ሊቀ ሰላዩ ደብረጽዮን የህወሃት መክሸፍ ያሳሰባቸው ይመስላል። "ነጻው ጋዜጠኛ" ዳዊት ከበደ "አውራምባ times" በሚባለው ጉራማይሌ ጋዜጣ ላይ የሰሞኑን ቃለምልልሳቸውን ሲያትም ያወጣው ፎቶ በደብረጽዮን ጠረጴዛ ላይ የሚታየው Why Nations Fail የሚለውን የDaron Acemoglu እና የJames A. Robinson መጽሃፍ ነው። ላለመክሸፍ የባዕድ መጽሃፍ ከማንበብ ከምትሞቀው ወንበር ትንሽ ብድግ ብሎ "እረኛ ምን ይላል?" ማለት ከክሽፈት ያድን ይሆናል! ወይስ አላማው ለኦህዴድ መሪዎች ተሃድሶ ሊያስተምሩበት ይሆን? ወይስ ሃይለማርያም ደሳለኝ ባለፈው ግምገማ "አዳዲስ ቃላት አመንጭተህ አታውቅም" ተብለው ስለነበር "የሃይለማርያምን መሰደብ የሰማ" በማለት ለራሳቸው አዳዲስ ጸረ-ክሽፈታዊ ቃላትን ሊማሩበት ይሆን? የወንበሩዋ ተስፈኛ አይደሉ! መጽሃፉ ስለክሽፈት ብዙ ያስተምራል ግን … [Read more...] about ላለመክሸፍ?!
Left Column
ህብረት ህብረት ህብረት አሁንም ህብረት
በኢትዮጵያ ውስጥ ያለው ግፍና የፍትህ መጥፋት ስለበዛ ህዝባዊ አመጽ በሁለት መንገድ ሊነሳ ይችላል ሲሉ ቆይተዋል አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች። አንደኛው ህዝብ ራሱ ድንገት የሚያነሳውና የሚመራው (spontaneous አመጽ) ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ በፖለቲካ ወይም በሲቪክ በተደራጁ ሃይላት ታቅዶ የሚመራ በቅስቀሳና በጥሪ የሚነሳ ሊሆን ነው። ከወር በላይ የሆነውና በኦሮሞ ክልል ውስጥ በሰፊው የተነሳው ተቃውሞ የአዲስ አበባውን ማስተር ፕላን ተከትሎ የተፈጸመውን ማፈናቀል እንደ ማቀጣጠያ አድርጎ የተነሳ በህዝብ የተመራ ህዝባዊ አመጽ ሆኖ ብዙ ሰው በሚገባ እንደተረዳው የህዝቡ ጥያቄ የመንግስት ለውጥ ጥያቄ ነው። ለብዙ ዓመታት ታምቆ የቆየ የመልካም አስተዳደርና የዴሞክራሲ እጦት፣ የመሬት ነጠቃው ጉዳይ ናቸው ዛሬ ይህን ህዝብ አስመርረው- አስመርረው ጎዳና ላይ ያወጡት። ህዝቡ በየቦታው … [Read more...] about ህብረት ህብረት ህብረት አሁንም ህብረት
ድንበር
መግቢያ “ድንበር ሲፈርስ፤ መሐሉ ዳር ይሆናል” በሚል ርእስ ይህች ጦማር የፈለቀችበት ዘመን፤ ኢትዮጵያን ከጎረቤት አገር የሚያዋስኗት ድንበሮችና፤ በውስጥም ዜጎቿ ተከባብረውና ተዋደው የሚኖሩባቸው ወሰኖች የፈረሱበት፤ ረዥም ዘመን የኖሩ ዛፎች የተጨፈጨቡት፤ መልሰው እንዳያቆጠቁጡ፤ (እንዳያንሰራሩ) ግንዶች ከነስራቸው የነገሉበት ዘመን ነው። ለ 25 ዓመት ኢትዮጵያን የገዛው የወያኔ መንግሥት፤ አገሪቱን ከተቆጣጠረበት ቅጽበት ጀምሮ በቅርብ የሚታየው ከሩቅ የሚሰማው መፍረስና መገሰስ ቢሆንም፤ በየዘመኑ ድንበር እየጣሱ ከመጡ ወራሪዎች ጋራ ለዳር ድንበር ስትፋለም የኖረች ጥንታዊት የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተውህዶ ቤተ ክርስቲያናችን በዚህ ወቅት ምን ትላለች?የሚለው ጥያቄ በኢትዮጵያውያን መካከል ብቻ ሳይወሰን፤ የኢትዮጵያን ታሪክ በሚያውቁ በውጭ አገር ሊቃውንት መካከልም መነጋገሪያ … [Read more...] about ድንበር
በአደባባይ የተነገረው እውነት ውሸት ሆኖ ይከስማል ወይም እውነት ሆኖ ይጠበድላል
ትግርኛ ቋንቋም ያደናብር ጀመረ እንዴ! ዛሬ (ጥር 6) በፌስቡክ ላይ እንዳየሁት አንዲት ሴት ወገብዋን በነጠላዋ አስራ ትግርኛ የማያውቀውንም የሚቀሰቅስ ንግግር ስታደርግ ነበረ፤ የተናገረችው ብዙ ሕዝብ በተሰበሰበበት ነው፤ የሕዝቡን ቀልብ ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥራው ነበር ለማለት አያስቸግርም፤ አንዳንድ ትግርኛ ተናጋሪዎች "ጀግና" እያሉ በወያኔ ላይ የተቃውሞ ንግግር ማድረጉዋን ሲገልጹ አንዳንዶቹ የቋንቋው ባለቤቶች ደግሞ በጣም እየተናደዱ የሴትዮዋ ንግግር የተቃውሞ ሳይሆን የድጋፍ ንግግር ነበር እያሉ ይሞግታሉ፤ የትግርኛ ተናጋሪዎች ተቃውሞንና ድጋፍን ለመለየት ችግር አለባቸው ከማለቴ በፊት ከዚህ በፊት እኔ በትግራይ ሕዝብ ምክንያት የታማሁበትን እንደሚያስታውሰኝ መግለጹ ተገቢ ይመስለኛል፤ የወያኔ ግልጽ ተጽእኖ የትግራይ ሕዝብ በሙሉ በሀሳብ እንዳይለያይ ነው፤ ወያኔ በትግራይ ችጋር የለም … [Read more...] about በአደባባይ የተነገረው እውነት ውሸት ሆኖ ይከስማል ወይም እውነት ሆኖ ይጠበድላል
ዳሪና ቀባሪ
ዳሪ ወዳጄ እንደምነህ - ውዱ ጎረቤቴ ባለህበት ቦታ - ይድረስህ መልክቴ የልጄ ሰርግና - የሟች ልጅህ ቀብር አንድ ላይ መሆኑ - ፈጥሮብኛል ችግር መቼም ይገባሃል - ግልጽ ነው ነገሩ ብዙ ነው ማዕረጉ - የሠርገኛ ክብሩ ስለዚህ አደራ - የልጄን ታላቅ ሠርግ በደስታ በሆታ - እንዳሳልፍ በወግ በዛ ቀን ተነስተህ - ልጅህን ስትቀብር ስዎችን ሰብስበህ - አታብዛ ግርግር እንደውም ጨርሶ - ከሞት ላታድናት በሳቅ በደስታ - በ`ልልታ ቅበራት ለለቅሶኛው ሁሉ - ይኼን ንገርልኝ ነገ ማታ ድረስ - መልስህን ላክልኝ ቀባሪ ክቡር አስተዳደር- የላኩልኝ መልዕክት እጅግ አስገራሚ - ድንቅ ነው በእውነት ታስራ ተገንዛ - ልጅ ልትቀበር ተሞሸረች አሉኝ - የርስዎ ልትዳር ለክብርዎ ሲባል - ለርስዎ ወግ … [Read more...] about ዳሪና ቀባሪ
ሰላም ወዳድነት አሸናፊነት ነው
ኢትዮጵያ በአፍሪካና አለም ታሪክ አኩሪ ስም ይዛ የኖረች ታላቅ ሀገር ናት። ልጆቿ ጎሳና ቋንቋ ሳይለያቸው ለሃገራቸውና ለክብራቸው በቆራጥነት በከፈሉት የጋራ መስዋእትነት ለራሳቸው ብቻ ሳይሆን ለአህጉራቸው ህዝብ ጭምር ክብር ያጎናፀፉ ጀግኖች መሆናቸውን ያስመሰከሩባት የአበሻ ምድር ናት። ኢትዮጵያ በሽታ ድህነትና ማይምነት ሳይበግረው የውጪ ጠላትን ያንበረከከ ጀግና ህዝብ ያላት ታምረኛ ሃገር ናት። ኢትዮጵያ የራሳቸውን ያገር አንድነት በሚያስደንቅ ወኔ ህይወታቸውን በመገበር ለአፍሪካ ወንድሞቻቸውና እህቶቻቸው አለኝታነታቸውን ያረጋገጡ ኩሩ ህዝብ ሃገር ናት። ኢትዮጵያ ከራሷም አልፋ ላለም ሰላምና ደህንነት የታገለችና በጥቁር ህዝብ አኩሪ ታሪክ ተምሳሌነቷ ለትውልድ ልእልና ያጎናጸፈች የጀግና ህዝብ ምድር ናት። እንዳለመታደል ሆኖ ያቺ ስመገናና ሃገር ያች በህዝ ያገር ፍቅር ወኔና ጀግንነት … [Read more...] about ሰላም ወዳድነት አሸናፊነት ነው
ካለፉት ድርጊቶች መማር ያልቻለ ትውልድ፣ ለገጠሙት ችግሮች መፍትሔ ማግኘት አይቻለውም!
የአንድ አገር ችግሮች የዛሬ ሁኔታዎች የፈጠሩዋቸው ብቻ አይደሉም። እንዳውም የአብዛኞቹ ችግሮች መነሻ መሠረታቸው ዛሬ ሳይሆን፣ ትናንትና ከትናንት ወዲያ ነው። የወቅቱን ችግሮቹ አስቸጋሪና ውስብስም የሚያደርጋቸውም ይኸው ምንጫቸው ካለፉ ትውልዶች ተያይዘው መምጣታቸው ነው። የዛሬውን የአገራችን ፖለቲከኞች አብሮ ለመሥራት ቀርቶ እንደ ኢትዮጵያዊ ዜጋ ማሰብ ያቃታቸው የለውጥ አራማጅ ነኝ የሚለው ትውልድ ዘርቶት የሄደው «ኢትዮጵያ አገር አይደለችም፤ እንዳውም የብሔረሰቦች እስር ቤት ናት፤» የሚለው አስተሳሰብ ተሸካሚ በመሆኑ ነው። በመሆኑም ዛሬ ትውልዱ ለገጠመው ሁለንተናዊ ችግር መፍትሔ ለመሻት ከልቡ ካሰበና ለዚህም ቆርጦ ከተነሳ፣ ያለፉት ትውልዶች የተከተሉትን ሕዝብን በቋንቋ፣ በሃይማኖትና በማንነት የመከፋፈል አስተሳሰብና አመለካከት አውልቆ መጣልና ኢትዮጵያዊ ማንነትን መቀበል ይጠበቅበታል። … [Read more...] about ካለፉት ድርጊቶች መማር ያልቻለ ትውልድ፣ ለገጠሙት ችግሮች መፍትሔ ማግኘት አይቻለውም!
መሬት ለአራሹ!
በኣስራ ዘጠኝ ስልሳዎቹ ኢትዮጵያ ደምቃ ነበር። የለውጥ ጥም ይዟት ትጮህ ነበር። መቼም በየሃገሩ ኣገራዊ ችግሮችን መልክ ኣስይዞ፣ መሪቃል ወይም መፈክር ኣውጥቶ ለውጡን የሚመራውና የለውጥ ሃይል የሆነው ወጣቱ ሲሆን በተለይ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ሁሌም ቀዳሚዎች ናቸው። ታዲያ በዚያ የለውጥ ወራት ጊዜ ከነበረው ኣንዱና ትልቁ ጥያቄ የመሬት ላራሹ ጉዳይ ነበር ኣሉ። መሬት ላራሹ! መሬት ላራሹ! መሬት ላራሹ!……… ወጣቱ ድምጹን ኣሰማ ። ኣራሹ ማን ነው? ያውጭሰኛውና መሬት የለሹ ዜጋ ነዋ። በጥቂት የመሬት ከበርቴዎች እየተጨቆነ የሚኖረው የሰፊው ድሃ ህዝብ ግፍ ይብቃ፣ ኣዲስ ዘመን መጥቷልና እናንተ የመሬት ከበርቴዎች ሆይ በቃችሁ። ኣራሹ ገበሬ እጣው በሆነችው በዚህች ኣገር ውስጥ፣ የርስቱ ገመድ በወደቀባት በዚህች ምድር ላይ መሬት ይኑረው ነው ጥያቄው። በርግጥ ይህ ጥያቄ በጥሩና ሳይንሳዊ … [Read more...] about መሬት ለአራሹ!
“ደሞዝ የከፈለ ማዘዝ ይችላል” የሚለው አባባል በፖለቲካ ይሰራል
እንደ ሰላማዊ ትግል ተማሪ ከህዳር ወር መጀመሪያ ግድም አንስቶ እስከ ታህሳስ ወር አጋማሽ 2008 ድረስ የተካሄደውን የኦሮሚያ ተማሪዎች ሰላማዊ ትግል በቅርብ ስከታተል ነበር። የሰላማዊ ትግሉ መልዕክት “የኦሮሚያን መሬት አስመልክቶ የፌደራል እና የክልል መንግስት የወጠናችሁትን እቅድ እናውቃለን ። እኛ ለእቅዳችሁ ትብብር አንሰጠውም፣ አናጸድቀውም፣ እንቃወመዋለን። እኛን እንደ ተመልካች ማየታችሁን አቁማችሁ አዳምጡን። የመሪታችን ባለቤቶች እኛ መሆናችን ተገንዝባችሁ አነጋግሩን፣ በውሳኔ መስጠቱ ሂደት አሳትፉን። የመሪታችን ተጠቃሚነት መብታችንን እወቁ።” የሚል ነበር። ካለምንም ጥርጣሬ፣ ንቀት እና እብሪት ሰልፈኞቹ የሚናገሩትን ላደመጠ እና ያነገቡዋቸውን ጽሑፎች ላነበበ ሰው የሰልፈኞቹ መልዕክት ግልጽ ነበር። ጥያቄው እጅግ በጣም ቀላል ነበር። ምንም ውስብስብነት አልነበረውም። መንግስት … [Read more...] about “ደሞዝ የከፈለ ማዘዝ ይችላል” የሚለው አባባል በፖለቲካ ይሰራል
“ፕሮፌሰር፣ ጄኔራል” ሳሞራ
ረቡዕ በተሰማው ዜና መሠረት የቻይናው ቲያንጂን የቴክኖሎጂና ትምህርት ዩኒቨርሲቲ ለሳሞራ የኑስ የክብር ፕሮፌሰርነት ማዕረግ ሰጥቷል፡፡ ሚያዚያ 1999 የዖጋዴን ብሔራዊ ነጻ አውጪ ግምባር በክልሉ በሚገኝ የነዳጅ ፍለጋ ቦታ ላይ ባደረሰው ጥቃት ከ70 በላይ ንጹሃንን በገደለበት ወቅት ዘጠኝ ቻይናውያን ከሞቱት መካከል ነበሩ፡፡ በትግራይ ህዝብ ነጻ አውጪ ግምባር አዛዥነት በየጊዜው በዖጋዴን ሕዝብ ላይ የሚደርሰውን ጥቃት ሲቃወም የነበረው ኦብነግ ለወሰደው ድንገተኛ እርምጃ በሟቹ መለስ የሚመራው ህወሃት በክልሉ አምስት ቦታዎች ማለትም በፊቅ፣ ቆራሄ፣ ጎዴ፣ ዋርድሄር እና ደጋሃቡር ዘግናኝ የሆነ የመልሶ ማጥቃት ጭፍጨፋ በነዋሪው ሕዝብ ላይ አድርሷል፡፡ የሰብዓዊ መብት ተሟጋቹ ድርጅት (ሂውማን ራይትስ ዎች) ባወጣው ዘገባ መሠረት ኦብነግ ላደረሰው የአጸፋ መልስ እና ታጣቂዎችን ለመደምሰስ … [Read more...] about “ፕሮፌሰር፣ ጄኔራል” ሳሞራ










