• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ፍቅር እስከ መቃብር” በሰሜን ዋልታ

February 9, 2015 07:07 am by Editor 1 Comment

ዶክተር ሬዶልፍ ክኑት ሞልቨር (Reidulf Knut Molvær) የ77 ዓመት ኖርዌጂያዊ አዛውንት ናቸው። ዋና ሙያቸው የሥነ ጥሑፍ፣ የቋንቋ፣ የታሪክና የማህበራዊ ሳይንስ ተመራማሪነት ነው። በአማርኛ ሥነ ጽሁፍና ቋንቋ ጥናት ከሎንዶን ዩኒቨርስቲ የዶክትሬት ድግሪያቸውን ያገኙ ሲሆኑ፣ ኢትዮጵያ ውስጥ 14 ኬንያ ውስጥ ደግሞ 6 ዓመታትን ባለም አቀፍ ድርጅቶች ውስጥ በመሥራት አሳልፈዋል። የትዳር ጓደኛቸው ኬንያዊት ሲሆኑ፣ አራት ልጆችም በጋራ አፍርተዋል። ከልጆቻቸውም መካከል አንዱ የሕክምና ዶክተር፣ ሁለቱ ኢንጂነሮች ሆነዋል።

ዶ/ር ሞልቨር ለፍልስፍና ማስትሬት ድግሪያቸው መመረቂያ  አዘጋጅተውት የነበረው ጥናታቸው ቀዳሚውን እውቅና አስገኝቶላቸው የነበረ ነው። ይህን ጥናታቸውን “ልማድና ለውጥ በኢትዮጵያ – Tradition and Change in Ethiopia: Social and Cultural Life as Reflected in Amharic Fictional Literature ca. 1930-1974” በሚል አቢይ ርእስ ስር አስቀምጠው ባለ 365 ገጽ መጽሐፍ እ.አ.አ. በ1980 ዓ.ም- አሳትመው አውጥተዋል። ይህ የበኩር ሥራቸው የብዙ አንባቢያንንና ተመራማሪዎችን ቀልብ የሳበ ሆኖ እስከዛሬ ድረስ ዘልቋል። ለጥቀውም ”ማኅበራዊነትና ማኅበራዊ ቁጥጥር በኢትዮጵያ – Socialization and Social Control in Ethiopia” እ.አ.አ. በ1995 ዓ.ም. አንድ ዳጎስ ያለ መጽሐፍ ለንባብ አብቅተዋል።

ከዚህ ሥራቸው ቀጥለውም በእንግሊዝኛ ቋንቋ “Black Lions – The Creative Lives of Modern Ethiopia’s Literary Giants and Pioneers” በሚል ርእስ የመጀመሪያውን የ33 ኢትዮጵያውያን ደራስያንን ሥራና የሕይወት ታሪክ ያካተተ መጽሐፍ እ.አ.አ. በ1997 ዓ.ም. ላይነ ንባብ አብቅተዋል። ይህም ድንቅ ሥራቸው በዚህ ረገድ የነበረውን የመረጃ እጥረት ክፍተት ለመሸፈን ከፍተኛ እገዛ አድርጓል። ከብላቴን ጌታ ሕሩይ ወልደ ሥላሴ እስከ እኔ ትውልድ ያሉትን ተጠቃሽ ጸሐፍት አካተውበታል።

ሰንበት ብለውም በዚሁ መድበላቸው ውስጥ ያልተካተቱትነ የሁለት እውቅ ኢትዮጵያውያን የሕይወት ታሪኮችና ሥራዎቻቸውን ”የሰሜን ምሥራቅ አፍሪካ ጥናት- Northeast African Studies” በተሰኘ ታዋቂ  ጁርናል ላይ አቅርበው አስነብበዋል። እኒህም ሁለት እውቅ ደራስያን ሻምበል  አፈወርቅ ዮሐንስና ደራሲ ደበበ ሰይፉ ናቸው።

ቀጥለውም የተለያዩ ጥናታዊ ጽሑፎችን በኢትዮጵያ ሥነ ጥሑፍ፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ማህበራዊ ሳይንስ ዙሪያ እያዘጋጁ በተለያዩ ጉባዔዎችና ጁርናሎች ላይ አቅርበዋል። አሁን በቅርቡ በሐምሌ ወር 2014 ዓ.ም. ደግሞ የክቡር ዶ/ር ሀዲስ ዓለማየሁን ዝነኛውን ያገራችንን ረዥም ልቦለድ መጽሐፍ ”ፍቅር እስከ መቃብር”ን ወደ ኖርዌጂያንኛ ቋንቋ “Kjærlighet til graven” በሚል ርእስ ተርጉመው፣ ለንባብ አብቅተዋል። ይህ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ የተተረጎመው ሥራቸው 607 ገጾች ያለው ሲሆን፣ በኖርዌጂያን አንባቢያን ዘንድ ትልቅ ተነባቢነትንና ተቀባይነትንአግኝቶላቸዋል።

