• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የሽብርተኛ ትርጉም

March 31, 2016 01:31 am by Editor 1 Comment

የሚማር የለም እንጂ የሚማር ቢኖር የሽብርተኛነትን ትርጉም ሰሞኑን በቤልጂክ እያየንና እየሰማን ነው፤ በኢትዮጵያ ያሉ የእውቀት ምልክቶችን በዶላር እየገዙ ስማቸው ላይ የለጠፉ ጉልበተኞች ተናገርክ(ሽ) ብለው ብቻ ሳይሆን አሰብህ(ሽ) ብለው ሰፋፊ እስር ቤቶች እያሰሩ ወጣቶችን ሲያጉሩበት ምክንያታቸው ሽብርተኛነት ነው፤ ሽብር ማለት ሰሞኑን በቤልጂክ አውሮጵላን ጣቢያና በባቡር ጣቢያ ላይ እንደታየው ከሆነ ኢትዮጵያ ውስጥ አልታየም፤ ከታየም በአገዛዙ ኃይሎች የተፈጸመ ነው፤ ለብዙ ዓመታት ሲፈጸም የቆየ ነው፤ የኢትዮጵያ ጉልበተኞች ከቻሉ ሊያስተውሉት የሚገባ አንድ ነገር አለ፡- ሽብርም ነጻነትን ይፈልጋል፤ በቤልጂክ ሽብሩን የፈጸሙት ሁሉ ነጻነትን ፈልገው ከአገራቸው የተሰደዱና በአገራቸው ያላገኙትን ነጻነት በሰው አገር እየተሞላቀቁበት እንደሆነ የሚያመለክት ነው፤ ትርጉሙ፡- ነጻነት በሌለበት ሽብር አይኖርም፤ እንዴት ብሎ? የት ተደብቆ? የት ሸምቆ?

ሽብርን የጸነሰውን እንዳያስብ አፍኖ፣ እንዳይናገር አንደበቱን መርጎ፣ እንዳይንቃሳቀስ በዳኛ ትእዛዝ ወህኒ ቤት ውስጥ ቆልፎ ሽብርን ማቆም አይቻልም፤ የሚቻለው፣ እየሆነ ያለውም ዝንባሌው ያላቸው ኢትዮጵያውያን ለሽብር ትምህርት ወደአውሮፓና ወደአሜሪካ እንዲሄዱ የሚገፋፋቸው ነው፤ የዚህን ግፊት ውጤት የኢትዮጵያ ጉልበተኞች የሚወዱት አይመስለኝም፤ መጠቃት እንደማጥቃት አያስደስትም!

የእኛ ጉልበተኞች ሽብር ምን እንደሆነ አያውቁም፡፡

የእኛ ጉልበተኞች በንግግርና በተግባር መሀከል ያለውን ልዩነት አያውቁም፤ በቤልጂክ ሽብር የተባለው ሠላሳ አንድ ያህል ሰዎች የሞቱበት፣ ወደሦስት መቶ ሠላሳ ያህል ሰዎች የተጎዱበት ነው፤ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲህ ያለ ነገር ደርሶ ያውቃል? እንዴታ! በዙ ጊዜ፤ ግን ሽብርተኞች በተባሉትና በታሰሩት አይደለም፤ በተመቻቸውና ሕግ በማይደርስባቸው ሌሎች ጉልበተኞች የተፈጸመ ነው፡፡

የእኛ ጉልበተኞች በፍርሃት የደነዘዘው አንጎላቸው ዓይናቸው እውነቱን እንዲያይ፣ ጆሮአቸው እውነትን እንዲሰማና ልባቸው ወደመወያየትና ወደእርቅ እንዲያቀና አያደርጋቸውም፤ ወላጆቻቸውን ንቀው ብቻቸውን የቆሙ ስለሆኑ መካሪ የላቸውም፤ መንፈስ ስለሌላቸው መንፈሳዊ አባት የላቸውም፤ ያሳዝናሉ፡–

ሀሳቤን አንዱ ግጥሜ ይገልጽልኛል መሰለኝ፡– የሞተ ኅሊና

የማይጣላ ኅሊና ያለው

እንዴት የታደለ ነው!

እግዜር ብቻ ነው ኅሊና የሌለው፤

የማይሳሳት የማየወቆጨው፡፡

ሰው ሰውነቱ፣ ጭንቀቱና ልፋቱ፣

ኅሊናው ከስሜቱና ከፈላጎቱ መጣላቱ፣

የሚረሳ የሚሳሰት፣ የማይታየው የፊቱ፣

የሚወድ፣ የሚጠላ፣ የሚፈራ፣ ኧረ ስንቱ!

ከሳሽ፣ ተከሳሽ፣ ዳኛ መሆን

እንዴት ይችላል መበየን?

ሲያፍነው ግን ኅሊናውን

አይለይም ጨለማውን ከብርሃን!

ኅሊናውን ገደለ ሰው

ማን ሊቀረው? ምን ሊያቅተው?

የጉልበቱ መሣሪያ ነው፤

ጊዜ ጉልበቱን እስቲሰብረው! … …

እውነተኞቹ ሽብርተኞች በኢትዮጵያ ውስጥ ካሉ ከሥልጣን ውጭ አይደሉም፤ ከሥልጣን ውጭ ሆነው ቅራኔ የሚያሰሙ ጉልበታቸው እዚያው ላይ ያበቃል፤ በምድረ ኢትዮጵያ ሽብርን መቃወም ሽብርተኛ ያደርጋል፤ ወህኒ ያስገባል፤ ተመስገን ደሳለኝ፣ እስክንድር ነጋ፣ አብርሃ ደስታ፣ … በወህኒ ቤት የሚማቅቁት ቅንጣት የሚያህል የሽብር ተግባር ፈጽመው አይደለም፤ ሽብር እንዳይፈጸም ስለታገሉ ነው፤ ሽብር ከነገሠ ሰላም ወንጀል ይሆናል፤ በኢትዮጵያ ሰላም ዋጋ እያጣ መሄድ ላይ መሆኑን የሚጠራጠር የለም፤ ከባሕር ማዶ የተጀመረው ቀረርቶ ወደተግባር ሲለወጥ መፍራት ፋይዳ የለውም፤ ለጉልበተኞቹ የሚያዋጣው የፍርሃት ጊዜው አሁን ነው! እንደሳዳም ሁሴንና እንደጋዳፊ እንደአይጥ ከተሸጎጡበት ስርቻ እየተጎተቱ ሲወጡ አይደለም፡፡

መጋቢት 2008

(ምንጭ: Mesfin Wolde-Mariam Blog)

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Comments

  1. eunetu says

    April 13, 2016 05:47 pm at 5:47 pm

    እጅግ የማከብርዎትና የምወድዎት የተከበሩ ፕ/ር መስፍን
    ከእርስዎና ከመሳሰሉት ለራሳቸው ከማይኖሩ ስጦታዎቻችን
    የመማር ልብ የሌለው ሰው በምድሪቷ ላይ የሌለ ቢመስልም
    አንዳንዶቻችን ስለእውነት መኖር ማለት ምን ማለት እንደሆነ
    ከኢየሱስ ክርስቶስ ወንጌል ቀጥሎ ከእርስዎ ተምረናል!
    እየተማርንም ነውና የዘመናት ጮኸትዎ ባዶ እንዳልቀረ
    ላረጋግጥልዎ እወዳለሁ!!! እንዲያውም ከ 12 ዓመት
    በፊት ስለየወት ”ካለመጽሐፍ ቅዱስ ወንጌል ሰባኪ ወንጌላዊ” ብየ
    በአንድ አርቲክል ላይ ስም አውጥቼልዎት ነበር!!!ከተቀበሉኝ
    ታዲያ ወንጌል ቢጨመርበት ምን ይሆን እንደነበር እንገምት???
    ጤ ና ዎ ት ን እግዚአብሔር ይጠብቅ !!!

    በሐርያት ሥራ 8፡26 ላይ የተገለጸው ኢትዮጵያዊው ጃንዳረባ የንግሥቲቷ ባለሟል ሆኖ ሳለ ለመሳለም ሩቅ መንገድ ቢጓዝም እንደማያውቅ ተረድቶ የሚያነበው የሕይወት መጽሐፍ እንዳልጋባው በግልጽነት በመናገሩ ለችግሩ መፍትሔ በማግኘት ደስተኛ ሆነ። ከዚህ በሳልና የግል ስም እያለው ኢትዮጵያዊ ተብሎ ከተጠራ ሰው የምንማራቸው ሁለት ነገሮች፡ 1/ የሂሳብ ባለሙያ ቢሆንም የማይገባውን መጽሃፍ የሚያነብና አገር አቋርጦ በመሄድ ሊሳለመው የፈለገው ሁሉን ቻይ አምላክ በቦታ የማይወሰን እንደሆነ አለማወቁን ባለመደበቁ የደስታ ምንጭ የሆነውን እውቀት መቀበሉን፣ 2/ የተቀዳንበት እውተኛው ምንጭና ያሁኑ የእኛ ማንነት(አንዳችን ካንዳችን ከመማር ይልቅ ሁሉን አውቃለሁ ባይነት)ፈጽሞ የማይገናኝ በመሆኑ ይባስ ብሎ ኢትዮጵያ የሚለውን የጋራ መጠሪያ ስም መስማት የማይፈልግና የራሱን ታሪክ የማያውቅ አዋቂ ትውልድ ተነስቷል። ጉድ ያለው ገንፎ አድሮ ይፋጃል ይሏል ይሄ ነው!!!

    በእርግጥ አገራችን የአዋቂወች/ያስተማሪዎች ደሃ አይደለችም!እደግመዋለሁ አይደለችም!!! ከራሳችን ሰዎች ለመማር የቀና ልብ ስላጣን እንጂ! ወይም በሌላ ቋንቋ እንደ ኮከብ ብልጭ ሲሉ በብዙዎቻችን ውስጥ ባለው ጨለማ ለሞት አሳልፈን ስለምንሰጣቸው!(በደቂቀ እስጢፋኖስ መጽሐፍ ላይ እርስዎና ፕ/ር ጌታቸው ሃይሌ እንደገለጻችሁልን) ስለዚህ እኔ በበኩሌ ከነጭ አዋቂዎች ብቻ ሳይሆን እንደናንተ ካሉ አባቶቼ/ወገኖቼ በተለይ ማንነቴን የበለጠ ለመማር 100% ዝግጁ ነኝና እስከ ነፍስ ህቅታ ድረስ በርቱ! ደግሞም በነቢዩ ዳንኤል እንደሆነው ቅንነትን የራበው አንበሳ እንኳ አይበላውምና ከመምሸቱ በፊት በርቱ! በርቱ!! በርቱ!!!እናንተ አላዋቂ የሆናችሁ አዋቂ ወገኖቻችንም ቆም ብላችሁ አጠገባችሁ ካለው ወገናችሁ ተማሩ እንማር?ለነገሩ ተማር ያላለው በ40 ዓመቱም አይማርም! ይባል የለ!!! በእውነት ይህ አይሁንባችሁ!!!

    እግዚአብሔር የኢትዮጵያዊውን ጃንደረባ ልብ ይስጠን!!! የገባው አሜን ይበል?
    ፕሮፌሰሮቻችንም አሜን ብትሉ ታተርፋላችሁ እንጂ አትከስሩም።
    ፕ/ር መስፍን ትክክል አይደለሁም?

    እውነቱ /eunethiwot@gmail.com/ ነኝ
    እንድኖር ተፈቅዶልኝ ካለሁበት!

    Reply

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule