እንኳን ለ፪ሺ፯ ዓ.ም. አደረሠን፣ አደረሣችሁ! ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፦ እኛ ኢትዮጵያውያን በየዓመቱ የመስከረምን ወር የመጀመሪያ ቀን የዘመን መለወጫ ዕለት አድርገን ማክበር የጀመርነው በሺህዎች ለሚቆጠሩ ዘመናት እንደሆነ ይታወቃል። በረዥሙ ታሪካችን እንደየአመጣጣቸው፦ ደስታን እና ሐዘንን፣ መከራን እና ብሥራትን፣ ጦርነትን እና ሰላምን፣ መቆርቆዝን እና መበልፀግን፣ ረሃብን እና አንፃራዊ ጥጋብን፣ ወዘተርፈ አስተናግደናል። ያለፈውን ዘመን ሸኝተን አዲስ ዓመት ስንቀበል ዘወትር መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። ስለዚህ ይህ መግለጫም የኢትዮጵያውያን የዘመናት ትውፊት አንዱ አካል ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ያገባደድነውን ዓመት ዘመነ-ማርቆስን ስንሸኝ በዓመቱ ውስጥ ያከናወናቸውን ተግባሮች መመዘን ጠቃሚ ይሆናል። ስለሆነም፦ «እኔ ለራሴ ነፃነት መከበር፣ እንዲሁም ወገኖቼ … [Read more...] about በአዲስ ዓመት ለተግባራዊ ዕርምጃ መዘጋጀት ይገባል
Left Column
የታገደው ድፍረት ፊልም የይገባኛል ጥያቄ አስነሳ
አንጀሊና ጆሊ ኤግዚኪዩቲቭ ፕሮዲዩሰር የሆነችበትና ነሐሴ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ዲፕሎማቶችና የመንግሥት ባለሥልጣናት በተገኙበት በብሔራዊ ቴአትር ሊመረቅ የነበረው ድፍረት ፊልም፣ በፍርድ ቤት እግድ ከተቋረጠ በኋላ የይገባኛል ጥያቄ ማስነሳቱ ታወቀ፡፡ በአሜሪካ በሰንዳንስ ፊልም ፌስቲቫል ተሸላሚ ከሆነ በኋላ የፊልሙ በአዲስ አበባ መመረቅ በብዙዎች በጉጉት እየተጠበቀ ነበር፡፡ እንዲህ የተጠበቀው ፊልም ሊመረቅ በታሰበበት ዕለት ከአሥራ አምስት ደቂቃዎች በላይ ሊታይ አልቻለም፡፡ በብሔራዊ ቴአትር እየታየ ፌደራል ፖሊስ ደርሶ ሊያቋርጠው የግድ ሆኗል፡፡ ፊልሙ በእውነተኛ ታሪክ ላይ የተመሠረተ በመሆኑ የሚያጠነጥነው አስገድዶ የደፈራትን የ29 ዓመት ወጣት በገደለችው የ14 ዓመት ታዳጊ አበራሽ በቀለ (በፊልሙ ሒሩት) ሕይወት ዙሪያ ነው፡፡ ደፋሪዋ … [Read more...] about የታገደው ድፍረት ፊልም የይገባኛል ጥያቄ አስነሳ
“ሕወሀት ኢሕአዴግ” በቅርብ ጊዜ የብሔራዊ እርቅ ተማጻኝ!
ብሔራዊ እርቅ (National Reconciliation) በተለይ በእርስ በእርስ ግጭት ደም የተቃባንና የከፋ አደጋ የተጋረጠበትን ኅብረተሰብ ወይም የመበታተን አደጋ የተጋረጠባትን ሀገር በይቅር ለእግዚአብሔር ይቅር አባብሎ ሰላም ለማውረድና የቂም በቀልን ዶሴ ዘግቶ በአዲስ መንፈስ ብሔራዊ መግባባትን (National Consensus) ፈጥሮ የአንዲት ሀገርን ሕዝብ በአንድነት አስተባብሮ ለማንቀሳቀስና ህልውናውን ከመረጋጋቱ ጋራ ለማስቀጠል ዓይነተኛ መንገድ ነው፡፡ በሕወሀት ኢሕአዴግ የአገዛዝ ዘመን የዚህ የብሔራዊ እርቅ (National Reconciliation) ጥያቄ በተለያዩ አካላት በተደጋጋሚ ሲቀርብ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን የአገዛዝ ሥርዓቱ ይህ እርቅ ቢፈጸም የመጀመሪያውና ዋነኛው ተጠቃሚ እሱ መሆኑን እስከአሁንም ቢሆን መረዳት ባለመቻሉ ምክንያት የተለያዩ የእብሪት ኃይለ ቃሎችን … [Read more...] about “ሕወሀት ኢሕአዴግ” በቅርብ ጊዜ የብሔራዊ እርቅ ተማጻኝ!
የዛፍ ጥላ ስር ትምህርት ቤቶች
ጠመዝማዛ ባላዎች ላይ የቆመው ክፍል በደደሆ ዛፍ ቅጠል የተሠራ ጣሪያ አለው፡፡ ክፍሉ ውስጥ ከ20 የማይበልጡ ትንንሽ ድንጋዮች ላይ ኩርምት ኩርምት ብለው የተቀመጡ ተማሪዎች ይታያሉ፡፡ ደብተሮቻቸውን በየጉልበታቸው ላይ አድርገው ከፊት ለፊታቸው ያለውን መምህር ያዳምጣሉ፡፡ ከመሬት ብዙም የማይርቀው የክፍሉ ጣሪያ መምህሩን ጐንበስ ብሎ እንዲያስተምር ግድ ብሎታል፡፡ መምህሩ ለማለቅ በተቃረበ ነጭ ጠመኔ ያረጀ ሰሌዳ ላይ ቁጥሮች እየጻፈ ድምፁን ከፍ አድርጎ ሒሳብ ያስተምራል፡፡ የክፍሉ ጣሪያ በሳሳበት አቅጣጫ የተቀመጡ ተማሪዎች ጸሐይ ይመታቸዋል፡፡ ተማሪዎቹ ድንጋዩ ጐርበጥ ሲያደርጋቸው ወደ አንድ ወገን ገደድ እያሉ ለመመቻቸት ይጣጣራሉ፡፡ እነዚህ በዛፍ ጥላ ስርና በዳስ የሚማሩ ተማሪዎች የመኪና ድምጽ በሰሙ ቁጥር አንገታቸውን አጠማዘው ይመለከታሉ፡፡ ግድግዳ በሌለው ክፍላቸው አቅራቢያ … [Read more...] about የዛፍ ጥላ ስር ትምህርት ቤቶች
ቴዲ አፍሮ – በሁለት ጽንፎች
ኢትዮጵያ ውስጥ ፈጽሞ ሊተቹ የማይችሉ ሶስት ግዝፍ ነገሮች አሉ። እነዚህም 1ኛ - ሃይማኖት 2ኛ - መንግስት 3ኛ - ቴዲ አፍሮ ናቸው። ከእንግዲህ ቴዲ አፍሮ ዘፋኝ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ መቆራቆዣ ተቋም ሆኗል። ይህን አስመልክቶ ወዳጃችን Girmabbaacabsaa Guutamaa እንዲህ ይላል.... "ቴውድሮስ ካሳሁን aka ቴዲ ኣፍሮ ዘፋኝ ብቻ ኣይደለም። በሃገሪቱ ውስጥ ካሉት ይልቁንም ባብዛኛው ሊታረቁ የማይችሉ (divergent) ማህበረ-ፖለቲካዊ እሳቤዎችን በሚያራምዱ ኤሊቶች ከሚመሩት የተለያዩ ቡድኖች መካከል የኣንዱ ግሩፕ political ideologue ነው ቴዲ።" ይህ ብያኔ (Definition) የተለጠጠ ቢሆንም ውሸት ግን አይደለም። ቴዲ በሁለት ጽንፍ የቆሙ የፖለቲካ ወገኖች መቆራቆዣ አእማድ (Pillar) ሆኗል። የቴዲን ዘፈኖች መተቸት … [Read more...] about ቴዲ አፍሮ – በሁለት ጽንፎች
Why Free Trade Agreements with the EU will hurt African countries!
Impacts of Free Trade & Globalization Since 2002 the EU, African countries and including the Caribbean states have been conducting negotiations to reach Economic Partnership Agreements(EPAs) that might give opportunities for these states to get access for their products into the EU market. In turn the EU wants to get a free access to the African market. The negotiation has taken too long because of the nature and complexity of the issue and at the same time because of the intriguing … [Read more...] about Why Free Trade Agreements with the EU will hurt African countries!
የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን?
“የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን” የኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን የሚለውን ቃል ለምን በትእምርተ ጥቅስ እንዳስቀመጥኩት የገባችሁ ይመስለኛል፡፡ ጣቢያው ስሙ እንደሚጠቁመው የሀገር የብዙኃን መገናኛ ሳይሆን እራሳቸውን በመንግሥት ስም ያደራጁ በአብዛኛው ከሀገርና ከሕዝብ ጥቅም ተፃራሪ የሆነ ጥቅም ፍልጎትና ዓላማ ያለው ቡድን ዓላማ ማራመጃ ከሆነ ዐሥርት ዓመታት አልፏልና ነው መትእምርተ ጥቅስ ማስቀመጤ፡፡ ይህ የብዙኃን መገናኛ ሕግና ሕዝብ እንዲሆን የሚጠብቀው ነገር ግን የመንግሥት (የሕዝብ) መሆን ያልቻለው ብሔራዊ የቴሌቪዥንና ሬዲዮ (የምርአየ ኩነትና የነጋሪተ ወግ) ጣቢያ ትናንትና በ19-12-2006 ዓ.ም. የግል የኅትመት የብዙኃን መገናኛዎችን በተመለከተ “ያልተገሩ ብዕሮች” በሚል ርእስ ዘጋቢ ፊልም ሲል በሠየመው ዝግጅት ዝግጅቱ ምንም እንኳን ዘጋቢ ፊልም (ምትርኢት) ለመሰኘት … [Read more...] about የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን?
የቅርብ ጊዜ አዳዲስ ስሞች
ከቅርብ ጊዜያት ወዲህ እየወጡ ያሉ ስሞች 1. ልማቱ ፈጠነ 2. ቦንድነህ አባይ 3. ሊግ ይበልጣል 4. አኬልዳማ ታዬ 5. ኑሮ ውድነህ 6. ፌደራል እርገጤ 7. ስልጣኑ በዛብህ 8. ኮንዶሚኒየም ለማ 9. ግምገማ ከበደ 10. ተሳለጭ ሃገሬ 11. መተካካት ተሻለ 12. ባድመ ይበቃል 13. አሰብ ተስፋዬ 14. ቻይና ፍቅሩ 15. መብራት ይታገሱ 16. ቴሌነሽ በዝብዝ 17. አክስዮን ሰብስቤ 18. ቫቱ በዛብህ 19. ግብሩ ጫንያለው 20. ህገመንግስት ጣሴ 21. ነጠፈ ብሩ 22. ፌስቡክ ተመስገን 23. ሀያልነሽ መንግስቴ 24. አምስትለአንድ አደራጀው 25. ግንቦት ሃያ ገብረማርያም (ምንጭ: Ethio-Sunshine ፌስቡክ) በአንባቢያን የተጨመሩ: Gulilat Kasahun የጨመሩት 1. ምርጫዬ ደረሰ 2. ደሞዝ ስሜነህ 3. … [Read more...] about የቅርብ ጊዜ አዳዲስ ስሞች
ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል
ጉልበት አራዊት የሚተዳደሩበት ሕግ ነው፤ ሕገ አራዊት የሚባለው አራዊት የሚተዳደሩበት ጉልበት ነው፤ በአራዊት ዓለም ማናቸውም ነገር በጉልበት ያልቃል፤ በሰዎችም መሀከል ጉልበት አድራጊ-ፈጣሪ ሆኖ ጎልቶ ሲወጣ የአእምሮንና የኅሊናን መዳከም ወይም ጭራሹኑ አለመኖር ያመለክታል፤ ጉልበት አለን በማለት፣ ወይም ተመችቶናል በማለት፣ ወይም ጠያቂ የለብንም በማለት የማንኛውንም ሰው ሰብአዊ መብቱንና ሰብአዊ ክብሩን መግፈፍ ሦስት ነገሮችን ያመለክታል፤ አንደኛ ጉልበት እንጂ አእምሮና ኅሊና እንደሌለ፣ ሁለተኛ ጉልበት እንጂ ሕግ እንደማይከበር፣ ሦስተኛ በአንተ ላይ እንዲያደርጉብህ የማትፈልገውን አንተም በሰዎች ላይ አታድርግ የሚለውን ሕግ መጣስን ያሳያል፤ በመጨረሻም፣ ዘግይቶም ቢሆን በራስ ላይ ቅሌትን መጋበዝን ያስከትላል፤ የሌላውን ሰውነት ስናረክስ ሰውነትን በጠቅላላው ማርከሳችን ነው፤ ሰውነትን … [Read more...] about ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል
Ethiopian Special Forces can quell the unrest in Ferguson.
On 9, Aug, 2014 a white police man allegedly shot an unarmed African American teenager, Michael Brown, 18, in Ferguson Missouri, USA. Ever since Washington seemed unable to restore calm and tension in the city. However if the USA had invited Special Forces of the current Ethiopian government, the whole public chaos and mob would have been quelled in a matter of hours. For more than the past 23 years the Ethiopian government (EPDRF) has been diligently working in producing Special Forces who … [Read more...] about Ethiopian Special Forces can quell the unrest in Ferguson.