ዶ/ር ሞልቨር ለዚህ ድንቅ ሥራቸው ክብርና ሞገስ ሊሰጣቸው የሚገባችው ታታሪ ሰው ናቸው። ”ፍቅር አስከ መቃብር” ከዚህ ቀደም ወደ ራሽያንና ወደ እንግሊዝኛ ቋንቋዎች መተርጎሙ ይታወሳል። አሁን ደግሞ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ መተርጎሙ፣ በሰሜን ዋልታ የእስካንዲኔቪያን አገሮች ቋንቋዎች የመተርጎም እድሉን ከፍ ያድርገዋል። ይሄውም ወደ እስዊድንኛ፣ ዳንማርኪኛ፣ ፊንማርኪኛና ሳሚኛ ቋንቋዎች የመተርጎም እድሉ ሰፊ ነው። ዶ/ር ሞልቨርን ሳወያያቸው በቀጣይነት ስላሰቧቸው የትርጉም ሥራዎቻቸው ጠይቄያቸው ነበር። ከአማርኛ ሥነ ጽሑፎች ውስጥ የብላቴን ጌታ ማህተመ ሥላሴ ወልደ መስቀልን “እንቅልፍ ለምኔ” ፣ የአፈወርቅ ገብረ ኢየሱስን ”ጦቢያ”፣ የደጃዝማች ግርማቸው ተክለ ሐዋሪያትን ”አርአያ”፣ ከኬንያ ሥነ ጽሑፍ ደግሞ የንጉጊ ዋቲያንጎን “Grain of Wheat” ለመተርጎም ከጀመሯቸውና በእቅድ ከያዟቸው ሥራዎች መካከል እንዳሉ አጫውተውኛል። የታዋቂውን ኬንያዊ ደራሲ የንጉጊን መጽሐፍ እንዲተረጉሙ የግድ ሰበብ የሆናቸውም ለሥነ ጽሑፍ የኖቤል ሽልማት እጩ ሆኖ እንዲቀርብ ስለታሰበ፣ ከወዲሁ በኖርዌጂያን አንባቢያን ዘንድ እውቅናውን ለማጠንከርና መንገዱንም ለመጥረግ እንዲያመች እንደሁ ዶ/ር ሞልቨር አልሸሸጉኝም። እኒህ ይበልጡኑ በኢትዮጵያ ሥነ ጥሑፍ፣ ቋንቋ፣ ታሪክና ማህበራዊ ሳይንስ ዙሪያ ጥብቅ ምርምር ሲያደርጉ የኖሩ ሰው፣ ከዚህ ቀደምም አንድ በኪስዋህሊ ቋንቋ የተጻፈ የኬንያ ሥነ ጽሑፍ ወደ ኖርዌጂያን ቋንቋ መተርጎማቸውም ይታወቃል።

ከዶ/ር ሞልቨር ተጨማሪ ሥራዎች መካከል እነዚህም ይገኙባቸዋል

ዶ/ር ሞልቨር ለኢትዮጵያውያን ደራስያንና የቀለም ሰዎች ታላቅ አክብሮትና ፍቅር ያለቸው ሰው መሆናቸውም የሚሰመርበት ጉዳይ ነው። እ.አ.አ. በ2005 ዓ.ም. ባለቅኔ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድኅንን ለኖርዌይ ደራስያን ማኅበር “ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ ሽልማት” እጩ ተወዳዳሪ አድርጌ ባቀረብኩበት ሰዓት ከጎኔ ከሞቆማቸውም በላይ፣ በቀጣዩ ዓመት ሎሬት ጸጋዬን ለኖቤል ሽልማት እጩ አድርጎ ለማቅረብ፤ ከእኔና ከጋሼ ኃይሉ ገብረ ዮሐንስ (ገሞራው) ጎን ለመሰለፍ ቃል ገበተውልን የነበሩ ናቸው። በሎሬት ጸጋዬ እረፍት ምክንያት ያሰብነው ሳይተገበር በውጥን ቀርቷል።

ዶ/ር ሞልቨር በጅምር የያዙዋቸውን ሥራዎች ጨርሰው ለኖርዌጂያን አንባቢያን አቅርበው ለማስነበብ እንዲያበቃቸው ምኞቴ ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. BELIYU BERHANU says

    October 13, 2017 01:01 pm at 1:01 pm

    IT IS VARY GOOD

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule