ቴዲ በክርስቶስ ተቦርነም በጲላጦስ እንዲት ይመሰላሉ? ምሳሌያዊ አነጋገሮች ተረቶቻች፣ የታላላቅ ሰዎች አባባሎች መጽሐፍትና ገጠመኞች እየተጠቀሱ ንግግር መክፈቻም ሆነ የጽሁፍ መነሻ መሆን በፊትም የነበረ አሁንም የቀጠለ የተለመደ ነገር ነው። እንደዚሁም የክርስቶስ ቃል የሀዋርያት ትንቢት ምሳሌና ተግሳፅም እንደቦታው አስፈላጊነት የሚጠቀስበት ጊዜ አለ። ይህም የሚሆነው ትምህርት ለመስጠት የእግዚአብሔርን ቃል ለመስበክ እንደአስፈላጊነቱም ጊዜውና የተፈጸመውን ድርጊት ለማስተማር ነው። በሰርግ ጊዜ ጌታ በሰርግ ቦታ ተገኝቶ ባዶዎቹን እንስራዎች በጣፋጭ ወይን ሞላቸው ተብሎ ትምህርት እንደሚሰጠው። አንተም ለጽሁፍህ መነሻ ያደረከው ቃል በማትዮስ ወንጌል ምዕራፍ ፳፯ ቁጥር ፲፩. ሰፍሮ ይገኛል። ቃሉም እንደሚያስረዳው እየሱስ በዛን ጊዜ ይሁዳ አሳልፎ ስጥቶት ሽማግለዎችና የካህናት … [Read more...] about ክንፉ ምን ነካህ?
Right Column - Primary Sidebar
ገድለህ ማረው
የሰራህን በዓይንህ አይተህ ሲወሻክት ወይም ሰምተህ ልታቆመው ብትነሳ በዝምታ ፊት ብትነሳ አፍሮ ይተው እንዳይመስልህ ስምህን ነው ሚከትፍልህ ከዛ - ይልቅ ነገርህን አ’ርገህ ድብቅ ትንሽ ጊዜ ብትጠብቅ እንደወትሮው ሱሱን ሊያደርስ ካ’ንዱሊቀምስ ካ’ንዱ ሊልስ ከሰው ጋራ ሲቀላቀል ባልታሰበ የፊት ተንኮል ተይዞልህ ፊትህ ሲቀል መፋረጃህ ያን ጊዜ ነው ተቀላቅለህ አብረህ በለው ወይንም በዓይንህ ገድለህ ማረው (ወለላዬ ከስዊድን) … [Read more...] about ገድለህ ማረው
ተቦርነ በየነ “አንተ አልክ?” – ቴዲ አፍሮን
እንዲህም ሆነ። የይሁዳ ገዥ የነበረው ጲላጦስ ክርስቶስን አስጠርቶ "አንተ የአይሁድ ንጉስ ነህን?" ሲል ጠየቀው። ክርስቶስም መልሶ "አንተ አልክ?" አለው። ሰማይን ያለ ምሰሶ ያቆመው ክርስቶስ "ጥፋ" የምትል ቃል ብቻ ከአንደበቱ ቢያወጣ ኖሮ ጲላጦስ አይደለም መላው ቂሳር ክምድረ-ገጽ በጠፉ ነበር። ታዋቂዎች በአዋቂዎች ላይ የሚቀልዱበት ይህ የገሃዱ አለም እውነታ ግብረ-ገብ ወደ ግብግብ በተቀየረበት በዚህ ዘመን ባሰበት እንጂ አልጠፋም። ጥንት አንቺ-ትብሽ፣ አንተ-ትብስ ይባል የነበረው ብሂል አሁን በ“አንቺ ብስብስ አንተ ብስብስ” ተቀይሯል ሲል አንዱ አጫወተኝ። ከቶውንም ስድብን እንደ ስንቅ በከረጢት ቋጥረው በሚጓዙበት የፌስቡክ ዘመን መስመር የመልቀቁ ነገር አዲስ ሊሆን አይችልም። "አንተ አልክ?" ብሎ ማለፍ ምን ይጎዳል? ብላቴናው ላይ አንዳች እንከን ሲያጡ፣ የጠወለገን የጥላቻ … [Read more...] about ተቦርነ በየነ “አንተ አልክ?” – ቴዲ አፍሮን
ተደናቂ ለሆነ የፍትሕ አገልግሎት ስለ ተሰጠ ሽልማት
ጋዜጣዊ መግለጫ ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ - የኢትዮጵያ ጉዳይ ተደናቂ የሆነ የፍትሕ አገልግሎት በመፈጸማቸው ከዚህ ቀጥሎ ስማቸው ለተዘረዘሩት ሽልማት ያበረከተ መሆኑን ይገልጻል፤ ቀሲስ/ዶር. ምክረ-ሥላሴ ገብረ አማኑኤል፤በፋሺሽት ኢጣልያ የኢትዮጵያ ወረራ ዘመን ስለነበረው የቫቲካን ሚና ግንዛቤ እንዲገኝ በደረሱት መጽሐፋቸው አማካኝነት ስላበረከቱት አስተዋጽኦ፤ ሚር. ኢያን ካምፕቤል፤ ፋሺሽቶች በኢትዮጵያ ላይ ስለ ፈጸሙዋቸው የጦር ወንጀሎች በደረሱዋቸው መጽሐፎች ስላበረከቱት አስተዋጽኦ፤ ሚር. ቫሌሪዮ ቺሪያቺ፤ ፋሺሽት ኢጣልያኖች፤ በኢትዮጵያ ላይ ስለ ፈጸሙት የጦር ወንጀልና ባሁኑ ወቅት በመኪያሔድ ላይ ስላለው የፍትሕ ጥረት ግንዛቤ እንዲገኝ ፊልም በማዘጋጀት ስላበረከተቱት አስተዋጽኦ፤ አቶ ከባዱ በላቸው፤ ፋሺሽት ኢጣልያኖች፤ በቫቲካን የትብብር ድጋፍ፤ … [Read more...] about ተደናቂ ለሆነ የፍትሕ አገልግሎት ስለ ተሰጠ ሽልማት
“ጋንታይናው” ‹ጋትዬ› አሰፋ ጫቦ
እውቁ ፖለቲከኛና አንጋውፋ ምሁር አቶ አሰፋ ጫቦ አረፉ። አቶ አሰፋ በማራኪ ተናጋሪነታቸው እና አንደበተ ርቱዕነታቸው የሚታወሱ የሕግ ምሁር ነበሩ። ብዙውን እድሜያቸውን የጨረሱት በኢትዮጵያ ፖለቲካ እና በእስር ቤት ውስጥ ነው። አሜሪካ ከገቡ በኋላ በ20 ግዛቶች እየተዘዋወሩ ኖረዋል። በቅርቡ ባሳተሙት የ”ትዝታ ፈለግ” መጽሃፋቸው ለረጅም ግዜ በአንድ ቤት የተቀመጥቁት እስር ቤት ውስጥ ብቻ ነው ሲሉ አስነብበውናል። በአንድ ቤት የተቀመጥቁት እስር ቤት ውስጥ ብቻ ነው ሲሉ አስነብበውናል። እኚህ ምሁር በደረሰባቸው ህመም ዳላስ-ቴክሳስ በሚገኝ ሆስፒታል ህክምና ሲክታተሉ ቆይተው በዛሬው እለት (እሁድ) ከዚህ አለም በሞት ተለይተዋል። ጣይቱ የባህልና የትምህርት ማህከል አሰፋ ጫቦን እረፍት አስመልክቶ የሚከተለውን የሃዘን መግለጫ አውጥቷል። አቶ አሰፋ ጫቦ ከአባቱ ከጫቦ ሣዴ ሃማ ያሬና … [Read more...] about “ጋንታይናው” ‹ጋትዬ› አሰፋ ጫቦ
ወንዙ እና ዛፉ
ስርሽን አየሁት ቁልቁል ተዘርግቶ፣ ረዝሞ ተባዝቶ፣ አንድ አንቺን ሊያሳድግ፣ አንድ አንቺን ሊያቀና፣ እጅግ ተበራክቶ፣ በዚህ ከቀጠለ የጉዞ ርዝመቱ፣ ውፍረት ከጨመረ፣ ካደገ ቁመቱ፣ ወንዙ አንጀቱ ታልቦ፣ መቅኒው ተመጥምጦ፣ አፅመ ወዙ ደርቆ፣ ደም ውሃው ተመጦ፣ መላ አካሉ ፈርሶ እርቃኑን ተጋልጦ፣ ባዶ መቅረቱ ነው ድንጋይ ጥርሱ ገጦ፣ ወለላዬ ከስዊድን (welelaye2@yahoo.com) … [Read more...] about ወንዙ እና ዛፉ
ለዴሞክራሲ አርበኞች ተባብሮ ለመታገል የሚያስችል ቀላልና ጠቃሚ ሃሳብ
አስቀድሞ የከበረ ሰላምታ ይድረሳችሁ፤ በዚህ ማስታወሻ የቀረበውን ሃሳብ ጠቃሚ ነው የምትሉ ስለጠቀሚነቱ፤ ጎጂ ነው የምትሉም ስለጎጅነቱ የሚታያችሁን ምክንያቶች ጨምራችሁ መልስ እንድትሰጡ ትጠየቃላችሁ፤ ሌሎች ይህ ሃሳብ ከተላለፈበት ዕለት ቀደም ብሎ ተደራጅታችሁ እንቅስቃሴ የጀመራችሁና በዚህ ዝርዝር ውስጥ ያልገባችሁ ካላችሁ ተቀላቅላችሁ ድምጻችሁን ማሰማት ትችላላችሁ። በጉዳዩ ላይ ድምጽ ለማሰማት ግለሰቦችም መብታችሁ የተጠበቀ ነው። መልስ ስትሰጡ ግን አድራሻችሁን ማኖር አትርሱ። የመልሱ ውጤት ከታየ በዃላ ቀጣይ ሂደት ይኖራ ተብሎ ተስፋ ይደረጋል። ለዚህ ጽሁፍ መነሻ፤- ከወራት በፊት አቶ ዘውዴ ጉደታ የተባሉ ወንድም "የኢትዮጵያ አገራዊ ንቅናቄ እና የአገር አንድነትን "ያገቱት" ሦስት ተጻራሪ ሃይሎች" በሚል ርዕስ አንድ ሰፋ ያለ ጽሁፍ አስነብበው ነበር። ከዚያም በላይ የጸሃፍያን … [Read more...] about ለዴሞክራሲ አርበኞች ተባብሮ ለመታገል የሚያስችል ቀላልና ጠቃሚ ሃሳብ
የበጋው መብረቅ (ሌፍተንት ጀነራል ጃጋማ ኬሎ)
. . . ጃጋማ በውጊያ ብቻ አልነበረም ብስለቱ በአስተዳደርም የተደነቀ ነበር።ለምሳሌ፤ከአምቦ መንገድ በላይ ያሉት ነዋሪዎች ጥራጥሬ እያዋጡ ቆሎ እየቆሉ ለአርበኛው ይረዳሉ፤ከአምቦ መንገድ በታች ያሉት ግን የጃገማ አርበኞች ሙጀሌ የወረሳቸው ሰለሆኑ ይህን የተሰነጣጠቀ እግራቸው ችሎ መራመድ አይችሉም፤ስለዚህ እንኳን እኛን ከኢጣሊያ ስራዊት ሊጠብቁን እና ሊከላከልሉን ቀርቶ ለራሳቸውም ሰለማይሆኑ በምንም ነገር አንረዳቸውም ማለታቸውን ጃጋማ ሰማ። ለሰራዊቱም ትእዛዝ ሰጥቶ ወደ ሃያ ሺህ ከብቶቻቸውን አስነዳባቸው፤ ህዝቡም በጣም ተደናግጦ ምነው ምላሳችንን በቆረጠው በሚል በጣም ተደናገጡ።ቀንበራቸውን ተሸክመው የጃጋማ ጦር የሰፈረበት ቦታ ድረስ በመሄድ እግዚኦ አሉ። ወጣቱ መሪ ጃጋማ እንዲህ አላቸው (እኛ ከእናንተ የወጣን የእናንተ ልጆች ነን፤ጠላት የሚንቀን አንሶ ለሐገራችንና ለእናንተ በባዶ … [Read more...] about የበጋው መብረቅ (ሌፍተንት ጀነራል ጃጋማ ኬሎ)
የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ ተስፋና ሥጋት!
ላለፉት ሁለት ዐሥርት ዓመታት በዘረኛው የትግሬ ነፃ አውጪ የአገዛዝ መዳፍ ሥር የታፈነውን ሕዝባችንን ወደ ነፃነትና የዴሞክራሲ ምዕራፍ ለማሸጋገር የጋራ ትግል ለማድረግ ሲሞከር ቆይቷል። ሆኖም በእነዚህ ዘመናት ውስጥ የተፈጠሩት የፖለቲካ ኃይሎች ትብብር፣ ቅንጅት፣ ኅብረት እና ውህደት አንዱም ከዳር ሳይደርስ እንዲሁ ሲሰበሰብና ሲበተን ከርሟል። እንደ አባባልም እንደ መታወሻም “ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ” የሚለው የዶ/ር መረራ ጉዲና መፈክር አንዱም ገቢራዊ ሳይሆን አብዛኞቹ የፖለቲካ ተቋማት በአገዛዙ ጫናና በራሳቸው ደካማ አደረጃጀት ህልውናቸው እየጠፋ ለሐገር የሚተርፍና ትውልድ የሚረከበው አንድም አግባቢ የጋራ ማዕከል ሳይመሰረት በኪሳራ የታጀቡ ዓመታትን አሳልፈናል። ትብብር የጉልበት ምንጭ ነው።ትብብር ድልን ማቅረቢያ ዘለቄታዊና ሠላማዊ ሽግግርን ማሳለጫ መሳርያ ነው።ትብብር ከሚከሰረው … [Read more...] about የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ ተስፋና ሥጋት!
«ችግሩን ለማስወገድ፣ ግለሰብ ወይም ቡድን መወገድ አለበት» ዐባይ ፀሐዬ
የትግራይ ሕዝብ ነፃ አውጭ ግንባር (ወያኔ) አጠቃላይ ግብ፣ ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ማጥፋት ነው። የዚህ ግብ መዳረሻ ደግሞ በኢትዮጵያዊነታቸው በጽኑ የሚያምኑ ኢትዮጵያውያን እና ከሁሉም በላይ፣ የዐማራውን ነገድ ማጥፋት ሲቻል እንደሆነ በማመኑ፣ ላለፉት 43 ዓመታት የኢትዮጵያዊነት የወል ዕሴቶችን፣ ነባር ሃይማኖቶችን፣ የአገራዊነት መገለጫ የሆነችውን ሰንደቅ ዓላማችንን፣ በሕዝቡ መሀል የአንድነት መገለጫ የሆኑ ተቋሞችንና አሠራሮችን፣ ግንኙነቶችን በአዋጅ አጥፍቷል። በዐማራው ነገድ ላይ የተቀነባበረ የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል ፈጽሟል። የተለያዩ መረጃዎች እንደሚያመለክቱት በወያኔ ዘረኛ አገዛዝ ከአምስት ሚሊዮን በላይ ዐማሮች ከምድረ-ገጽ እንዲጠፉ ተደርጓል። የትግሬ-ወያኔ ለዚህ ኢትዮጵያን፣ ኢትዮጵያዊነትንና የዐማራውን ነገድ ለማጥፋት ላለመው ዓላማው ወደ ግቡ መዳረስ … [Read more...] about «ችግሩን ለማስወገድ፣ ግለሰብ ወይም ቡድን መወገድ አለበት» ዐባይ ፀሐዬ









