‶…ልዑሉ በሰዎች መንግስት ሁሉ ላይ ሙሉ ስልጣን እንዳለውና እነዚህንም መንግስታት ለወደደው እንደሚሰጥ እስክታውቅ ድረስ…″ ዳን.4፡32 ሉዓላዊ መንግስት (sovereign nation) በሌሎች ቅኝ ግዛት ወይም ባርነት ስር ያልወደቀ ራስ-ገዝና ነጻ መንግስት ሲሆን የሃገሪቱ የአመራር አካላት እንደመጨረሻው ውሳኔ ሰጪ አካላት ተደርገው ይወሰዳሉ፡፡ የህዝቡም ሰላምና የሁለንተና እድገት በሃገሪቱ አመራር አካላት ብቃትና ቅንነት ይወሰናል፡፡ ሉዓላዊነት ሌሎች አካላት በአንድ ሃገር የውስጥ ጉዳይ ጣልቃ እንዳይገቡ (meddle) ዋስትና እንደሚሰጥ በማሰብ አንዳንድ መንግስታት በማንአለብኝነት ከእግዚአብሔርም ከሰውም የሚያነካካ እርምጃ ሲወስዱ ይስተዋላሉ፡፡ ከነዚህም አንዱ ለትምህርታችን በቅዱሱ መጽሀፍ በስፋት የተተረከልን የባቢሎን ንጉስ ናቡከደነጾር ነው፡፡ ይህ እግዚአብሔር ባርያዬ/አገልጋዬ … [Read more...] about ልዑል በሉዓላዊ መንግስት ይሰለጥናል!
Archives for September 2016
“ሕዝቡ እኔን አይቶ መታረቅ አለበት” ፈይሣ ሌሊሣ
አትሌት ፈይሣ ሌሊሣ ዛሬ በፌሰቡክ ከጋቢና ቪኦኤ ጋር የቀጥታ ውይይት አካሂዷል፡፡ ስላሳ ደቂቃ አካባቢ በፈጀው ቆይታው ከፕሮግራሙ ተከታታዮች ለቀረበለት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ሕወሃት ደንቁሯል እንጂ ከዚህ በላይ መልዕክት አያስፈልገውም ነበር፡፡ ዜግነቱን ለመቀየር ሃሳብ እንደሌለውና ራሱን ጀግና ብሎ እንደማይቆጥር የተናገረው ፈይሣ ለትግራይ ተወላጆች፣ ትግራዮችን በትግሬነታቸው ለሚጠሉ፣ ለትግራይ ወጣቶች፣ በሥልጣን ለሚገኙት ግፈኛ የህወሃት ባለሥልጣናት፣ ለነ ኃይሌ ገ/ሥላሴና መሰል አንጋፋ አትሌቶች፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለወጣቶች፣ … እስኪበቃው ተናግሯል፡፡ የሰላም ታጋይና ዕርቅ ወዳድ የሆነው ፈይሣ ስለ ዕርቅም በሚገባው ሁኔታ አስረድቷል፡፡ በአማርኛ ያደረገውን ሙሉውን ቃለምልልስ እዚህ ላይ መመልከት ይቻላል፡፡ በአፋን ኦሮሞ ያደረገው ቃለምልልስ እዚህ ላይ … [Read more...] about “ሕዝቡ እኔን አይቶ መታረቅ አለበት” ፈይሣ ሌሊሣ
መልዕክት ለመምህራን
እንደሚታወቀው ከቅርብ ቀናት በፊት ከመስከረም 4 ጀምሮ የሚሰጠውን የመምህራን ስልጠና በምን መልኩ ወደ ተቃውሞ መድረክ መቀየር እንደምንችል መምህራኖችን መጠየቃችን ይታወሳል። መምህራኖችም ግልፅ በሆነ ቋንቋ ሀሳባቸውን ገልፀውልናል። ለዚህም ልናመሰግናቸው እንወዳለን። እኛም ሀሳባቸውን ጨምቀን አቅርበናል። ከዛ በፊት ግን ይህንን ስብሰባ መቃወም ለምን እንደሚያስፈልግ መግለፁ ተገቢ ነው። 1) ይህ ስብሰባ መምህራን ሙያቸውን የሚያሻሽሉበት ሳይሆን ገዥው ፖርቲ የራሱን ፕሮፖጋንዳ የሚነዛበት የፖለቲካ መድረክ ነው። ይህንን ደግሞ ከዚህ በፊት ከነበረው ልምድና ለስልጠናው ከተዘጋጁት ማኑዋሎች መረዳት ይቻላል። ስለዚህ ከዚህ ስልጠና ለመማር ማስተማሩ ሂደት የሚጠቅም አንዳች ነገር አይኖርም። 2) ወያኔ የሀገሪቱን የፖለቲካ ቀዉስ በውይይት ሳይሆን በመሳሪያ ለመፍታት ወስኗል። ይህንን ምርጫም … [Read more...] about መልዕክት ለመምህራን
የእናት ለቅሶ
እናት በፍቅር፣ ጽንስ ይዛ፣ ዘጠኝ ወር አርግዛ፣ ራስዋን ምግብ አድርጋ፣ በማኅጸንዋ ሸሽጋ፣ ሽሉን ወደሰውነት አሳድጋ፣ የፈጣሪን ባሕርይ ተጋርታ፣ ሰው ሆና ሰው ፈጣሪ የሕይወት አለኝታ፣ በጻዕር አምጣ ወልዳ፣ አቅፋ በፍቅር አጥብታ፣ ተጨንቃ አሳድጋ፣ እንቅልፍ አጥታ፣ ሲስቅ ሲያስቃት፣ ሲያለቅስ ሲያስለቅሳት፣ ስትቆጣው እንዲያድግላት እንዲማርላት፣ ክቡር ሰው ሆኖ እንዲያኮራት፣ ያላትን ሁሉ ከፍላ መስዋእት፣ በጉጉት ስትጠብቅ -- ጨካኞች ሬሳውን ጣሉላት፡፡ ማኅጸንዋ ተኮማተረ፤ አንጀትዋ አረረ፤ አስፋልቱ ላይ የተንጣለለው ደም፣ ከልጅዋ አካል ጠብታም አልቀረም፤ ሙት አደረጋት በቁም፤ ከማኅጸንዋ እንደፈሰሰ ተሰማት፤ ተወልዶ ያደገ ልጅ አስወረዳት፤ በወጣት ልጅዋ የፈራረሰ አካል እስዋም ፈራረሰች ወየው ልጄ! ስትል፤ አካልዋ ተፍረከረከ፤ ጉልበትዋ … [Read more...] about የእናት ለቅሶ
የሰማዕታት ዝርዝር በከፊል
Partial list of Oromos that have been killed as a result of Excessive force by Ethiopian Government (TPLF's regime) armed forces during Peaceful demonstration on August 6,2016, Oromia, Ethiopia. (updated 4 September 2016) Nr Name Sex Age Zone Locality Killed by 1 Abbuu Muummee M 17 Arsii Ticho Agazi 2 Abdallaa Mohammed M - East Harageh Qobo Agazi 3 Abda Jiloo M 24 West Arsii Asasa Agazi 4 Abdaa Hasanoo M 31 West … [Read more...] about የሰማዕታት ዝርዝር በከፊል
ምነው! ፈጣሪ አምላክ!
አላለቅስም ያልኩት … እንባ የፈሪ ነው ብዬ ዋጥ ያ’ረኩት፣ አይቻል ተችሎኝ ይዤው የከረምኩት፣ ገንፍሎ ወጣና እንባዬ ፈሰሰ ጉንጮቼን ሰንጥቆ ፌቴን አዳረሰ በዛ እንባዬ መሀል አንገቴን አቅንቼ ለፈጣሪ ጮኽኩኝ! እጆቼን ዘርግቼ ምነው? ፈጣሪ አምላክ ምነው! ረሳኸን ምነው! ይሄን በደል አላይልን አልከን ምነው? የኛን ጩኸት ሰምተህ ጨከንክብን ብዬ ወተውትኩት አልኩበት እዬዬ አሁንም ይፈሳል አልቆመም እንባዬ ምነው! ፈጣሪ አምላክ! … … [Read more...] about ምነው! ፈጣሪ አምላክ!
