ለሞረሽ የዐማራ ድምፅ ሬድዮ ሥርጭት መጀመር የሚያግዘንን ገንዘብ በተከታታይ እርዳታ መጠየቂያ። ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት ማስታወቂያና የሕዝብ ግንኙነት … [Read more...] about ለሞረሽ የዐማራ ድምፅ ሬድዮ አገልግሎት የገንዘብ እርዳታ ጥየቃ ማስታወቂያ
Opinions
“ለሕዝብ ይፋ ካላደረጋችሁት የፋይናንስ ሪፖርቱን እሰጣችኋለሁ”
የሆላንድ ዜምብላ ጋዜጠኞች የኦሮሞ ጸሃፊው የሆነውን ያሶ ካባባን ይዘው ወደ ጊንጪ ያመራሉ። እግረመንገድ ላይ የሚያገኟቸው ገበሬዎችም ሲጠይቋቸው በምስሉ ይታያል። እነዚያ በቀያቸው ማረፍያ እንኳን የሌላቸው ገበሬዎች የጋዜጠኞቹን መኪና ከብበው እንዲህ ሲሉ ይደመጣሉ። "መሬታችንን ቀምተው ለነጮች ሰጡብን። እኛንም በታተኑን..." በገዛ ቀያቸው ስደተኛ የሆኑ እነዚህ ወገኖቻቸን ሰቆቃቸው የከፋ ነበር። በመጨረሻ ተሰባሰቡና መከሩ። ሰባት ሺህ የሚሆኑ የጊንጪ ተወላጆች ሆ! ብለው ወጥተው ይህንን የሁለት ሚሊዮን ዩሮ (ሃምሳ ሚልዮን ብር) ንብረት በሰኮንዶች ውስጥ አወደሙት። ምስላቸውን ለካሜራ ሳይደብቁ፣ ስሜታቸውን እና የወደፊት እቅዳቸውን ይናገራሉ። "ከአምባገነን መንግስት ጋር አብሮ ከመስራት ይልቅ የአካባቢው ነዋሪዎች ሊጠቀሙ በሚችሉበት መንገድ መስራት እንደሚችሉም" ለፈረንጆቹ ይመክራሉ። … [Read more...] about “ለሕዝብ ይፋ ካላደረጋችሁት የፋይናንስ ሪፖርቱን እሰጣችኋለሁ”
የሽብርተኛ ትርጉም
የሚማር የለም እንጂ የሚማር ቢኖር የሽብርተኛነትን ትርጉም ሰሞኑን በቤልጂክ እያየንና እየሰማን ነው፤ በኢትዮጵያ ያሉ የእውቀት ምልክቶችን በዶላር እየገዙ ስማቸው ላይ የለጠፉ ጉልበተኞች ተናገርክ(ሽ) ብለው ብቻ ሳይሆን አሰብህ(ሽ) ብለው ሰፋፊ እስር ቤቶች እያሰሩ ወጣቶችን ሲያጉሩበት ምክንያታቸው ሽብርተኛነት ነው፤ ሽብር ማለት ሰሞኑን በቤልጂክ አውሮጵላን ጣቢያና በባቡር ጣቢያ ላይ እንደታየው ከሆነ ኢትዮጵያ ውስጥ አልታየም፤ ከታየም በአገዛዙ ኃይሎች የተፈጸመ ነው፤ ለብዙ ዓመታት ሲፈጸም የቆየ ነው፤ የኢትዮጵያ ጉልበተኞች ከቻሉ ሊያስተውሉት የሚገባ አንድ ነገር አለ፡- ሽብርም ነጻነትን ይፈልጋል፤ በቤልጂክ ሽብሩን የፈጸሙት ሁሉ ነጻነትን ፈልገው ከአገራቸው የተሰደዱና በአገራቸው ያላገኙትን ነጻነት በሰው አገር እየተሞላቀቁበት እንደሆነ የሚያመለክት ነው፤ ትርጉሙ፡- ነጻነት በሌለበት … [Read more...] about የሽብርተኛ ትርጉም
የስልጣን ተስፈኛ ፖለቲከኞች
የኢህአዴግ የቁርጥ ቀን ልጅ ልደቱ አያሌውና ፓርቲው ኢዴፓ ባዲስ ትርፍ የፓርላማ መቀመጫ ፍለጋ ሰሞኑን ከእንቅልፋቸው መንቃታቸውን ሰምቼ ትንሽ ተገረምኩ። በውል ያልተደነቅሁበት ምክንያት ኢዴፓንና ሌሎች በኢህአዴግ-ወለድ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ም/ቤት ውስጥ የታጨቁ የስልጣን ተስፈኞች እንጂ ፖለቲካ የሚያውቁ ቁርጠኛ ተቃዋሚዎች ናቸው ብዬ ስለማላውቅ ነው። ደግነቱ ደግሞ ነገሩ እውነት መሆኑ ነው። እነዚህ ኢህአዴግ በልካቸው በሰራላቸው ጉረኖ ታሽገው በኢትዮጵያ ህዝብ መስዋእትነት ስልጣን ለመቀላወጥ በተስፋ የሚያደቡት ኢዴፓና አጃቢዎቹ ሰሞኑን የኢህአዴግ ዙፋን ሲነቃነቅ በፈጠረው የፖለቲካ ስንጥቅ ለመሰካት በጠቅላይ ሚንስትሩ እግር ስር ወድቀው ትራፊ ወንበር እንዲረጥቧቸው ልመና መጀመራቸውን ሰምቼ አፈርኩባቸው። የኢዴፓ ሊቀመንበር ዶክተር ጫኔ ከበደ አርብ መጋቢት 16 ቀን 2008 ዓም ለአሜሪካ … [Read more...] about የስልጣን ተስፈኛ ፖለቲከኞች
በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች
ገዢው አምባገነን የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት በየዕለቱ በሚያደርገው ፀረ-ኢትዮጵያዊ ተግባር፤ የተለያዩ የፖለቲካ ሕዝባዊ ስብስቦች መግለጫ ያወጣሉ። አዳዲስና ነባር የፖለቲካ ድርጅቶች፤ አለን በማለት ስማቸውን በአንባቢዎች ያስመዘግባሉ። ለመሆኑ ጋዜጣዊ መገለጫዎች ለምንድን ጉዳይ ነው የሚወጡት? ማነው የሚያወጣቸው? መግለጫዎችን ተከትሎ የሚተገበሩት ምንድን ናቸው? አሉስ ወይ? መግለጫ አውጪዎቹና መግለጫ ያላወጡ የፖለቲካ ሕዝባዊ አካሎች መለያቸው ምንድን ነው? መግለጫዎችና አውጪዎቻቸው፤ ሕዝባዊ ናቸው ወይንስ ጠባብ ወገንተኛ? መልዕክት አላቸው ወይንስ አደረግሁ ለማለት የተወረወሩ? አስፈላጊነታቸውስ ምን ያህል ነው? በተደጋጋሚ ጋዜጣዊ መግለጫ በተንጎደጎዱ ወቅት የደረሱኝ እጦማሮች ነበሩ። ሁሉም ወቀሳዎች ናቸው። “ለምን መግለጫ አታወጣም?” “ካሁን በፊትም ዝም ብለሃል!” የሚሉና … [Read more...] about በመቶዎች የሚቆጠሩ ጋዜጣዊ መግለጫዎች
Leadership Gap: The main reason why we keep failing to topple dictatorship
In the last couple of decades, people around the world fought and toppled dictators. Courageous Africans removed dictators from Benin, Zambia, and Ghana in the 90’s and early 2000. The Arab Spring that took place in the northern African countries such as in Tunisia, Egypt, and Libya ousted despots.Likewise, successful revolutions in Asia like the one in Philippines (Yellow Revolution)that took place in 1986 overthrew President Ferdinand Marcos. In the beginning of the new century, Rose, Orange, … [Read more...] about Leadership Gap: The main reason why we keep failing to topple dictatorship
ሞረሽ የዐማራ ድምፅ የሬድዮ ጣቢያ ማቋቋም ለምን አስፈለገ?
ባለፉት ፳፭(ሃያ አምሥት) ዓመታት በዐማራው ላይ የሚፈጸመው የዘር ማጥፋት እና የዘር ማጽዳት ዘመቻ ከችግሩ ሥፋት እናጥልቀት አንፃር ተመጣጣኝ የሆነ የሚዲያ ሽፋን አልተሰጠውም። በ«ኢትዮጵያዊነት» ስም በተቋቋሙት ድርጅቶችም ሆነ በተለያዩ አገሮች መንግሥታት ሥር የሬድዮ እና የቴሌቪዥን መርኃ-ግብሮችን በአማርኛ ቋንቋ የሚያሠራጩ ሚዲያዎች በዐማራው ላይ የሚፈጸመውን ግፍ እና በደል የዓለም ማኅበረሰብ እንዲያውቀው የማድረግ ፈቃደኝነታቸው እጅግ ውስን መሆኑን በተደጋጋሚ ታይቷል። ይህም «ችግሩ ችግራችን ነው» ብሎ የሚይዝ ሚዲያ አለመኖሩን ያረጋግጣል። ስለሆነም እኛ የሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት አባሎች እና ደጋፊዎችለመላው የዐማራ ሕዝብ ድምጽ የሚሆን የሬድዮ ጣቢያ ለማቋቋም ቆርጠን ተነስተናል። ዐማራው በተገንጣይ እና ጠባብ የጎጠኞች ቡድኖች የተክፈተበትን የሥነ-ልቦና ጦርነት ተመጣጣኝ በሆነ … [Read more...] about ሞረሽ የዐማራ ድምፅ የሬድዮ ጣቢያ ማቋቋም ለምን አስፈለገ?
ሀላፊነት እወስዳለሁ ማለትና ይቅርታ በተግባር መተርጎም አለበት
ጠቅላይ ሚኒስቴር ሐይለማርአም ደሳለኝ ከጥቂት ቀናት በፊት ለፓርላማው ባቀረቡት ዘገባ ውስጥ ጨምረው በሀገራችን ባሁኑ ሰአት በተለይም በኦሮሚያና በአማራ ክልሎች ጎልቶ የሚታየውን የህብዝን መነሳሳት ከመልካም አስተዳደር መጥፋትና ከስርአቱ ብልሽት ጋር የተያያዘ እንደሆነ ለተፈጸመው በደል ተጠያቂ እንደሆኑም አምነው "ይቅርታ" ጠይቀዋል። (የመግለጫው ሙሉ ቃል እዚህ ላይ ይገኛል)። … [Read more...] about ሀላፊነት እወስዳለሁ ማለትና ይቅርታ በተግባር መተርጎም አለበት
ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ ለኢትዮጵያውያን የቢሊዮኖች ዶላር ካሣ ይጠይቃል
ጋ ዜ ጣ ዊ መ ግ ለ ጫ መጋቢት 7 ቀን 2008 ዓ/ም Garland, Texas: (ጋርላንድ፤ ቴክሳስ)፡ ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ - የኢትዮጵያ ጉዳይ፤ መንግሥታዊ ያልሆነ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የኢኮኖሚና የማሕበራዊ ጉዳዮች አካል ውስጥ የተመዘገበ ተቋም ነው። በዚህ ሳምንት በኢትዮጵያ እየተከናወነ በሚገኘው የኢጣልያ ፕሬዚዳንትና ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ጉብኝት አጋጣሚ ጊዜ የድርጅታችን ዓላማ የኢጣልያ መንግሥት እ.አ.አ. በ1928-33 ዓ/ም በኢትዮጵያ ላይ ለፈጸመው የጦር ወንጀልና የሰው እልቂት ተገቢው ፍትሕ እንዲገኝና ከኢትዮጵያ የተዘረፈውን ኢጣልያ፤ የቫቲካን ቤተ መጻሕፍትና ሌሎችም እንዲመልሱና እንዲክሱ ለማድረግ ነው። በ1928-33 ዓ/ም ኢጣልያ በኢትዮጵያ ላይ በፈጸመችው ጦርነት፤ ፋሺሽቶች በአውሮፕላኖች አማካኝነት በነስነሱት የመርዝ ጋዝ ጭምር የብዙ ሰው … [Read more...] about ዓለም አቀፍ ሕብረት ለፍትሕ ለኢትዮጵያውያን የቢሊዮኖች ዶላር ካሣ ይጠይቃል
በርሀብ የሚገድል መንግሥት እንዴት በሥልጣን ላይ ይቆይ?
ታላላቅ ረሀቦች ተብለው በዓለም ታሪክ ከሚዘከሩት ውስጥ የቻይናውያን ረሀብ ኣይዘነጋም። እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር ከ1958-1961 ድረስ ቻይና ውስጥ ከፍተኛ ረሀብ ተከስቶ ወደ ሰላሳ ሚሊዮን ህዝብ ረግፏል። ብዙ ምሁራን እንደሚሉት ለዚህ አስከፊና ቻይናውያን ሊረሱት ለማይችሉት ረሀብ አንደኛ ተጠያቂ ማዖ ዚዳንግን ነው። የኮሙኒስት ፓርቲ መሪ የነበረው ማዖ ዚዳንግ በሶቪየት ህብረት በነጆሴፍ ስታሊን አብዩት ፍቅር የከነፈ ሲሆን ቻይናን በአምስት ዓመታት ውስጥ ከሁዋላ ቀር ግብርና አውጥቼ ወደ ኢንዱስትሪ እለውጣታለሁ በማለት Great Leap Forward ታላቁ የግስጋሴ ርምጃ የተሰኘ የአምስት ዓመት የትራንስፎርሜሽን እቅድ ነድፎ አመጣ። እቅዱ የግል የመሬት ባለቤትነትን የሚጻረርና የወል እርሻን የሚያራምድ ነበር። በዚሁ እቅድ መሰረት ቻይናውያን በፍጥነት እየተደራጁ የወል እርሻ ሥራን … [Read more...] about በርሀብ የሚገድል መንግሥት እንዴት በሥልጣን ላይ ይቆይ?










