ከባርነት ሞትን የመረጥከው ወንዱ፣ አፉን ክፍት አርጎ የዋጠህ መቃብሩ፣ የማዋይህ አለኝ ስማኝ ሰማእቱ፡፡ የፈሰሰው ደምህ በህልሜ እየታየኝ፣ አጥንትህ ከመቃብር እየጎራበጠኝ፣ እሾህ ቀጋ ሆኖ አላስተኛህ አለኝ፡፡ ለፍትህ ስትጮህ የቀረኸው ባጭር፣ ጎንደር ደብረታቦር ወልድያ ባህርዳር፣ ቡሬና ዳንግላ ማጀቴና አቸፈር፣ ዛሬም ወንድሞችህ ታስረዋል ግዮን ዳር፡፡ በስናይፐር የፈጁህ ህሊና ቢሶቹ፣ ለውጥ አመጣን ብለው ያንኑ ደገሙ፣ አንድ አስገዳይ ነቅለው ሌላውን ተከሉ፡፡ አጥንትህን ከአምቦ ከእሬቻ ለቃቅሞ፣ መሰላል አረገው ከለማ ጋር ሰርቶ፡፡ በስንት በጎች ደም እንደተነከረ፣ እጁን ሳይታጠብ አቢይ ቀደሰ፡፡ ኢያሱና ሙሴን ተከተሉ እያሉ፣ ስንቱን ዘልዛላ እንከፍ ከጀርባ አሰለፉ፡፡ ተመራጩ አስገዳይ መራጩም ገዳይ ነው፣ የሌላው ማሽቃበጥ ምን … [Read more...] about ስማኝ ሰማእቱ!
QUE SERA SERA!
Whatever will be, will be! Ethiopia has a new Prime Minister. Actually we never had Prime Ministers so far, for the last almost 27 years but Prime Miseries. None of them talked before, about Ethiopia. Dr Abiy Ahmed Ali talked about Ethiopia. That does sound like the Prime Minister of Ethiopia. Does it? Time will tell. Que sera sera! I have never called the Woyyane House of Cards, the EPRDF, by its fake name. For me, EPRDF was just a cover coat. The real body inside was the TPLF, or the … [Read more...] about QUE SERA SERA!
“(ዓብይ) ብዙ ቃል የገባቸውን ጉዳዮች ፈጽሟል”
ማክሰኞ መጋቢት 18 ቀን 2010 ዓ.ም. ምሽት እኩለ ሌሊት እየተቃረበ እያለ የተሰማው ሰበር ዜና በአገር ውስጥና በውጭ የሚገኙ ኢትዮጵያዊያንን ያነጋገረ ነበር፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከኢሕአዴግ ሊቀመንበርነታቸውና ከጠቅላይ ሚኒስትርነታቸው በገዛ ፈቃዳቸው ለመልቀቅ መወሰናቸውን ይፋ ካደረጉ በኋላ፣ ተተኪያቸው ማን ይሆን የሚለው በመላ አገሪቱ ዋነኛ መነጋገሪያ እንደነበር አይዘነጋም፡፡ በተለይ ማክሰኞ መጋቢት 11 ቀን 2010 ዓ.ም. ተተኪውን የግንባሩን ሊቀመንበር ለመምረጥ ስብሰባ የተቀመጠው የኢሕአዴግ ምክር ቤት ለአንድ ሳምንት በመቆየቱ፣ በርካቶች በመላ ምቶችና በሴራ ንድፈ ሐሳቦች እንዲጨናነቁ አድርጓቸዋል፡፡ የአገሪቱ ፖለቲካ ለትንተና እስከሚያስቸግር ድረስ የተለያዩ መረጃዎች ከተለያዩ አቅጣጫዎች በመሰማታቸው፣ የተተኪው ማንነት ብዙዎችን ቢያሳስብ አይገርምም … [Read more...] about “(ዓብይ) ብዙ ቃል የገባቸውን ጉዳዮች ፈጽሟል”
ህዝባዊ ትግል መቀጠሉ ነው ዋስትናው
የተደራጀ ኃይል ወደተሻለ ዴሞክራሲያዊ ስርዓስት ያደርሰኛል ብሎ ብዙ የጠበቀውና መስዋዕት ሲከፍል የኖረው የኢትዮጵያ ህዝብ ዛሬ በራሱ አመፅ የትግሉ ባለቤት ሆኗል። በኦሮምያ፣ በአማራ፣ በደቡብና በተለያዩ ቦታዎች በአምባገነኖች ጥይት ግንባራቸው እየተመታ የወደቁት፣ በእስር የሚማቅቁት፣ ተፈናቅለው የተሰደዱት ሁሉ የዚህ ወይንም የዚያ ድርጅት አባላት አይደሉም። በተቃውሞ ሰልፍ፣ በመንገድ መዝጋት፣ቤት ውስጥ በመቀመጥ፣ የነዳጅ ትራንስፖርት በማገድ፣ ሱቅ በመዝጋት፣ ግብር ባለመክፈል፣ ትጥቅ ላለመፍታት ገድሎ በመሞት፣ በኳስ ሜዳዎችና በህዝባዊ ስብሰባዎች ዘራፊ አምባገነኖችን በማጋለጥ፣ በመደበኛና በሶሻል ሚድያ ቅስቀሳ በማድረግ ስርዓቱን የሚይዘውና የሚጨብጠው ያሳጣው በዚህ ወይንም በዚያ ድርጅት አመራር የሚንቀሳቀስ አካል ብቻ አይደለም። የዘመናት ብሶት ያደቀቀው በቃኝ ብሎ ለተመሳሳይ ዓላማ … [Read more...] about ህዝባዊ ትግል መቀጠሉ ነው ዋስትናው
ከዶ/ር አብይ ንግግር ትኩረት የሳቡ ነጥቦች
በዶ/ር አብይ የሹመት ንግግር ውስጥ፤ ይቅርታ፣ እርቅ፣ ካሳ፣ ዲያስፖራ፣ ኤርትራ፣ ሙስና፣ ተቀናቃኝ ሃይሎች፣ የባከነ እድል፣ ስለ ዘረኝነት በሽታ እና የኢትዮጵያ ታላቅነት ተነስተዋል። “በቅጡ ሳይቧርቁ ሕይወታቸው ለተቀጠፈ ለውጥ ፈላጊ ወጣቶች ለስነ-ልቦናዊ እና አካላዊ ቀውስ ለተዳረጉ ቤተሰቦችና ግለሰቦች ከልብ የመነጨ ይቅርታ እጠይቃለሁ" ሲሉ ጀመሩ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ። በተለያየ ግዜያት መስዋዕትነትን ለከፈሉ፤ የመብት ተከራካሪዎች እና የፖለቲካ ስዎች ለደረሰው ጉዳት፣ ለፈሰሰው ደም እና ለጠፋው ህይወት፤ ይቅርታ ብቻ ብለው አላለፉም። ለተፈጠረው ችግር እልባት፤ ለተበደለ ወገን ደግሞ ካሳ እንደሚከፍሉም ተናግረዋል። “ከስህተታችን ተምረን ሃገራችንን የምንክስበት ወቅት ነው!” ማለታቸው ራሱ ንግግራቸውን በተግባር ለመተርጎም ያላቸውን ቁርጠኝነት አጉልቶ ያሳየናል። የመርህ … [Read more...] about ከዶ/ር አብይ ንግግር ትኩረት የሳቡ ነጥቦች
ዘብ ቆመናል ክቡር የኢትዮጵያ ልጅ ዶ/ር አብይ አህመድ
ሁላችንም ካለንበት አጣብቂኝ ውስጥ መውጫ መንገድ አጥተን ተፋጠን ሰንብተናል። ስንነካከስ እንዳንጠፋፋ በሚያስፈራበት መልኩ ሁላችንም ግብ ግብ ስንገጥም እዚህ ደረስን። መንግስት በጉልበቱ ሲገፋበት፥ ሕዝብ በአመፁ ሲዘልቅበት፥ አማራጭ ኃይል በሁሉ አቀፍ ትግሉ ሲዘምትበት፥ አካሄዱ ሁሉ ሲያስፈራ የኢትዮጵያ ዕጣ ፈንታ ምን ይሆን ያሰኝ ነበር። ሕዝቡ ሁሉ በሁሉም አቅጣጫ ወደ አምላኩ ከመጮህ አልተቆጠበም። በአራቱም አቅጣጫ አንድነቷን እና ብልጽግናዋን በማይወዱ የተከበበች ሀገር ሆና ሳለ፥ ከውስጥ ደግሞ በነውጥ ስትናጥ ተስፋዋ እየመነመነ ጫፍ ደርሶ ነበር። ምን አልባት ታዲያ የማታ ማታ ፈጣሪዋ ኢትዮጵያን ከምጥ ሊገላግላት፣ ውጥረቷን አርግቦ ሰላምን ሊሰጣት አስቦ ይሆን ዶ/ር አብይ እርስዎን ወደ አመራር ያመጣዎት? ካለንበት አጣብቂኝ ለመውጣት ረዥም መንገድ መሄድ እንዳለብን እሙን ነው። ዶ/ር … [Read more...] about ዘብ ቆመናል ክቡር የኢትዮጵያ ልጅ ዶ/ር አብይ አህመድ
ከአንድ አማራ ንቅናቄ የዶ/ር አብይ አህመድ መመረጥን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የአንድ አማራ ንቅናቄ ዶክተር አብይ አህመድ የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነውሃገራች ን መስቀለኛ መንገድ ላይ በደረሰችበት በዚህ ወቅት ላይ በመመረጥዎ ሃላፊነትዎን ከመቼውም ግዜ በላይ ወሳኝና ታሪካዊ ያደርገዋል ብለን እናምናለን። የአማራው ሕዝባችን የእርሶን መመረጥ አስመልክቶ የብሄር ፤ የቋንቋና ፤ የማንነትድንበር ሳያግደው ለእርሶ ያሳየው ድጋፍና እምነት በግልጽ የሚታይ ሃቅ ነው:: አማራው ትላንትም ዛሬም ሆነ ወደፊት በሃሳብ ጥራት በስልጡንና ጨዋ የፖለቲካ ባህል ለሚያምን : ሃገራዊና ህዝባዊ አመለካከት ያላቸውን መሪዎች የሚከተልና የሚያከብር በመሆኑ እርስዎ ከዚህ ቀደም በአደባባይ ካቀረቡት ወገናዊና ስነምግባራዊ አቀራረብ መነሻ በማድረግ ድጋፉን ያለማንገራገር እየገለጸ ይገኛል። ሃገራችን ኢትዮጵያ ከተጋረጠባት አደጋና ከገባችበት ከፍተኛ የፖለቲካ አጣብቂኝለመላቀቅ ስር ነቀል … [Read more...] about ከአንድ አማራ ንቅናቄ የዶ/ር አብይ አህመድ መመረጥን አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
የትግላችን መነሻና መዳረሻ ምንድነው?
ብቅ ብቅ ባለ ሣር የተሳበ በሬ፡አፏን ከከፈተች መሬት ይተርፍ ይሆን! ለምን ሕዝባዊ ትግል አስፈለገ?መስዋዕትነቱስ የሚከፈለው ምንስ ለመቀዳጀት ይሆን? ህይወት፤ ዕውቀት፤ጊዜና ገንዘብለሰው ልጅ እጅግ አስፈላጊ ነገሮች ናቸው። የሰው ልጅ እነዚህን መሠረታዊ ሀብቶቹን አሳልፎ መስጠት ካለበት በአንጻሩ ብልጫ ያለው ካልሆነም ተመጣጣኝ የሆነ ምላሽ መሻት ይገባዋል። ብሶት ብዙ ጊዜ የሚፈጥረው ትግል፤ በአግባቡ ካልተደራጀና ከታች ወደ ላይ ከላይ ወደ ታች በሚንቀሳቀስ አካሄድ ካልተመራ፣ትግሉ ያልተቀነባበረና ግብታዊነት የሰፈነበት ይሆናል።በንቃት የተደራጀ ከሆነ ቀጣዩን ትግል መልክ ለማስያዝ ጠንካራ ድርሻ ይኖረዋል። በዚህ መልክ ትግሉ ከተመራ የሚከፈለው መሰዋዕትነት በዉጤት የጎመራ ይሆናል። እዚህ ላይ ልናስተውለው የሚገባ ዐብይ ጉዳይ በተበታተነ መልክ ለሚደረግ ትግል የሚከፈለውመሰዋዕትነት … [Read more...] about የትግላችን መነሻና መዳረሻ ምንድነው?
የዶ/ር አብይ አህመድ ፈተናዎች
እርግጥ እንደ መለስ ዜናዊ ባለ ሙሉ ስልጣን ጠቅላይ ሚኒስትር ይሆናል? ከልክ በላይ ለጥጠው፤ እንደ ልብ አንጠልጥል ፊልም ያቆዩትን ፍትግያ ትናንት በዜና ሲሰብሩት ደስታቸውን ይገልጹ የነበሩት ዜጎች ጥቂት አልነበሩም። ወትሮውን በስብሻለው ከሚለን ስራዓት አዲስ ነገር የሚጠብቅ ተስፈኛ ቢደሰት ብዙም አይደንቅም። የጠቅላይ ሚንስትር እንጂ የስራዓት ለውጥ መች ተመለከትን? ዶ/ር አብይ አህመድ በዚህ ቀውጢ ሰዓት ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ መመረጡ ግን ከክብሩና ከስልጣኑ ይልቅ ፈተናው ያመዝናል። ለሶስት ቀናት ተብሎ የተጀመረው ግብግብ ይሉት ክርክር በተነገረለት ቀን መቋጨት ያለመቻሉ በራሱ የሚነግረን ነገር ነበር። አወዛጋቢው የአስቸኳይ ግዜ አዋጅ፣ ፓርላማ ላይ በጸደቀበት ወቅት ዶ/ር አብይ በስፍራው ባለመገኘታቸው የህወሃት ሰዎች ክፉኛ እንደተበሳጩ አይተናል። ይህንን ቅሬታ በብሎገሮቻቸውም … [Read more...] about የዶ/ር አብይ አህመድ ፈተናዎች
የHR 128 እና የማግኒትስኪ ሕግ ትሥሥር፤ የህወሓት ፍርሃቻ!
ተጨማሪ መረጃ፤ ያለፈው ሳምንት መገባደጃ አካባቢ የኮሎራዶ 6ኛው ወረዳ እንደራሴ ማይክ ኮፍማን በድረገጻቸው እንዳስታወቁት HR 128 በኤፕሪል ወር ለሕዝብ እንደራሴዎች ምክርቤት ድምጽ ይቀርባል ብለዋል። ጉዳዩን ከሚከታተሉ በርካታ ወገኖች መካከል የቅርብ መረጃ ያላቸው አቶ ኦባንግ ሜቶ የቀጠሮው ቀን ኤፕሪል 9 (ሚያዚያ 1) መሆኑን በፌስቡክ ገጻቸው በለቀቁት መረጃ አስታውቀዋል። ይህ ረቂቅ ጸድቆ በሕግ እንዲወጣ ከፍተኛ ሥራ እየሠራ የሚገኘውን የኢትዮጵያና የአሜሪካ ግብረኃይል ፌስቡክ ገጽ በመሄድ ለረቂቅ ሕጉ እንዴት ድጋፍ መስጠት እንደሚቻል የበለጠ መረጃ ማግኘት ይቻላል። ከዚህ ጋር በተያያዘ ባለፈው “ህወሓት፡ የHR 128 ፍርሃቻ እና የማግኒትስኪ ሕግ” የሚለውን ዘገባ በድጋሚ አቅርበናል። ይህ ዘገባ ህወሓት ለምን ረቂቅ ሕጉን እንደፈራውና እጅግ በርካታ ገንዘብ በማፍሰስ ለማጨናገፍ … [Read more...] about የHR 128 እና የማግኒትስኪ ሕግ ትሥሥር፤ የህወሓት ፍርሃቻ!










