• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

ስማኝ ሰማእቱ!

April 4, 2018 05:56 am by Editor Leave a Comment

ከባርነት ሞትን የመረጥከው ወንዱ፣
አፉን ክፍት አርጎ የዋጠህ መቃብሩ፣
የማዋይህ አለኝ ስማኝ ሰማእቱ፡፡

የፈሰሰው ደምህ በህልሜ እየታየኝ፣
አጥንትህ ከመቃብር እየጎራበጠኝ፣
እሾህ ቀጋ ሆኖ አላስተኛህ አለኝ፡፡

ለፍትህ ስትጮህ የቀረኸው ባጭር፣
ጎንደር ደብረታቦር ወልድያ ባህርዳር፣
ቡሬና ዳንግላ ማጀቴና አቸፈር፣
ዛሬም ወንድሞችህ ታስረዋል ግዮን ዳር፡፡

በስናይፐር የፈጁህ ህሊና ቢሶቹ፣
ለውጥ አመጣን ብለው ያንኑ ደገሙ፣
አንድ አስገዳይ ነቅለው ሌላውን ተከሉ፡፡

አጥንትህን ከአምቦ ከእሬቻ ለቃቅሞ፣
መሰላል አረገው ከለማ ጋር ሰርቶ፡፡

በስንት በጎች ደም እንደተነከረ፣
እጁን ሳይታጠብ አቢይ ቀደሰ፡፡

ኢያሱና ሙሴን ተከተሉ እያሉ፣
ስንቱን ዘልዛላ እንከፍ ከጀርባ አሰለፉ፡፡

ተመራጩ አስገዳይ መራጩም ገዳይ ነው፣
የሌላው ማሽቃበጥ ምን እሚሉት ጉድ ነው?

ትናንትናም ያአድጊ ዛሬም ይህአድጊ ነው፣
አሸርጋጅ የበዛው የምን ለውጥ አይቶ ነው?

አጋዚ ሰው ፈጅ እያለ እሚጮኸው፣
ጆሮ ጠቢ አቢይን ቅዱስ አርጎ አረፈው፡፡

እንኳን ፈሪሳውያን እነ ሆድ አምላኩ፣
እነ ኦባንግ ሜቶም ለይሁዳ ሰገዱ፡፡

ስንቱ ወለወልዳ ስትሞት ያለቀሰው፣
አዛኝ አንጓች መስሎ የአዞ እምባ ያነባው፣
አስገዳይህ ሲነግስ ደስ ይበልህ አለው፡፡

ስንቱን ላስፈጀ ጉድ ድጋፍ እየሰጡ፣
የፍትህ ታጋይ ነን ብለውን አረፉ፡፡

እንዳንተ በጽናት መታገል ሲለግሙ፣
በአጥንቶችህ ባላ አቢይን ሰቀሉ፡፡

ታሪክ በደም ጥፈህ በክብር ያለፍከው፣
ስማኝ ሰማእቱ የኔ መልእክት ይህ ነው፡፡

አንተ ሙተህ አዝነን ሳይወጣ ሳልስትህ፣
የምዕራብ ዲፕሎማት እንዲሁም ገዳይህ፣
ፖለቲካ ቁማር ዘረጉ እመቃብርህ፡፡

የሞትክለት ህልምህ እንዳይደርስ ከዳሩ፣
የነደደው እሳት እንዲጠፋ ፍሙ፣
ትልቅ ማዳፈኛ ከምድጃ ጎለቱ፡፡

አስገዳይ ለማንገስ ፓርላማ ከተሙ፣
የሕዝብ ተወካዮች ብለው አፍጣጮቹ፣
እንደ ኦሪት ሁሉ ህማማትን ጣሱ፣
መነኩሳትን አስረው እነሱ እያሽካኩ፣
ድግስ እየዋጡ ዳንኪራ እየመቱ፣
ጉልቻን አንስተው ጉልቻ ጎለቱ፡፡

እየታገልን ነው ሲሉ የነበሩ፣
በራሳቸው እምነት ብቃትን ስላጡ፣
ወደ ላይ አንጋጠው አቢይ አቢይ አሉ፣
እንኳን የሞቱትን ፈጣሪን ረሱ፡፡

የራሱን ልብ አሞት የተጠራጠረ፣
በካድሬው አቢይ ቃል አመነና ማለ፡፡

ዳሩ ይህም ቢሆን እንዳይልህ ክፍት፣
አርማህን አንስቷል ፍም ጎራሹ ወጣት፡፡

ብቁ ሰማእታት እንደ አንተ የፀኑ፣
ነፃነት ወይም ሞት ብለው የቆረጡ፣
ሞረሽ ይጣራሉ በዱር በገደሉ፡፡

ያሳደደህ ቢነግስ በህማማቱ እለት፣
አዳኝህ ይነሳል ቅዳምሽ እሁድ ማግስት፡፡

ሐዋርያት ዝቅዝቅ ታስረው ቢታረዱ፣
ክርስትና ሰፍቷል ቁመትና ወርዱ፡፡

ክርስቶስ ተሰቅሎ ተቀብሮ እንዳልቀረው፣
ያንተም ህልም እሚያርግ ዘላለም ህያው ነው፡፡

ገዳይ አስገዳዮች አንተን የሰውቱ፣
አስገዳይ ለማንገስ አንተን የረሱቱ፣
እንደ ፈሪሳውያን ይሁዳ ዘ አስቆርቱ፣
ታሪክ ሲመትራቸው ሲያርዳቸው ይኑሩ፡፡

ምድር ታሪክህን እንዳሳማረችው፣
ሰማዩም ነፍስህን በምቾት ያኑረው፣
እኛም አደራህን አኝከን አንብላው፣
ስማኝ ሰማእቱ መልእክቴ ይኸው ነው፡፡

በላይነህ አባተ (abatebelai@yahoo.com)
መጋቢት ሁለት ሺ አሥር ዓ.ም.

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Left Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule