• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ ተስፋና ሥጋት!

April 12, 2017 07:26 am by Editor 1 Comment

ላለፉት ሁለት ዐሥርት ዓመታት በዘረኛው የትግሬ ነፃ አውጪ የአገዛዝ መዳፍ ሥር የታፈነውን ሕዝባችንን ወደ ነፃነትና የዴሞክራሲ ምዕራፍ ለማሸጋገር የጋራ ትግል ለማድረግ ሲሞከር ቆይቷል።

ሆኖም በእነዚህ ዘመናት ውስጥ የተፈጠሩት የፖለቲካ ኃይሎች ትብብር፣ ቅንጅት፣ ኅብረት እና ውህደት አንዱም ከዳር ሳይደርስ እንዲሁ ሲሰበሰብና ሲበተን ከርሟል። እንደ አባባልም እንደ መታወሻም “ተባበሩ ወይ ተሰባበሩ” የሚለው የዶ/ር መረራ ጉዲና መፈክር አንዱም ገቢራዊ ሳይሆን አብዛኞቹ የፖለቲካ ተቋማት በአገዛዙ ጫናና በራሳቸው ደካማ አደረጃጀት ህልውናቸው እየጠፋ ለሐገር የሚተርፍና ትውልድ የሚረከበው አንድም አግባቢ የጋራ ማዕከል ሳይመሰረት በኪሳራ የታጀቡ ዓመታትን አሳልፈናል።

ትብብር የጉልበት ምንጭ ነው።ትብብር ድልን ማቅረቢያ ዘለቄታዊና ሠላማዊ ሽግግርን ማሳለጫ መሳርያ ነው።ትብብር ከሚከሰረው የሚያተረፈው የሚበዛበት የሕዝብን አብሮነት ማጠናከርያ፣ልዩነትን ማጥበቢያና የቅራኔ ማርገቢያ ጠቃሚ ዓላማ ነው።

አበው“ድር ቢያብር አንበሣ ያስር ” እንዲሉ የተበታተነን ትግል አቀናጅቶ ለውጤት በማብቃት የትብብር አስፈላጊነት ላይ ማንም ጥያቄ ባይኖረውም ይህንን ጠቃሚ መሳርያ ተጠቅሞና ኃይልን አጠናክሮ ጠላትን ለመርታት የሚያስፈልገውን ሰጥቶ የመቀበል፣የመቻቻልና የሰለጠነ ፖለቲካዊ ባህል ባለመኖሩ በተደጋጋሚ በሕዝብ ተነሳሽነት የተገኙ ወሳኝ ድሎች የተባበረ አመራር በመጥፋቱ ለቅልበሳ ሲዳረጉ ቆይተዋል።

ባለፈው ሰሞን የተለያዩ ወገኖች በተለያየ ጽንፍ ቆመው በአወዳሽነትና በነቃፊነት በየመገናኛ ዘዴዎቹ ሲናጩ የከረሙበት የአድዋ ድል በዓል ከአሸናፊነት የስነ ልቦና ውርስነቱና ፤ የክብር ልዕልናው ባሻገር ለዓለም ጭቁን ሕዝቦች ተምሣሌት የሆነ የመተባበር ውጤታማነት ማሳያ መሆኑን “ የራስ ወርቅ አያደምቅ” እንዲሉ እኛ ባለቤቶቹ ልንጠቀምበት ባንችልም በደቡብ አፍሪካ ፀረ-አፓርታይድ ትግል እና በሠሜን አሜሪካ የቆዳ ቀለም {ጭቆናን} ለመሰባበር ያስቻለ ተምሣሌት ለመሆኑ የትግሉ ባለቤቶች የመሰከሩትን ማየት ብቻ በቂ ይሆን ነበር።

ይህን የመሰለ ታሪክ አባቶቻችን ዘር፣ ቀለም፣ፆታና የብሔር ማንነት ሳይገድባቸው በሐገር ውስጥ የነበራቸውን ልዩነት አቻችለው በተባበረ ኃይል የአውሮፓ ወራሪን አሳፍረው በመመለስ ያቆዩልንን ሐገርና ዝንተ ዓለም በዓለም ጭቁን ሕዝቦች ታሪክ እንዳበራ የሚኖረውን ታሪክ ልንመራበት ቀርቶ ልንማርበት አለመቻላችን እጅጉን ያሳዝናል።

ከዚህ የተነሳ ሊያቀራርበን የሚችለውን ትተን ዘመን የሻረው አሮጌ ታሪክ ላይ ተቸክሎ፤ ማላዘን ተቋማዊና ሕብረተሰባዊ ባህል ወደ መሆን የደረሰ እስኪመስል ድረስ በሺህ ዘመናት ውስጥ ተገንብተው የኖሩ በጎና ተወራራሽ የጋራም የተናጥልም፤ የድል፣ የአብሮነትና የመቻቻል ታሪካችን ላይ ትኩረት ሰጥተን ያንን እንደማዳበር ከመቶ አምስት ዕጅ በማይሞላው የንትርክ አጀንዳ ላይ ኃይላችንን በማዋላችን ለሕዝባዊ ውድቀትና ለሃገራዊ ኋላ ቀርነት ተዳርገን ቆይተናል።

ሕወሃት ባሰማራቸው ቅጥረኞ፤ ባዶ ዝና ያናወዛቸው ዋልጌዎ፤ በጽንፈኛ ብሄረተኞች አቀጣጣይነት በሶሻል ሚዲያው በኩል የሚራገበው አሳፋሪ፤ አደገኛና ሗላቀር የጥላቻ ቅስቀሳ ተጠናክሮ ከቀጠለ ሕብረት መፍጠር አይደለም የሰላም ተስፋም እይኖርም። ከዚህም በላይ በሃገር ውስጥ ከእለት ወደ እለት እየተባባሰ የመጣው ድህነትና የአገዛዝ ጫና ሕዝባችንን ተስፋ ቆርጦ ወደ ለየለት አመጽ ገብቶ ሁኔታው ከቁጥጥር ውጭ ከሆነ በሗላ ለሕዝቡም ሆነ ለሃገሪቷ ልንደርስ የምንችልበት እድል በቀላሉ ስለማይኖር፤ ቀኑ ሳይመሽ ባለን እድል መጠቀሙ ለሁሉም የሚበጅ ይሆናል (ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ)

 

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Comments

  1. Biruk says

    April 14, 2017 01:14 pm at 1:14 pm

    እኔን ግን ከሁሉ ከሁሉ የገረመኝ አቶ ኃይለገብርኤል አያሌው ይህችን ፎቶ የለጣፋት ምን መልዕክት ለማስተላለፍ ፈልጎ እንደሆ ነው። ትልቅ ሰው ነኝ ለማለት ነው? ትልቅ ስለሆንኩ የኔ ውሎ ከፕ/ሮች ጋር ነው ለማለት ነው? በጣም የሚገርም ብቻ ነው።

    ለማንኛም ኮሜንት ልሰጥ ወደተነሳሁበት ዋናው ቁም ነግር ልግባ።

    አቶ ኃይለገብርኤል አያሌው አንተ ተስፋ የምትለው “የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ ” የሚባለውና ግንቦት 7 በበላይነት ሞተር ሆኖ የሚያሽከረከረው ንቅናቄ ለአማራው ምን እንደሆነ አማራው ጠንቅቆ ያውቃል። አንት ግን ስልጣንና በየመድርኩ እየተገኘህ ስምህንና ፎቶ መንሳትን ብቻ ስለምትወድና ስለተሸፈነብህ ግንቦት 7 ስለ አማራው ያለውን አመለካከት አታውቅም። ብታውቀም ስለተሸፈነብህ አይታይህም።

    አንት አማራው ተሎ ተደራጅቶ አንተ ተስፋ የምትለውን “የኢትዮጵያ ሐገራዊ ንቅናቄ” እንዲቀላቀል ትላላል። ግንቦት 7 ግን አማራው ተሎ ተደራጅቶ እንኳን ድርጅቱን እንዲቀላልቀል ቀርቶ እራሱን ብቻውን ቆም እንዲታግል አይፈልጉም። ለዚህ ማስረጃ የሚሆነው የሚከተለውን የከንቦት 7 ከፍተኛ አመራ የሆነው አቶ አበበ ቦጋ የተናገረውን ማዳመጥ ብቻ በቂ ነው። ሙሉን ማዳመጥ ጥሩ ነው። እኔ ግን እንድታዳምጠው የምፈልገውና አንተ ለጻፍከው የአማራ መደርጃት ለሚለው ጽሁፍ ግንቦት 7 ያለውን መለካከት ብቻ እጠቅሳለሁ።

    https://www.youtube.com/watch?v=eI7ZkWy3gyo

    ከቪድዮው ከ1:21፡00 (ከ1 ሰዓት 21 ደቂቃ ጀምሮ አዳምጥ)

    የኢትዮትዮብ ጠያቂ ጋዜጠኛ ዮሴፍ፤ ግን እኮ ሻለቃ ዳዊት ወልደጊዮርጊስ በስብሰባው ላይ ተጠይቀው በአሁን ሰዓት በአማራ ስም የተደራጁ ብዝህ ድርጅቶች ስላሉ ሁሉንም መጥራት ስላቻልን ወደፊት ለብቻ ሰርተን አንደ የተጠናከረ የአማራ ድርጅት ወደ “ሐገራዊ ንቅናቄ” እናመጣለን ብለው መስልስ ሰጥተዋል። ብሎ ሲጥይቀው

    መልስ የሚሰጠው የግንቦት 7 ከፍተኛ አመራር አቶ አበበ ቦጋለ፤ እኔ ሻለቃ ዳዊትን ብሆን ኖሮ ይህ አይነት ነገር ትክክል አይደለም ብየ ነበር የምናገረ። {አማራ ተደራጅቶ ወደ ንቅናቄ ይምጣ የሚለውን ነገር አልደግፍም ማለቱ ነው። ገባህ???}

    ስለዚህ አቶ ኃይለገብርኤል አያሌው ባጭሩ አንተ አማራው ተደርጅቶ ብትፈልግም የድርጅቱ አለቃና ሞተር ግንቦት 7 አይፈቅድም ማለት ነው።

    ከዚህ ላይ ግልጽ ላደርግልህ የምፈልገው ግን አማራው ተደራጅቶ የራሱ ስራ እየሰራ ነው። የተደራጀው ግን ከማንም ጋር ተቀላቅየ ስራ እስራለሁ ብሎ ሳይሆን በወያኔ እየደርሰበት ያለውን ጥቃት ለመመክት መደራጀት ስላለበትና መመከትም ስለምችል ነው። አማራ ከሆንህ አማራ ምን ማድረግ እንደሚችል ታውቃለህ።

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule