• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

የስልጣን ተስፈኛ ፖለቲከኞች

March 30, 2016 11:05 pm by Editor Leave a Comment

የኢህአዴግ የቁርጥ ቀን ልጅ ልደቱ አያሌውና ፓርቲው ኢዴፓ ባዲስ ትርፍ የፓርላማ መቀመጫ ፍለጋ ሰሞኑን ከእንቅልፋቸው መንቃታቸውን ሰምቼ ትንሽ ተገረምኩ። በውል ያልተደነቅሁበት ምክንያት ኢዴፓንና ሌሎች በኢህአዴግ-ወለድ የተቃዋሚ ፓርቲዎች ም/ቤት ውስጥ የታጨቁ የስልጣን ተስፈኞች እንጂ ፖለቲካ የሚያውቁ ቁርጠኛ ተቃዋሚዎች ናቸው ብዬ ስለማላውቅ ነው። ደግነቱ ደግሞ ነገሩ እውነት መሆኑ ነው። እነዚህ ኢህአዴግ በልካቸው በሰራላቸው ጉረኖ ታሽገው በኢትዮጵያ ህዝብ መስዋእትነት ስልጣን ለመቀላወጥ በተስፋ የሚያደቡት ኢዴፓና አጃቢዎቹ ሰሞኑን የኢህአዴግ ዙፋን ሲነቃነቅ በፈጠረው የፖለቲካ ስንጥቅ ለመሰካት በጠቅላይ ሚንስትሩ እግር ስር ወድቀው ትራፊ ወንበር እንዲረጥቧቸው ልመና መጀመራቸውን ሰምቼ አፈርኩባቸው።

የኢዴፓ ሊቀመንበር ዶክተር ጫኔ ከበደ አርብ መጋቢት 16 ቀን 2008 ዓም ለአሜሪካ ድምፅ ያማርኛው አገልግሎት በሰጡት ቃለምምልስ ተቃዋሚዎች በፓርላማ የውክልና ወንበር እንዲኖራቸው ለማድረግ ተስፋ እንደተሰጣቸው ያለሀፍረት ሲናገሩ ተደምጠዋል። እስቲ ማን ይሙት በዚህ ወቅት፣ ከአንድ የተቃዋሚ ፓርቲ የሚጠበቅ ይህ ነበር? ፊደል ያልቆጠረው ምስኪኑ የኢትዮጵያ ገበሬ ለዴሞክራሲና ፍትህ የድሃ ደሙን እያፈሰሰ ባለበት በዚህ ወሳን ወቅት የኛ ዶክተር ፖለቲከኞች ሊሞት በሚያጣጥር አምባገነን እግር ስር ወድቀው የፓርላማ ወንበር ይለምናሉ። መጥኔ አቦ! እንዴት ያለ ህሊና ቢኖራቸው ነው ጃል? በህዝብ ደም አሮጌ የስልጣን ወንበር መመኘት።

ክቡር የሆነውን የወገን ደም ማርከስ አይሆንም? እንደወጉ ቁርጠኛ ተቃዋሚ መሆን ባይሳካላቸውና ተፈጥሯቸው ባይፈቅድላቸው እንኳን ገላጋይ ሽማግሌ ለመሆን ቢጥሩ ምን ነበረበት? ህዝብ ለፍትህ ሲጮኽ ብትት እንኳን ሳይሉ የወንበር እርጥባን ሹክሹክታ እንዴት በአንድ ጊዜ አባነናቸው? ጉድ ነውመቼም!

ለነገሩ ይህ ፓርቲና አጋሮቹ ምን ጊዜም ኢህአዴግ ጭንቅ በገጠመው ጊዜ ሁሉ ደራሽና የቁርጥ ቀን አገልጋዮች በመሆናቸው ታሪካቸውን ለሚያውቅ ድርጊታቸው የሚያስገርመው አይሆንም። የቅንጅት ዘመን ሚናቸውን ያስታውሷል። ያኔም ቢሆን ሀገር የከዱት በስልጣን ጥምና ስግብግብ ፍላጎታቸው ነበር። ዛሬም ያው ልማደኛ የስልጣን አራራቸው ተነሳና የህዝብ አስከሬን ላይ ቆመው ስልጣን ይለምኑ ጀመር። አቤት ክፉ ቀን ስንት ክፉ ነገር ያሳያል? ይህን ከመሰሉ አርተፊሻል ተቃዋሚዎች ኢህአዴግ በስንት ጣዕሙ ጃል!

ዛሬ ኢትዮጵያ የምትገኝበት ሁኔታ ልዩ መፍትሄ የሚሻ ነው። አሁን ስልጣንና ወንበር በስሌት የምንከፋፈልበት ጊዜ አይደለም። አሁን ይህች ውብ ሀገር ከገጠማት የታሪክ ፈተና ለማውጣት ሁላችንም (ምናልባትኢህአዴግን ጨምሮ) ሌት ተቀን የምንጨነቅበት ወቅት ነው። ዛሬ ነባር የግልና የቡድን ጥቅማችንን እያሰላን ሆዳችን የሚጮኽበት ጊዜ ሳይሆን በምጥ ላይ የምተገኘውን ሀገራችንን ካንቺ በፊት ያርገኝ የምንልበት ፈታኝ ወቅት ነው። እናም ኢደዓዊያን፣ እባካችሁ ህሊና ግዙ። ይሉኝታም ያስፈልጋል። ሀገር ሰላም ከሆነ ሌት ተቀን የሚያቃዣችሁ የስልጣን ሱስ የሚረካበት ጊዜ ሊመጣ ይችላል። ሀገር ከወደቀች ግን ከነቅዠታችሁ ትቀበራላችሁና አስቡበት። ቢቻል የህዝብን ጩኸት ችላ ብላችሁ በጓሮ በር ስልጣን ለመቀላወጥ ያደረጋችሁት ሙከራ አሳፋሪ ነውና በይፋ ይቅርታ ጠይቁ። ይህ ጨዋነት የማይሆንላችሁ ከሆነ ደግሞ ለገዛ እናታችሁ ቀብር መቆፈር የጀመራችሁትን ቁፋሮ አቁሙ። ኢህአዴግም ይታዘባችኋል። ይህ ካልሆነ ዛሬ ለኢትዮጵያ በቆፈራችሁት ጉድጓድ እናንተው ትገቡበታላችሁ። በጭንቅ ቀን ሀገሩን የከዳ ዋጋው ከዚህ ያነሰ ሊሆን አይችልም። ልቦና ይስጣችሁ! አሜን።


“ጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ የሕዝብ” እንደመሆኑ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ ሥር የድርጅቶችና የማንኛውም ግለሰብ ነጻ ሃሳብ የሚስተናገድ ሲሆን ከአንባቢያን የሚላኩልን ጽሁፎች በጋዜጣው የአርትዖት (ኤዲቶሪያል) መመሪያ መሠረት ያለ መድልዖ በዚህ ዓምድ ሥር ይታተማሉ። ይህ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ በ“የኔ ሃሳብ (Opinion)” ዓምድ የታተመ ጽሁፍ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® አቋም ሳይሆን የጸሃፊው ነው።

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule