አቶ ፈቃደ ሸዋቀና የስደትን ነገር መነሻ አድርገው ስለ ብሔራዊ እርቅ የሰነዘሩት ሀሳብ ካለፈው የባሰ ጨለማ የሆነው የሀገራችን መጻኢ እድል አሳስቦ አስጨንቆአቸው ያቀረቡት በጎ ሀሳብ እንደመሆኑ አንብበን የምንተወው ወይንም ተግባራዊ ሊሆን የማይችል ብለን ልናናንቀው የሚገባ አይደለም፡፡ ርሳቸውም አንዳሉት ሁሉም የየበኩሉን ይበጃል የሚለውን ሀሳብ በመሰንዘር በመተላለቅ ሳይሆን በመታረቅ የምናተርፈበትንና ሀገራችንንም አድነን ለመጪው ትውልድ ልጆቿ በሰላምና በፍቅር የሚኖሩባት ዴሞክራሲያዊት ሀገር ለማቆየት ወደሚያስችለን እቅጣጫ ብናመራ ነው የሚበጀው፡፡ በዚህ መንፈስ እኔም እንዲህ ቢሆን እላለሁ፡፡ ወያኔ ስልጣኑን ለብቻው ካደረገ ግዜ ጀምሮ በተለያየ መንገድ የብሔራዊ እርቅ ጥያቄ የተነሳ ሲሆን የሀሳቡ አቀንቃኞች በሁለት ወገን መወገዛቸውን እናስታወሳለን፡፡ ወያኔ የደርግ ሥርዓት ወንጀለኞችን … [Read more...] about በቅድሚያ ከራሳችን እንታርቅ
“መሞቴ … የተሻለ ነው” አንዳርጋቸው
* “ልማታዊ ግድያውን” ተጠናክሮ ቀጥሏል እየሠራሁ ነው ለሚለው ልማትና ግድብ “እንደጀመርን እንጨርሰዋለን” እያለ የሚፈክረው ኢህአዴግ በየእስር ቤቱ የሚያሰቃያቸው ወገኖች ቁጥር እንዳለ ሆኖ “ልማታዊ ግድያውን” አጠናክሮ ቀጥሏል፡፡ ሰሞኑን በግፍ የተገደለው ሳሙኤል አወቀን ጨምሮ ማክሰኞ ዕለት የዓረና-መድረክ አባል የሆኑት አቶ ታደሰ አብርሃ ታንቀው መገደላቸው ተሰማ፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ በሚያዚያ ወር በእንግሊዙ አምባሳደር የተጎበኙት አንዳርጋቸው ጽጌ ለመሞት ደስተኛ እንደሆኑና ምናልባትም የተሻለ መሆኑን ተናገሩ፡፡ የአቶ ታደሰ አብርሃን አገዳደል በፌስቡክ ገጹ ያሰራጨው አምዶም ገብረሥላሴ በዚህ መልኩ አቅርቦታል፡- አቶ ታደሰ አብርሃ የተባሉ የዓረና-መድረክ አባልና የምዕራባዊ ዞን የዓረና አመራር አባል ትናንት ማታ 09/10/2007 ዓ/ም በሶስት ሰዎች ታንቀው ተገደሉ። አቶ … [Read more...] about “መሞቴ … የተሻለ ነው” አንዳርጋቸው
እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፰
ከአዘጋጆቹ፤ ወዳጃችን ወለላዬ “እኚህ ሰው ማናቸው?” በሚል ዓምድ ሥር ለአገራቸው የለፉና የደከሙ ኢትዮጵያውያንን እንዲነሱ፣ እንዲወደሱ፣ እንዲከበሩ፣ ... በማድረግ ግሩም ሥራ ሲሰሩ ቆይተው ባለፈው ባቀረቡት ሃሳብ መሰረት እናንተ አንባቢያን ታሪካቸው መነሳት አለበት የምትሉትን ከፎቶ ጋር እንድታቀርቡ ጥሪ አድርገው ነበር፡፡ የአገራችን ታሪክ በሚያስደነገጥ ፍጥነት እየወደመ ባለበት በአሁኑ ወቅት በህይወት ያሉትንም ሆነ የሌሉትን አንስተን ማወደስ ተገቢ ተግባር ብቻ ሳይሆን ሁላችንም ልንሳተፍበት የሚገባ አገራዊ ጥሪ እንደሆነ እናምናለን፡፡ ትኩረታችን እና ኃይላችንን የሚወስደው ነገር አንድ ብቻ መሆን የለበትም ምክንያቱም እየደረሰብን ያለው ጥቃት ከበርካታ አአቅጣጫ ነውና፡፡ ስለዚህ አሁንም ይህንን ዓምድ በከፈትንበት መልኩ ሥራቸውና ታሪካቸው እንዲነሳ የምትፈልጉት ሰው ካለ ፎቶውንና … [Read more...] about እኚህ ሰው ማናቸው? – ፲፰
የሻእቢያ “የተሀድሶ” ስትራቴጂ አካሄዱና እንደምታው
በአቶ ኢሳያስ አፈወርቂ የሚመራው አስመራ ላይ የተሰየመው የሻእቢያ መንግሥት ለ 23 ዓመታት የተከተለውን አካሄድ እንዳላዋጣው በመገንዘብ ይመስላል በተወሰነ ደረጃ ለየት ያለ ገጽታን ለማሳየት እና ራሱን አለሳልሶና የሰላም አባወራ ሆኖ ለመቅረብ በመሯሯጥ ላይ ይገኛል። ይህ ምን መልክ ይዞ ነው የሚራመደው? ለሀገራችን ኢትዮጵያስ ምን እንደምታ አለው? የሚለው የዚህ ጽሑፍ ዋናአላማው ነው። (ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about የሻእቢያ “የተሀድሶ” ስትራቴጂ አካሄዱና እንደምታው
ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ በድብቅ ጅዳ ገቡ
የውጭ ጉዳይ ምክትል ሚ/ር አቶ ብርሃነ ገ/ክርስቶስ በድብቅ ጅዳ ማምሻውን ገብተዋል፡፡ ወደ ሳዑዲ አረቢያ የመጡበት ምክንያት ባይታወቅም በዚያው የሚገኙ የኢህአዴግ ሹሞችና ልማታዊ ዲፕሎማቶች ድንገተኛውን ጉብኝት ተከትሎ ከብርሃነ ጋር ለመወያየት ሽርጉድ ይሉ ለነበሩ የጅዳና አካባቢው ካድሬዎች፣ ለልማት ማህበራት ተወካዮችና ለደጋፊዎቻቸው በሚስጥር ጥሪ አስተላልፈዋል፡፡ ምስጢራዊውን ጥሪ የሚቃወሙ ኢትዮጵያውያን አንድ ባለስልጣን በዚህ መልክ ወደ ጃዳ መግባታቸው ዲፕሎማት ብለው ለሾሟቸው አገልጋዮቻቸው ያላቸውን ንቀት የሚያሳይ ብቻ ሳይሆን በዲፕሎማቱ ላይ እምነት እንደሌላቸው አመላካች መሆኑን ይናገራሉ። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ የኢህአዴግ ከፍተኛ ባለሥልጣናት ለስራ ጉብኝትም ይሁን ለህክምና ወደ ሳውዲ አረቢያ ሲገቡ የኤምባሲው ዲፕሎማቶች መረጃ የሚያገኙት ከተለያዩ ድህረ ገጾች መሆኑን … [Read more...] about ብርሃነ ገብረ ክርስቶስ በድብቅ ጅዳ ገቡ
በሐና ላላንጎ ጉዳይ የተከሰሱት 17-20 ዓመት እስራት ተፈረደባቸው
ታዳጊ ወጣት ሐና ላላንጎን ደፍረው ለሕይወቷ ማለፍ ምክንያት ሆነዋል የተባሉ አምስት ተከሣሾች ተፈረደባቸው፡፡ የፌደራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት በተበየነባቸው ወንጀለኞች ላይ ያሣለፈው ከ17 ዓመት እስከ 20 ዓመት የሚደርስ የእሥራት ቅጣት ነው፡፡ በዚህም መሠረት አንደኛና ሁለተኛ ተከሣሽ ሣምሶን ሺበሺና በዛብህ ገብረማርያም በሃያ ዓመት እሥራት፣ ሦስተኛ ተከሣሽ በቃሉ ገብረመድህን በ17 ዓመት እሥራት፣ አራተኛ ተከሣሽ ኤፍሬም አየለ በሃያ ዓመት እሥራት፣ አምስተኛ ተከሣሽ ተመስገን ፀጋዬ በ18 ዓመት እሥራት እንዲቀጡ ችሎቱ ፈርዷል፡፡ አንደኛና ሁለተኛ ተከሣሾች ፍርዱ ከተሰማ በኋላ ችሎቱን ዘልፈዋል፡፡ የሃና ላላንጎ አባትና የቅርብ ዘመዶቿ በቅጣቱ እንዳልረኩ ተናግረዋል፡፡ ለተጨማሪ የተያያዘውን ዘገባ እዚህ ላይ ያዳምጡ፡፡ (መለስካቸው አመሃ የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ) … [Read more...] about በሐና ላላንጎ ጉዳይ የተከሰሱት 17-20 ዓመት እስራት ተፈረደባቸው
የዳርፉሩ “ወንጀለኛ” ከደቡብ አፍሪካ አመለጡ
* አልበሽር አገራቸው ሲገቡ “ደማቅ” አቀባበል ተደርጎላቸዋል በዘር ማጥፋትና በሰብዓዊ ዘር ላይ ወንጀል በመፈጸም እንዲያዙ ማዘዣ የተቆረጠባቸውና ከደቡብ አፍሪካ እንዳይወጡ በፍርድቤት የተወሰነባቸው የሱዳኑ ተፈላጊ ወንጀለኛ ፕሬዚዳንት ኦማር አልበሽር አምልጠው አገራቸው ገብተዋል፡፡ እሁድ ማምሻውን ከነበሩበት ቦታ በመሰወር ወደ ደቡብ አፍሪካ የአየር ኃይል ቤዝ በመደብ የቆዩት አልበሽር ሰኞ ዕለት ከተሰወሩበት አየር ኃይል ተነስተው አገራቸው ገብተዋል፡፡ እዚያም ሲደርሱ “ደማቅ” አቀባበል እንደተደረገላቸው ተነግሯል፡፡ አልበሽርን ለመያዝ ከፍተኛ ጥረት ሲያደርጉ የነበሩት የአይሲሲ ባለሥልጣናት ደቡብ አፍሪካ በፈጸመችው “ክህደት” በሚባል ተግባር እንዳዘኑ ገልጸዋል፡፡ ምክትል ዓቃቤ ሕጉ ጀምስ ስቴዋርት ለቢቢሲ እንዳሉት አሁንም ተስፋ በማድረግ ሥራቸውን እንደሚቀጥሉና ፍትህ እንዲበየን … [Read more...] about የዳርፉሩ “ወንጀለኛ” ከደቡብ አፍሪካ አመለጡ
ኦማር አልበሽር ከደቡብ አፍሪካ እንዳይወጡ ታገዱ
ዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት የከሰሳቸውና እንዲያዙ ማዘዣ የቆረጠባቸው የሱዳኑ ፕሬዚዳንት ለአፍሪካ ኅብረት ስብሰባ ከሄዱበት ደቡብ አፍሪካ እንዳይወጡ እዚያ የሚገኝ ፍርድ ቤት ማዘዣ ሰጠ፡፡ በኢትዮጵያ በሰው ዘር ላይ ወንጀል ለፈጸሙ የህወሃት ሹሞች ይህ ታላቅ ማስጠንቀቂያ ሊሰጣቸው እንደሚገባ ኦባንግ ሜቶ አስታወቁ፡፡ በእንግሊዝኛው ምህጻረ ቃል አይሲሲ የሚባለው ዓለምአቀፉ የወንጀለኞች ፍርድቤት የሱዳኑን ፕሬዚዳንት ኦማር አልበሽር የዛሬ ስድስት ዓመት አካባቢ በዘር ማጥፋትና በጦር ወንጀለኝነት ክስ መስርቶ እጃቸውን እንዲሰጡ ወይም እንዲያዙ ማዘዣ ቆርጦባቸው ነበር፡፡ የተወነጀሉበት ክስም በደቡብ ሱዳን አማጽያንን ትረዳላችሁ በማለት ሦስት ጎሣዎች ላይ ጥቃት እንዲፈጸም፣ ሴቶች እንዲደፈሩ፣ ነዋሪው እንዲፈናቀል፣ እንዲገደል፣ ወዘተ የጃንጀዊድ ሚሊሻዎችን በማስታጠቅ በሥፍራዎቹ … [Read more...] about ኦማር አልበሽር ከደቡብ አፍሪካ እንዳይወጡ ታገዱ
Ethiopia’s hope for changing an unwanted government by ballot box dashed
The Ethiopian current ruling party (actually it has been ruling the country for the past 25 consecutive years) has shown an enormous growth in becoming more and more dictatorship in each elections held every since it got on power by bullet not by ballot in 1991. On may 21 .2015 the ethnic based Ethiopian government organized a fake election as usual for the 5th time since the day it clinged on to the power by slaughtering Ethiopians during the harsh civil war which stayed for about 17 years. The … [Read more...] about Ethiopia’s hope for changing an unwanted government by ballot box dashed
በአዲስ አበባ መብራት እንዳይቋረጥ አንድ ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል
* የከተማዋ መብራት መቋረጥ ችግር የከተማዋ ዕድገት ነው * የችግሩ ምክንያት የኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያና ማሠራጫ ጣቢያዎች እርጅና ነው * የበልግ ዝናብ በተፈለገው መጠን ባለመዝነቡና ግድቦች አለመሙላታቸው ነው ችግሩ * ለጥናቱ 3.5 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ተደርጓል * ዕቅዱ በሚቀጥሉት 20 ዓመታት ተግባራዊ ይሆናል በአዲስ አበባና በአካባቢው ለረጅም ጊዜ እያጋጠመ ያለው የኃይል መቆራረጥ፣ በዋናነት በኤሌክትሪክ ኃይል ማስተላለፊያና ማሠራጫ ጣቢያዎች እርጅና ምክንያት ነው ሲባል ቆይቷል፡፡ ነገር ግን ከቅርብ ወራት ወዲህ ለኃይል መቆራረጡ የበልግ ዝናብ በተፈለገው መጠን ባለመዝነቡ ምክንያት፣ ግድቦች በቂ ውኃ ባለመያዛቸው እንደሆነ ባለሙያዎች እየተናገሩ ነው፡፡ በአዲስ አበባና በዙሪያዋ የሚገኙ 12 የኦሮሚያ ክልል ልዩ ዞን ከተሞች በየጊዜው የሚገጥማቸውን የኤሌክትሪክ ኃይል … [Read more...] about በአዲስ አበባ መብራት እንዳይቋረጥ አንድ ቢሊዮን ዶላር ያስፈልጋል










