የዘመናት ታሪክ ባለቤትና ከትውልድ ወደ ትውልድ በመተላለፍ፤ ወደፊትም ለዘለዓለም የምትኖር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እውነተኛ የክርስቶስ ማደሪያ የምትባለው ዛሬ ኖሮ ነገ ለማይኖረው አምባ ገነንና ዘረኛ አገዛዝ መሣሪያ ሳትሆን ከተበደለውና መብትና ነጻነቱን ከተገፈፈው የኢዮጵያ ሕዝብ ጎን መቆም የቻለች እንደሁ ብቻ ነው። (ሙሉው ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about “ቤ/ክናችን አደጋ ላይ ነች፤ አድኑኝ ትላለች”
Right Column - Primary Sidebar
የደሞዝ Vs. የጠብሽ* ሰሞን
የዘወትር የድረገጻችን ተሳታፊ የሆኑ ይህንን ጽሁፍ እንድናነበውና እንድናትመው በላኩልን መሠረት እነሆ ለአንባቢዎቻችን አቅርበነዋል፡፡ በዚሁ አጋጣሚ ለጸሐፊዋ ማሕሌት ፋንታሁን ከፍ ያለ ምስጋናችንን እናቀርባለን፡፡ የደሞዝ Vs. የጠብሽ* ሰሞን አነጋገራችንን፣ አካሄዳችንን፣ አበላላችንን፣ አስተያየታችንን ባጠቃላይ የምናደርገውን ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ ቀጥጠኛ አስተዋፅኦ ካላቸው ነገሮች አንዱና ዋነኛው በኪሳችን ያለው ገንዘብ ዋነኛው ነው፡፡ ገንዘብ ከምናገኝባቸው አንዱ መንገድ ደግሞ ተቀጥሮ መሥራትና ወር ሲያልቅ የሠራንበትን ክፍያ/ደሞዝ ማግኘት ይገኝበታል፡፡ አብዛኛው በከተማ አካባቢ የምንኖር በዚህ መስመር ውስጥ እንገኛለን፡፡ ደሞዝ ተቀብሎ ቀጣዩን የደሞዝ ቀን እንደ ምፅአት ቀን በጉጉት የማይጠብቅ ካለ ይህ ሰው ከደሞዙ ውጪ ሌላ ተጨማሪ ገቢ አለው ወይም አንድ ቀልድ ላይ … [Read more...] about የደሞዝ Vs. የጠብሽ* ሰሞን
ኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያንና የ2012 ዓመተ ምህረቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ምርጫ
እንደማንኛውም የአሜሪካ ኅብረተሰብ ሁሉ፤ በኢትዮጵያዊ አሜሪካዊነታችን፤ ማንኛውንም ምርጫ ከራሳችን ጥቅም አንፃር መመልከቱ ለሕልውናችን አስፈላጊ ጉዳይ ነው። እናም የ2012 ዓመተ ምህረቱን የአሜሪካ ፕሬዘዳንት ምርጫ የምንመለከተው፤ ከዚህ ተነስተን ነው። እኛ ምን ሠራን? ምን ተጠቀምን? ምን ተጎዳን? ምን አገኘን? ምን ቀረብን? ምን ማድረግ ነበረብን? በመጨረሻ ደግሞ፤ ምን ትምህርት ወሰድን? ይህ ነው ለምርጫው ግምጋሜ ጠቅላላ ይዘቱ፤ ከኢትዮጵያዊ አሜሪካዊነታችን አንፃር ሲታይ። የባራክ ኦባማ ከጥቁር ዝርያ መሆኑ ወይንም የሚት ራምኒ ነጭ መሆን ቦታ አልነበረውም። የዴሞክራቲክ ፓርቲው ማቸነፍ ወይንም የሬፑብሊኩ ፓርቲ መቸነፍ፤ ለኛ ትርጉሙ በፓርቲነታቸው ሳይሆን፤ የኛን ጉዳይ በሚመለከት ባላቸው አቁዋም ነው። በአሜሪካን ፓርቲ ስሌት ደግሞ፤ የምንፈልገውን ለማግኘት፤ የሚተማመኑበት የአንድ … [Read more...] about ኢትዮጵያዊያን አሜሪካዊያንና የ2012 ዓመተ ምህረቱ የአሜሪካ ፕሬዚዳንት ምርጫ
ከእሁድ እስከ እሁድ
ኢህአዴግን በኃይል ለማስወገድ ጥሪ ቀረበ በኢትዮጵያ ያለውን አገዛዝ ለመጣል ይቻል ዘንድ ለቀድሞው ሰራዊት፣ አሁን በስራ ላይ ላሉት የመከላከያ አባላትና በአገር ውስጥና በውጪ ስደት ላይ ላሉ ዜጎች ሁሉ የትግል ጥሪ ቀረበ። “የግንቦት 7 ሕዝባዊ ኃይል” በሚል ስያሜ ጥሪውን ያስተላለፈው ክፍል ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ከሚመሩት ድርጅት ጋር ግንኙነት እንዳለው ለማጣራት ያደረገው ሙከራ እንዳልተሳካለት ኢሳት ዘወትር እሁድ በሚያቀርበው የሳምንቱ ዜናዎች ላይ አስታውቋል። ኢሳት በሰበር ዜና ያቀረበው ይህ ዜና ከዋናው የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ጋር ግንኙነት እንዳለውና እንደሌለው ለማጣራት ያደረገው ሙከራ ለጊዜው ባይሳካለትም፣ በቅርቡ ግን መረጃዎችን በማሰባሰብ በጉዳዩ ዙሪያ ማብራሪያ የሚያቀርብ መረጃ ለመስጠት እንደሚተጋ አስታውቋል። በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ ያለ ህዝብ ይሁንታ ላለፉት ሃያ አንድ … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
Leveling the playing field in Ethiopia
The press release was short and to the point. It was only six paragraphs long and was written in a matter of fact way. There were no trumpets blaring, no press conference with TV lights and no lavish dinner to commemorate the event. The announcement reminded me of the proverb ‘best things come in small packages.’ So it was without much fanfare I read the most important announcement on Abbay Media and Quatero. Tucked among the news was the announcement regarding the formation of Ginbot 7 Popular … [Read more...] about Leveling the playing field in Ethiopia
የጎልጉል ቅምሻ
ካውያ እንደ ስልክ ባለቤቱን በርካታ ሥራዎችን በአንድ ጊዜ መሥራት እንደሚችል በማሳየት ለማስደሰት ቆርጦ የተነሳው ፖላንዳዊው ባል እንዳሰበው አልሆነለትም፡፡ ባለቤቱ ከሥራ ስትመጣ ማከናወን የሚገባውን ሥራዎች በተገቢው ሁኔታ ሳይፈጽም መቅረቱ ሁልጊዜ የሚያሳስበው ባል ቴሌቪዥኑን ለኩሶ ከጎኑ ቢራውን እየተጎነጨ ልብስ መተኮስ ጀመረ፡፡ በመካከል ስልኩ ሲያንቃጭል እጁ ላይ ያለው የጋለ ካውያ ስልክ የመሰለው አባወራ ካውያውን ጆሮው ላይ በመደገን ባደረሰው ጉዳት አሁን በአንድ ጊዜ በርካታ ሥራዎችን ማከናወን በተመለከተ ከሴቶች ይልቅ ወንዶች እጅግ ደካማ እንደሆኑ አስመስክሯል፡፡ ከእንግዲህ ወደቤት ሥራ እንደማይመለስ የተናገረው ባል ጉዳዩ ሲያት ቀላል እንደሚመስል ከዚህ በኋላ ግን ለባለቤቱ ተገቢውን ክብር እየሰጠ አርፎ እንደሚቀመጥ ተናግሯል፡፡ ፕሬዚዳንት ኦባማ አራት ጊዜ ቃለመሃላ … [Read more...] about የጎልጉል ቅምሻ
ከእሁድ እስከ እሁድ
ገበያ የደራላት ጅቡቲ ታህሳስ 4 ቀን 2005 ዓም ከወደአገርቤት የተዘገበው ዜና መለስን በማስታወሻነት የሚዘክር ሆኗል። ዜናው እንዳለው ጠ/ሚኒስትር ሃይለማርያም ደሳለኝ በተገኙበት ጅቡቲ ታጁራ ላይ አዲስ ወደብ ለመገንባት የመሰረት ድንጋይ የማስቀመጥ ስነስርዓት አከናውናለች። የጅቡቲው ፕሬዝዳንት ኢስማኤል ኦማር ጌሌ የወደቡ ግንባታ ሲጠናቀቅ ኢትዮጵያ የምትፈልገውን የወደብ አገልግሎት በተሟላ ደረጃ እንድታገኝ ያስችላታል ሲሉ የ “ገበያው ደራ” ንግግር አድርገዋል። በስነ ስርአቱ ላይ የተገኙት ሃይለማርያም ደሳለኝ ፥ አዲሱ የወደብ ግንባታ የኢትዮጵያና የጅቡቲ ህዝብ ግንኙነት ወደ ላቀ ደረጃ የሚያሸጋግር መሆኑንን ጠቅሰው መናገራቸውን የገለጸው ፋና ብሮድካስቲንግ “ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዳሉት በየብስና በባቡር ትራንስፖርት ፣ በሃይል አቅርቦትና በወደብ አገልግሎት የተቆራኘው የሁለቱ … [Read more...] about ከእሁድ እስከ እሁድ
ኢህአዴግ እያስታመመ ነው
የአቡነ መርቆርዮስ ወደ አገር ቤት መመለስ ከስምምነት ላይ ተደረሰ፡፡ ልዩነት የተፈጠረው መንበራቸውን በመረከባቸው አብይ የቤ/ክርስቲያን ቀኖና ላይ ነው፡፡ ይህ የተገለጸው ከህዳር 26 እስከ ህዳር 30፤ 2005ዓም (December 5 – 9, 2012) በዳላስ ከተማ በቴክሳስ ጠቅላይ ግዛት በአገርቤቱ ሲኖዶስና በአሜሪካ ከሚገኘው ስደተኛ ሲኖዶስ ተወካዮች ድርድራቸው ካጠናቀቁ በኋላ ባወጡት የጋራ መግለጫ ነው፡፡ የጋራ መግለጫው ከመውጣቱ በፊት ፕሬዚዳንት ግርማ ወ/ጊዮርጊስ አቡነ መርቆሪዮስ ከነሙሉ መንበራቸው አገር ቤት እንዲመለሱ የሚጠይቅና ማረጋገጫ የሚሰጥ ደብዳቤ ልከው ነበር፡፡ “የኔው የራሴ ደብዳቤ ነው” በማለት ለቪኦኤ የአማርኛ ክፍል በቃላቸው ጭምር ያረጋገጡት ፕሬዚዳንቱ ከአፍታ በኋላ “ያለሥልጣኔ ገብቼ የፈጸምኩት ነው” በማለት ደብዳቤውን መሰረዛቸውን አስታውቀው ነበር፡፡ … [Read more...] about ኢህአዴግ እያስታመመ ነው
መሰላል
መሰላል መሰላል ለመውጣት አለው ትልቅ ብልሃት፡፡ የላዩን ጨብጦ፣ የታቹን ረግጦ፣ ወደላይ መመልከት፡፡ እጆችን ዘርግቶ በኃይል መንጠራራት፡፡ ጨብጦ መጎተት የላዩን! ላዩ ታች እንዲሆን! አንድ ባንድ እየረገጡ፣ መሰላል የወጡ፡፡ ብልሆች የማይጣደፉ፣ ሞልተዋል በያፋፉ! ዘርግተው የጨበጡትን መርገጥ፣ የመውጣት ሕግ ነው የማይለወጥ ሲወርዱ ግን ያስፈራል፤ የረገጡትን ያስጨብጣል፡፡ (መስፍን ወልደማርያም፣ እንጉርጉሮ፣ 1967) yeKanadaw kebede “በሳቅ ፍርስ አሉ” በሚል ርዕስ ላቀረቡት የግጥም ጨዋታ ዱባለ፣ በለው እና dawit ለጨዋታው ምላሽ ስለሰጣችሁ ከልብ እናመሰግናችኋለን፡፡ የጨዋታውን ደራሲ yeKanadaw kebede እንዲሁ፡፡ ስለ “መሰላል”ስ ምን ትላላችሁ? እስቲ ጨዋታውን አምጡታ!? … [Read more...] about መሰላል
ከአእምሮ ባርነት ነጻ እንውጣ!
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በተደጋጋሚ የተሃድሶን አስፈላጊነት በሚያወጡት ርዕሰአንቀጽ ላይ አስነብበውናል፡፡ ባለፈው ጊዜ “ከፖለቲካ ተሃድሶ በፊት [የእውቀት] ተሃድሶ በአስቸኳይ!!” በሚል ርዕስ የተሃድሶን ጥቅምና አስፈላጊነት አስታውቀውናል፡፡ በቅርቡ ደግሞ “የተሃድሶ ያለህ!!!” በማለት በድጋሚ የሰሚ ያለህ ብለውናል፡፡ እኔም ይህንን በሙሉ ልብ የማምንበትን ሃሳብ በማንሳታቸው ላመሰግናቸው እወዳለሁ፡፡ በዚሁ ርዕስ ዙሪያ “ከአእምሮ ባርነት ነጻ እንውጣ” በሚል ሃሳቤን እንደሚከተለው አቅርቤአለሁ፡፡ ከአእምሮ ባርነት ነጻ እንውጣ የሰውን ልጅ “ሰው” ከሚያሰኙት መካከል ማንነቱን የሚወስኑት የአካላዊ፣ የአእምሯዊና የመንፈሣዊ ኃይላት ውጤት መሆኑ በዋንኛነት ተጠቃሽ ነው፡፡ እነዚህ ዕድገታቸውን በተመጣጠነ መልኩ ካልተጠበቀ የሰው ልጅ “ሰው” ተብሎ ቢጠራና ራሱንም “ሰው ነኝ” እያለ … [Read more...] about ከአእምሮ ባርነት ነጻ እንውጣ!










