ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዮርዳኖስ ውሀ በዮሐንስ እጅ እንደተጠመቀ እንኳን ክርስቲያን ከክርስትና እምነት ውጭ የሆነ ሁሉ ያውቀዋል። ክርስቲያን ነኝ የሚል ሁሉ ይሰብከዋል። በተለይ እኛ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን ካህናት የጥንት ኢትዮጵያውያን ሊቃውንት አበው በሰሩልን ስርአት ከዓለም ልዩ በሆነ መንገድ እናንጸባርቀዋለን። በውስጡ ያዘለው ለወዳጅ ለጠላት የተሸከመው የመልእክቱ ይዘት እና ጥልቀት ምን ያህል እንደገባን እራሳችንን እንጠይቅ። ምክንያቱም ይህች ጦማር የተሸከመችውን ያባቶቻችንን ስሜት ለመናገር ለመመስከርና ትውልዱን ለማስተምር የሚጠይቅና የሚፈትን ከዚህ ዘመን የከፋ የለም። ስለ ጥምቀት በዓል ሁሉም የሚሰብከውን ሁሉም የሚያውቀውን በዚህች ጦማር ገልብጨና መልሸ በመናገር አንባቢን ማድከም አልፈልግም። ሲነገር ብሰማ ኖሮ ሰአቴን ባላጠፋሁ እኔም ባልደከምኩ ነበር። ይህ … [Read more...] about የጥምቀት በዓል
“በሴቶች ላይ የሚደረግ አካላዊ ጥቃትና ትንኮሳ ይቅር!”
ነገ ከተራ፣ ከነገ በስቲያ ጥምቀት ስለሚከበር ቢሮ ውስጥ ያለን ኢትዮጵያውያን ጥምቀትን አይተው ለማያውቁ ፈረንጅ ባልደረቦቻችን ስለ በአሉ ዘርዘር አድርገን እያወራን ነበር፡፡ ወሬው ሲሟሟቅ አንዱ ልጅ "the best part is throwing lemon (lime) on the girls!" አለ፡፡ ‹‹ከሁሉ ከሁሉ ደስ የሚለኝ ግን ልጃገረዶች ላይ ሎሚ መወርወር ነው›› እንደማለት ፡፡ ፈረንጆቹ ግራ ተጋቡ፡፡ ‹‹በበአል ምድር ምን ይሁን ብላችሁ ነው ሴቶች ላይ ሎሚ የምትወረውሩት?›› ብሎ ጠየቀ አንዱ፡፡ ‹‹ለፍቅር ለመጠየቅ ነዋ!...ሎሚ የተወረወረባት ሴት ደስ ይላታል፡፡ እንደውም ልጃገረዶች ወደ ጥምቀት ሲሄዱ አዲስ ልብስ ወይ ያላቸውን አጥበውና ተኩሰው ለብሰው፣ ተኳኩለው ነው የሚሄዱት፡፡ ያውም፤ ‹‹ እንደው ቀንቶኝ ሎሚ የሚወረውርብኝ አገኝ ይሆን!›› ብለው አልኩት፡፡ ይባስ ግራ … [Read more...] about “በሴቶች ላይ የሚደረግ አካላዊ ጥቃትና ትንኮሳ ይቅር!”
ኢትዮጵያን ለማየት ፣ ጥምቀት በጎንደር ማክበር…!
የከተራው በአል ከተራ ምንድን ነው? ከሚለው ትርጓሜ እንነሳ ... በየዓመቱ የጥምቀት በዓል በድመቀት ይከበራል፡፡ ከበዓሉ በፊት የከተራ በዓል የሚከበርበትን ታሪካዊና ሃይማኖታዊ ገለጻ ከተራ ከበበ ካለው የግእዝ ግሥ የወጣ ነው፡፡ ፍችው ውኃ መከተር፣ መገደብ ማለት ነው፡፡ የጥምቀት ዋዜማ ታቦተ ሕጉ ከቤተ መቅደስ ወጥቶ ውኃ ባለበት አካባቢ ስለሚያድር የየአጥቢያው ሕዝብ እየተሰበሰበ በወንዝ ዳር ወይም በምንጭ አካባቢ ድንኳን ይተከላል፡፡ ድንኳንም ከሌለ ዳስ ሲጥል ይውላል፡፡ የምንጮች ውኃ ደካማ በመሆኑ እንዲጠራቀም ይከተራል ፣ ጉድጓድ እየተቆፈረ ውኃው እንዳይሄድ ይገደባል፡፡ ከተራ በዓል በየዓመቱ በበዓለ ጥምቀት ዋዜማ ጥር 10 ቀን ይውላል ። የኦርቶዶክስ ክርስትና እምነት ተከታይ ምእመናን ሲወርድ ሲዋረድ ይዘው በመጡት ሃይማኔታዊና ባህላዊ እሴት መሰረት በጥምቀትን በዓል ዋዜማ … [Read more...] about ኢትዮጵያን ለማየት ፣ ጥምቀት በጎንደር ማክበር…!
ይመቻችሁ ጌቶቼ
ኩርዳዊ ነኝ ከኢራን - ኢማን አባስ እባላለሁ በቋንቋዬ እንዳልቀኝ - እንዳልከትብም ሁኛለሁ፤ የኔ ጌቶች ያሻቸውን - እሆን ዘንዳ ቢያስጨንቁኝ ግዳይ ጣልኩኝ እራሴን - ጭካኔያቸው ቢብሰኝ፤ ያውላችሁ ያሻችሁት - እንዳልሆን እሆን ፍርዳቸሁ አንደበቴን ተቆልፌ - ዐይኖቼን ተለጉሜ ይመቻችሁ እላለሁ - ጆሮቼን አስከርችሜ፤ ብእሬን ወርውሬ - ቀለሙን ደፍቼ ፍረዱኝ እላለሁ - እናንት ወገኖቼ፤ (ለምሥራቅ ኩርድ ባለቅኔው ለኢማን አባስ አመጽ መታሰቢያ) … [Read more...] about ይመቻችሁ ጌቶቼ
Terror plot to turn Ethiopian Epiphany celebration into an inferno uncovered
According to our well-placed sources in the inner circle of the ruling minority junta’s powerful and complex security apparatus, the regime has already assigned several well-trained and craven secret service agents dressed as Muslims to carry out massive bombing campaign during the Ethiopian Orthodox Tewahido Church’s Epiphany commemoration feast (Timket) on the 19th and 20 January 2014. The distinctly unpopular and even more feared government of Ethiopia, the godfather of terror and wanton … [Read more...] about Terror plot to turn Ethiopian Epiphany celebration into an inferno uncovered
“ወሬ አይደለም፤ አገር ቤት አንገባለን” ሌንጮ ለታ
የኦሮሞ ነጻ አውጪ ግንባር ከፍተኛ አመራርና ጸሐፊ የነበሩት አቶ ሌንጮ ለታ አዲስ ያቋቋሙትን ድርጅት ይዘው አዲስ አበባ እንደሚገቡ አስረግጠው ተናገሩ። አቶ ሌንጮ ድርጅታቸው ኢትዮጵያ ገብቶ ለመታገል መወሰኑ ለምን ወሬ እንደሚባል እንዳልገባቸውም አመላክተዋል። በሰላማዊ መንገድ ለመታገል ኢትዮጵያ መግባታቸውን ኦነግ እንደሚቀበለው ተጠይቀው "ኦነግን ጠይቅ" በሚል ጠበቅ ያለ መልስ ሰንዝረዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መረጃ እንደሌለው አመልክቷል። ጥር 5 ቀን ከጀርመን ድምጽ የአማርኛ ፕሮግራም ጋር ቃለ ምልልስ ያደረጉት አቶ ሌንጮ "ኖርዌይ ተቀምጠን ምን እናደርጋለን? ሃገር ቤት ገብተን እንታገላለን" ሲሉ ወደ አገር ቤት ለመመለስ መወሰናቸውን ግልጽ አድርገዋል። "ይሳካል?" በማለት ጠያቂው ላቀረበው “ይሳካል አይሳካም ተብሎ ወደ ትግል አይገባም” በማለት አቶ ሌንጮ ማምረራቸውን በሚያሳብቅ … [Read more...] about “ወሬ አይደለም፤ አገር ቤት አንገባለን” ሌንጮ ለታ
ፕ/ር በየነ “የአካኪ ዘራፍ ትግል አክሳሪ ነው፤ የስሜት ፖለቲካ ያብቃ” አሉ
“የአካኪ ዘራፍ ፖለቲካና ከስሜት ያልጸዳ የፖለቲካ ትግል መሪውንም ሆነ አምኖ የሚመራውን ህዝብ ለድል” እንደማያበቃ ፕሮፌሰር በየነ ጴጥሮስ ገለጹ። ከኤርትራ ጋር ስምምነት ቢደረግ መልካም መሆኑን፣ ነገር ግን ስምምነቱ የመሪዎችና የፖለቲከኞች ሳይሆን የህዝብን ስሜት የጠበቀ ሊሆን እንደሚገባውም ጠቁመዋል። ከጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ ጋር በተለይ ቃለ ምልልስ ያደረጉት ፕ/ር በየነ "አሁን ያለው የኢትዮጵያ ፖለቲካ ሁኔታ ከመቼውም ጊዜ በላይ አስተዋይነት የሚፈልግ፣ ዘመናዊ የትግል ስልት የሚጠይቅ ነው" በማለት ተናግረዋል። በቃለ ምልልሳቸው ደጋግመው "አሁን በተያዘው የአካኪ ዘራፍ መንገድ የትም አይደረስም" በማለት ምክንያታቸውን ዘርዝረዋል። ትንንሽ ጠርዝ በመያዝ የትም የማይደርስ ትግል ከየአቅጣጫው እንደሚፈለፈል ፕ/ር በየነ አመልክተዋል። በዚሁ የተነሳ ስትራቴጂካልና ታክቲካል ጉዳይ … [Read more...] about ፕ/ር በየነ “የአካኪ ዘራፍ ትግል አክሳሪ ነው፤ የስሜት ፖለቲካ ያብቃ” አሉ
አዲስ ዓመት?
ከሁለት ሳምንታት በፊት የፈረንጆች አዲስ ዓመት እንደገባ እናስታውሳለን፡፡ ይሄን ተከትሎ የአንዳንድ ድርጅቶች ሲገርመን ባልተለመደ መልኩ ጭራሽ ከሀገርና ከሕዝብ እሴትና ጥቅም አንጻር ከፍተኛ ኃላፊነት ያለበትና ከፍተኛ ጥንቃቄ ማድረግ የሚጠበቅበት የብዙኃን መገናኛውም (ሚዲያው) ይህንን የባዕዳኑን አዲስ ዓመት እድምተኞቻቸውም ማለትም አድማጭ ተመልካቾቻቸውም በዓሉን በማክበሩ እንዲቀላቀሏቸው በሚጋብዝ መልኩ በድምቀት አከበሩ፡፡ ይህ ስሕተት ጎልቶ ከታየበት የብዙኃን መገናኛዎች አንዱ ኢ.ቢ.ኤስ. በሚል አሕጽሮተ ቃል የሚጠራው የኬብል ቴሌቪዥን ነበር፡፡ በዚህ ቴሌቪዥን (ምርዓዬ-ኩነት) ከሚተላለፉ ዝግጅቶችና ይህን ስሕተት ከፈጸሙት ምስናዶች (ፕሮግራሞች) አንዱ “መቅዲ ሾው” (መቅዲ ትዕይንተ-ወግ) የተሰኘው ምስናድ ነበር፡፡ ጉዳዩ ትንሽ የሚያበሳጭ ስለነበር ለአዘጋጇ በፌስ ቡክ … [Read more...] about አዲስ ዓመት?
ቅዱስ ጦርነት
ሰሞኑን ከያኔ (አርቲስት) ቴዎድሮስ ካሳሁን ለዕንቁ መጽሔት የሰጠውን ቃለ ምልልስ ተንተርሶ በተለይ በማኅበራዊው የብዙኃን መገናኛ ልክና ገደብ ያለፈ መራኮት ተፈጥሮ ነበር ፡፡ አጋጣሚው የሀገር ጠላቶች ኢትዮጵያን እንዳልነበረች ለማድረግ ያላቸውን ዝግጅትና አቅም ያሳየ ሆኗል ፡፡ ክርስቶስ አደቡን ማስተዋሉን ይስጥልን ከማለት ውጪ ዓላማ ብለው ለያዙት የጥፋት ልጆች ለጊዜው ምንም የምለው ነገር የለኝም ፡፡ በእነዚህ የጥፋት መልእክተኞች እየተወናበዱ ላሉ የዋሀን ዜጎች ግን በአጭሩ የምለው ነገር አለኝ ፡፡ እባካቹህን አስተውሉ ይሄንን የተሳሳተ አስተሳሰብ የፈጠረው መርዘኛው የወያኔ የዘር ፖለቲካ እንደሆነ ልብ በሉ ፡፡ በእርግጥ እውነት ነው ዐፄ ምኒልክ 2ኛ ከዐፄ ቴዎድሮስ የተረከቡትን አደራ ኢትዮጵያን እንደገና የመሰብሰብና አንድ የማድረግ ተልእኮ ለመፈጸም ሲሉ እዚህም እዛም የገደሏቸው … [Read more...] about ቅዱስ ጦርነት
አፈንዲ፣ ጃዋር መሐመድ እና የቴዲ አፍሮ ጉዳይ
የሰሞኑ የነ ጃዋር ሲራጅ ግርግር ለኛም ስም አትርፏል፡፡ እንደፈቀደው ይሁን፡፡ እኛ ጉዳያችን ሞልቶልናል፡፡ የታቀደው የቴዲ ኮንሰርት በመሰረዙ በጣም ደስተኞች ነን፡፡ በኮንሰርቱ ታክኮ ሊከሰት የሚችለው የህዝብ መተላለቅ በመቅረቱ እሰየው ነው፡፡ ብርና ዝና ብቻ እያሰቡ የህዝብ መጨራረስን ሊጋብዙ የነበሩ ሰዎች ተንኮላቸው ስለከሸፈባቸው አላህን በጣም ነው የምናመሰግነው፡፡ ታዲያ ያስገረመኝ ነገር ስሜት እውነትን ለመሸፈን ምን ያህል ጉልበት እንዳለው መረዳቴ ነው፡፡ አጃኢብ ነው! ግጭትና ትርምስ ሲሰበክ የነበረው በውሸት የተፈጠረውን ወሬ እንደ ሰበብ በማድረግ ነው፡፡ ውሸቱን ለማዳመቅ በግርግሩ ውስጥ የገቡ ሀይሎች አበዛዝም ያስገርማል፡፡ ከአሜሪካ እስከ ኖርዌይ፣ ከለንደን እስከ ሸገር እየተጠራሩ ሽብሩን ለማጋጋል የተደረገው ጥረት አስደናቂ ነበር፡፡ ለወትሮው በአንድ ብሄር ላይ የሚደረግ … [Read more...] about አፈንዲ፣ ጃዋር መሐመድ እና የቴዲ አፍሮ ጉዳይ










