በአሜሪካ የአዲስ አበባ ባለአደራ ምክትል ሊቀ መንበር ተደርጎ የተሾመው የቀድሞው የህወሃት ካድሬና የበረከት ስምዖን ታማኝ ኤርሚያስ ለገሰ መሰናበቱ ተሰማ። እስክንድር ነጋን የጠቀሱ የጎልጉል እማኞች እንዳሉት ኤርሚያስ መባረሩን አያውቅም። በዚህ ሳቢያ 360 እንደ ስሙ ዘመቻውን ያዞራል ተብሎ ይጠበቃል። የእስክንድር ነጋን የአሜሪካ ጉዞ ተከትሎ በሰርግና ምላሽ የባለ አደራው ምክትል ሰብሳቢ የሆነው ኤርሚያስ ሹመቱን አስመልክቶ ስለ ቀጣዩ የትግል አቅጣጫ፣ የትግሉ ግብና አደረጃጀት እንዲሁም ኔትዎርክ ማብራሪያ ሰጥቶ እንደነበር ይታወሳል። ተያዘውም ወደ ተፈለገው ዓላማ እንደሚደርሱ ምሎ ነበር። ለድርጅቱ ሊቀመንበር እስክንድር ነጋ ቅርብ የሆኑና ይህ ውይይት ሲደረግ የነበሩ ኤርሚያስ ለገሰ በቅርቡ ከሃላፊነት መነሳቱ ይነገረዋል "የእሱ መሰናበት ያለቀ ነው። መጀመሪያም ትክክል አልነበረም" … [Read more...] about ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ
ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥
ኢትዮጵያ ስንት ልጆች ወለደቸ፤ ስንቱን አስተማራቸ፤ ስንቱን አቋቁማ ለአቅመ ዓዳም አበቃች፤ ስንት ጉድስ ተሸከመች። ቆጥረን ስለማንዘልቀው ቤቱ ይቁጠረው ብለን ብናልፈው ይበቃል። ብዙ ጉድ እንደተሸከመች ብናውቅም ብዙ ልጆቿ ሸክሟን ለማቅለል፤ ችግሯን ለመቅረፍ፤ እድገቷን ለማፋጠን ብዙ ጥረውላታል። በእውቀታቸው፤ በጉልበታቸውና በሃብታቸው ባቻ ሳይሆን ሕይወታቸውን ጭምር ገብረውላታል፤ እየገበሩም ይገኛል። በአንፃሩ በሃብቷ ተምረው ስሟን ያጎደፉ፤ ሕልውናዋን የተፈታተኑ ከሃዲዎች መኖራቸውን ስናይ እናዝናለን። እነዚህን የመሰሉ ልጆቿ ሃገሪቱን አመድ አፋሽ አርገዋታል። ይህ የቅርብ ጊዜ ክስተት ብቻ ሳይሆን በሶስት ሽህ ዘመን ጉዞዋ ሁሉ ሲከሰት የኖር ለመሆኑ ታሪክ ይነግረናል። ያአሁኑን ከጥንቱ ለየት የሚአደርገው ያለንበት ሃያ አንደኛው ክፍለ ዘመን መሆኑ፤ ልጆቿ ዘመናዊ ትምህርት … [Read more...] about ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥
ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል?
የዛሬ ሃምሳ ዓመት ገደማ መሰለኝ የያኔው ወጣት የዩኒቬርሲቲ ተማሪው ኢብሳ ጉተማ “ኢትዮጵያዊው ማን ነው?” በሚል ርዕስ አንድ ጽሁፍ አቅርቦ ለውጥ ፈላጊውን የዩኒቬርሲቲውን ማህበረሰብ ጥም ለማርካት የሞከረው። አብዛኛው የዩኒቨርሲቲው ተማሪ የፊውዳል ሥርዓቱ አገሪቷን ወደፊት እንዳትራመድ ጠፍንጎ የያዛት መሆኑን የተረዱና ሥርዓቱ ካልተለወጠ የሕዝቦቿ አብሮነት ውሎ አድሮ መሸረሸሩ አይቀሬ መሆኑን ተገንዝበው ኢትዮጵያንና ኢትዮጵያዊነትን ለማናበብ መላ ይመቱ ነበርና የዚህ ንቁ ተማሪ ግጥም ጊዜውን ጠብቆ የመጣ ነበር። በዚሁ ጊዜ ነበር ከተማሪው እንቅስቃሴ መሪዎች አንዱ የነበረው ዋለልኝ መኮንን የብሄር ጥያቄን አስመልክቶ ታሪካዊውን ጽሁፍ ያቀረበው። አንዳንዶች ያኔም ሆነ ዛሬ እነዚህን ጽሁፎችን አስመልክቶ ሁለቱን ንቁ የተማሪው ማህበረሰብ አባላትን አገሪቷን ለመበታተን ሆን ብለው … [Read more...] about ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል?
WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE”
By David Steinman Money, Blood and Conscience is a novel about Ethiopia’s democracy revolution. It tells the story of the brave Ethiopians who stood up for freedom. A lot of people have asked me why I wrote this book, and this article explains why. I became an adviser to Ethiopia's democracy movement soon after the TPLF took power because Meles was reneging on his promises of democratization. I saw that the TPLF was not going to lead Ethiopia in the right direction, and a lot of … [Read more...] about WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE”
አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል!
ስለ ዓድዋ ጦርነት አንዳንድ እውነታዎች❗️ ቀን: የካቲት 23, 1888 ቦታ: አድዋ፤ ኢትዮጵያ አሸናፊው ሀይል: ኢትዮጵያ በኢትዮጵያ በኩል የነበሩ የጦር አዛዦች አጤ ምኒልክ እቴጌ ጣይቱ ተክለ ሀይማኖት ራስ መኮንን ራስ ሚካኤል ራስ መንገሻ ፊታውራሪ ገበየሁ ፊታውራሪ ሀብተጊዮርጊስ ፊታውራሪ ዳምጠው ደጃዝማች ባልቻ ሳፎ ኒኮላ ሊዮንቴቭ በጣልያን በኩል የነበሩ የጦር አዛዦች ኦሬስቴ ባራቴሪ ቪቶሪዮ ዳቦርሚዳ ጁሴፔ አሪሞንዲ ማቲዎ አልቤርቶኒ ጁሴፔ ኤሊና በኢትዮጵያ በኩል የተሰለፈ የጦር ብዛት 80,0000 መሳርያ የታጠቅ 20,000 ጦርና ጎራዴ የታጠቀ 8,600 ፈረሰኛ በጣልያን በኩል የተሰለፈ የጦር ብዛት 24,804 ዘመናዊ መሳርያ የታጠቅ ወታደር 56 ረጅም ርቀት ተወርዋሪ መሳርያዎች በኢትዮጵያ በኩል የተሰዉ ጦረኞች ቁጥር … [Read more...] about አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል!
ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው)
በፈረስ ስማቸው ጎራው በመባል ይታወቃሉ፣ ከአድዋ በፊት ከኢጣሊያ ጋር በተደረጉ የአምባላጌ እና የመቀሌ ጦርነት ላይ በጀግንነት የተዋጉ የጦር መሪም ናቸው ፊታውራሪ ገበየሁ! በአምባላጌ ጦርነት ወቅት ጎራው ገበየሁ የጠላትን የጦር ሰፈር እንዲቃኙ በተላኩበት ጦርነቱን አስጀምረው በዚያ መሽጎ የነበረውን የኢጣሊያ ጦር ድል አደርገዋል ለዚህም፥ "ያ ጎራው ገበየሁ አላጌ በሩ ላይ ማልዶ ቢገጥማቸው፤ ለምሳም ሳይደርሱ ለቁርስ አደረጋቸው።" ተብሎ ተገጥሞላቸዋል። ምንም እንኳን የአምባላጌው ድሉ የኢትዮጵያ ቢሆንም ፊታውራሪ ገበየሁ ግን ገና ያልታዘዘ ጦርነት ነው ያስጀመሩት ተብለው እንዲታሰሩ ተወሰነባቸው። እርሳቸውም "ጀግና የጦር መሪ የምኒልክ አብሮ አደግ ነኝ እንዴት ይሆናል" ሳይሉ ፍርዱን ተቀብለው በሰንሰለት ታሰሩ። በኋላ ላይም በመቀሌው ጦርነት ወቅት ተፈትተው … [Read more...] about ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው)
የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል
ኦነግ አወዛጋቢ ማንነቱና ያልረጋ የፖለቲካ ሩጫው ዛሬም መነጋገሪያ ሆኗል። ቀደም ሲል ለኦሮሞ ትግል እንደ አንድ ብቸኛና ልዩ ምልክት ተደርጎ የተወሰደው ኦነግ በአራት ጎራ ተከፍሎ ቢቆይም አገር ቤት ከገባ በኋላ አንድ መሆን አልቻለም። በኤርትራ በረሃ እያለ እርስበርስ ጎራ ለይቶ በጥይት የተጫረሰው ኦነግ፣ በአውሮፓና በአሜሪካ ባሉ የተለያዩ አመራሮቹ የስልጣን ሽኩቻ አንድ መሆን አቅቶት ሁለት ዐሥርተ ዓመታት አስቆጥሮ አሁን አገሪቱ ውስጥ በተፈጠረው የፖለቲካ ለውጥ ሁሉም አካላት ወደ አገር ቤት ቢገቡም ልዩነታቸውን ማስወገድ አልቻሉም። ዳውድ ኢብሣ (ፍሬው ማሾ)፣ አባ ነጋ፣ ገላሳ ዲልቦና ጄኔራል ከማል ገልቹ የተቀራመቱት ኦነግ አራት መልክ ይዞ ወደ አገር ቤት ሲገባ ሕዝብ ጥያቄ ያነሳው “ለምን አንድ አትሆኑም? አንድ ሁኑና ኑ” የሚል ነበር። እነዚህ አራት ክንፎች እንኳን … [Read more...] about የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል
በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች
በቡራዩ የተከሰተውን ረብሻ አስመልክቶ ቢቢሲና የመንግሥት ሚዲያዎች የተሟላ መረጃ አለማቅረባቸውን የቡራዩ ነዋሪዎች ለጎልጉል ገለጹ። እነሱ እንዳሉት በአንድ መጠነኛ ሆቴል ምረቃ ላይ ለተነሳው ጸብ መነሻው በሽብር ተግባሩ የሚታወቀውና ጃል ማሮ (ኩምሣ ድርባ) የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ፎቶ በጨረታ እንዲሸጥ መቀረቡን ተከትሎ ነው። ነዋሪዎቹ ለጎልጉል የአዲስ አበባ ዘጋቢ ሲያስረዱ በምረቃው ላይ ጃል ማሮን የሚያወድሱ ሙዚቃዎች በዝተው ነበር። የውዳሴው ሙዚቃ መብዛቱ ከቡራዩና አካባቢው ወይም በተለምዶ የ“ሸዋ” የሚባሉትን ኦሮሞዎች አላስደሰተም። ሙዚቃው ቅይጥ እንዲሆን ቢጠየቅም ሰሚ አልነበረም። “በዚህ ስሜት ውስጥ እያሉ ነው ጃል መሮ የሚባለው የኦነግ ሸኔ ሽፍታ መሪ ምስል ለጨረታ የቀረበው” ሲሉ በስፍራው የነበሩ ምስክሮች ያረጋግጣሉ። አክለውም “የዚህን ጊዜ ንትርክ ተነሳ። … [Read more...] about በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች
“ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው
በኦሮሚያ ክልል አዲስ የተነሳው የፍረጃ ፖለቲካ የኃይል አሰላለፉን እንደቀየረና በርካታ የክልሉን ተወላጆች እያሳሰበ መሆኑ ተገለጸ። አካሄዱ ወደ ዘር ማጽዳት ለሚደረገው ድብቅ ጉዞ አመላክች ተደርጎ ሊወሰድ እንደሚችል አስተያየት እየተሰጠ ነው። ሲጀመር “ዲቃላ” የሚለው ፍረጃ በድንገት የተሰነዘረው የጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይን ስም በማንሳት ነው ቢባልም አቶ በቀለ ገርባ ቀደም ብለው ለዚህ አካሄድ ፍንጭ መስጠታቸውን ስጋት የገባቸው ለጎልጉል እንደመነሻ ያነሱታል። “ከሌሎች ብሔረሰቦች ጋር አትጋቡ፣ አትነግዱ” ሲሉ ዲስኩር ያደረጉት አቶ በቀለ ገርባ ይህ ንግግራቸው በወቀቱ ከፍተኛ ተቃውሞ አስነስቶባቸው እንደነበር ያወሱት እነዚህ ክፍሎች፣ ይህንኑ መርዘኛ ቅስቀሳ ለማስተባበል ጃዋር መሐመድ የሚመራቸው ሚዲያዎች በዘመቻ መልክ መትጋታቸውን ያክላሉ። በወቅቱ በፕሮፓጋንዳ ብዛት ነገሩ … [Read more...] about “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው
“ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ
“በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ” አለበት ጠቅላይ አቃቤ ሕግ በኢትዮጵያ የሕግ የበላይነትን ለማስከበር የተወሰዱ እና ሊወሰዱ ይገባቸዋል ስላላቸው እርምጃዎች የካቲት 5፣ 2012 መግለጫ አውጥቷል። በየቦታው የሚፈጠሩ የወንጀል ድርጊቶች ዋነኛ ችግር የፖለቲካ አመራሮች እጅ እንዳለበት የገለጸው መግለጫ ለሀገሪቱ ደህንነትና ለህዝቡ ህልውና ሲባል ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን እንደማይታገስ አቋም መያዙን ይፋ አድርጓል። የመግለጫው ሙሉ ቃል እንደሚከተለው ቀርቧል፦ ከኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ የተሰጠ መግለጫ የሕግ የበላይነትን ማስከበር ለድርድር የሚቀርብ ጉዳይ አይደለም የኢፌዲሪ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ የፍትህ ስርዓቱን የማጠናከርና የህግ የበላይነትን የማክበርና የማስከበር ተግባሩን … [Read more...] about “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ










