to a revolution, here (in South Africa) they lead to xenophobia.” Nomalanga Mikize, on Twitter A nation in cantankerous mood and truculent society baying for blood. The air is thick with terror and despair of foreign nationals living and working in one of the world’s racially intolerant nations, South Africa. Collectively known as Makwerekwere-a derogatory term for black African immigrants and Onomatopoeia-for other non-nationals who speak unintelligibly, life in … [Read more...] about Xenophobic attacks escalate as feeling of hatred sweeps South Africa
የደደቢት ጉዞ መዘዝ፤ ከሰራዊት ፍቅሬ እስከ ታገል ሰይፉ
በመጀመርያ ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ደጋፊና ተደጋፊ የኪነጥበብ ባለሙያዎችን በሙሉ ጠሯቸው። ሰበሰቧቸው። እንዲህም አሏቸው። "ወደ ደደቢት አብራችሁን ትሄዳላችሁ፤ እዛ እንደደረሳችሁም አመጣጣችንንና አካሄዳችንን በደንብ አድርጋችሁ ታጤናላችሁ። ከዚያ ስትመለሱ ሁሉንም ነገር ለህዝቡ ትናገራላችሁ።..." በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የሃገር መሪ ሆነው የሚሰሩት እኝህ ሰው መልዕክታቸውን በዚህ አላበቁም። አይናቸውን ፈጠጥ፤ ጉሮሯቸውንም ጠረግ-ጠረግ አደረጉና ንግግራቸውን ቀጠሉ "ስለረጅሙና መራራው ትግላችን፤ ከጅምራችን እስከ አያያዛችን የታዘባችሁትን ሁሉ ንገሩን። ጥሩውንም ይሁን መጥፎውን ነገር ሳትደብቁ ተናገሩ።..." ድምጻዊው በዝማሬ፣ ጸሃፊው በድርሰት፣ ተዋንያኑ በተውኔት ስለ ህወሃት የአርባ አመት ጉዞ እንዲመሰክሩ የተሰጠች … [Read more...] about የደደቢት ጉዞ መዘዝ፤ ከሰራዊት ፍቅሬ እስከ ታገል ሰይፉ
የሐመር አርብቶ አደሮችና የፖሊስ ግጭት ወቅታዊ መረጃ
በጥር 7/2007 ሐሙስ ዕለት በሐመር ወረዳ በ"ላላ" ቀበሌ በሐመር ብሔረሰብ አርብቶ አደሮችና ፖሊስ መካከል በተፈጠረ ግጭት የደረሰዉ ጉዳት የሚከተለዉን ይመስላል፤ ሀ/ የሞቱ-- 1. ሻምበል ለማ አሸናፊ 2/ ወ/ር ሙሴ ማቱሳላ 3/ ወ/ር ደፋሩ ጦና 4/ ወ/ር ካሬ 5/ ወ/ር በኃይሉ 6/ ስሙ ለግዜዉ ያልታወቀ የልዩ ኃይል ባልደረባ 7/ ስሙዋ ለግዜዉ ያልታወቀ ሴት ባለሙያ 8/መምህር መሳይ ነሽ መርነህ ለ/ የቆሰሉ 1/ አቶ ቹሜሬ የረር /የደቡብ ኦሞ ዞን ፍትህ ጸጥታና ደንብ ማስከበር ምክትል ሀላፊ 2/ ምክትል ሣጅን ጌታሁን ቶላ 3/ ወ/ር ተሰማ መሰረት 4/ ወ/ር ጌታቸዉ ጻንቃ 5/ ወ/ር ቱላ ኪያ 6/ ባሻ ወንድማገኝ ጨነቀ 7/ ወ/ር ሚልኪያስ ግራኝ 8/ ወ/ር ዘለቀ (አባታቸዉ ያልታወቀ) 9/ አቶ ደምሳሽ ሞላ (የዞኑ ሴቶችና ሕጻናት መምርያ … [Read more...] about የሐመር አርብቶ አደሮችና የፖሊስ ግጭት ወቅታዊ መረጃ