እኔ አማልሰጣችሁ፣ እናንተ እማትወስዱት! …
ያለ ስም፣ ስም – ስጡኝ ቅጡኝ፣ አስቀጡኝ፤ አግዙኝ፣ ወርውሩኝ፣ … በማጎሪያችሁ እሰሩት… እጀን፣ … በካቴናችሁ ‘ጠንዙት’ እግሬን፣ …. በእግር ብረታችሁ ቸንክሩት፣ ገንዙት፣ … ይደንዝዝላችሁ ሽባ ሆኘ ልቅር፣ ‘’ልሰንከልላችሁ’’:: ……… እንካችሁ …. ጀርባዬን መጫሚያ፣ መዳፌን፤ ግረፉት፣ አቃጥሉት፣ …. በኮረንቲ ገመድ የሰራ አከላቴ፣ ይክሰል፣ ይሁን ዓመድ:: ……… ዝረፉት … ሀብቴን ቤትና ንብረቴን፣ በምድር ያለኝን፤ ሰብስቡ፣ አከማቹት፣ ለዓለም ይሁናችሁ ለማይጠረቃው፣ ለከርስ ዓላማችሁ ለማፍረስ፣ ለመናድ፣ ለጥፋት ግባችሁ:: ……… እንካችሁ…… ደረቴን እንካችሁ…… ግ’ባሬን፤ ለታንክ፣ ለመትረጊስ፣ ለጥይታችሁ አፍስሱት ደሜን፣……. እስኪከረፋችሁ አድቅቁት አጥንቴን፣……. እስኪወጋችሁ::……. እንካችሁ……… እንካችሁ ሥጋ – ሰውነቴን፣ … [Read more...] about እኔ አማልሰጣችሁ፣ እናንተ እማትወስዱት! …
ዲገላው የጎረቤታችን ድመት የገጠመው የሞት አደጋና የወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል በንፅፅር ሲታዩ
በተወለድኩበት በሂርና ከተማ ጎረቤታችን የሆኑ እማማ የልፍተለው እናት የሚባሉ ደግ ሴትዮ ነበሩ። ታዲያ አንድ እሳቸው ያሳደጉት ድመታቸው ከቤት ሸሽቶ ወጥቶ በራሱ ተዳዳሪ ሆነ። በሀረርጌ ከአሳዳሪ ጌታው ቁጥጥር ውጭ ወጥቶ ዱር ገብቶ በራሱ የሚተዳደር ድመት ዲገላ ድመት (ማለትም እንደ አውሬ ዱር የገባ ድመት ማለት ነው) የሚል ስም ይሰጠዋል። ዲገላ ቃሉ ከኦሮምኛ ቋንቋ የመጣ ሲሆን ዛሬ ግን በሀረርጌ ያሉ አማሮችም የአማርኛ ቃል አድርገውት ከላይ በገለጽኩት ትርጉሙ ይጠቀሙበታል። ይህ ድመት በራሱ ተዳዳሪ ከሆነም በኋላ በሰፈራችን ውስጥ ያሉ ጫጩቶችን እየበላ፤ ድስት እየከፈተ፤ የተሰቀለ ቋንጣ እያወረደ ወዘተ የሰፈሩን ነዋሪ በጣም አስቸገረ። ይህ ድመት የእኛንም የዶሮ ጫጩቶች በተደጋጋሚ በልቶብናል። ይህን ድመት እግዚሃብሄር ከገላገላቸውና ከገደለላቸው ለሂርና ስላሴዎች እጣን ይዘን … [Read more...] about ዲገላው የጎረቤታችን ድመት የገጠመው የሞት አደጋና የወቅቱ የኢትዮጵያ ህዝብ ትግል በንፅፅር ሲታዩ
Ethnic cleansing and Ethiopia
The TPLF Party (ህዝባዊ ወያነ ሓርነት ትግራይ) that is in charge of Ethiopia but that mostly parades around as EPRDF is currently on an apology mode and no resource is spared in spreading the well-rehearsed lie. They have activated former leaders from retirement. Old trusted and reliable Cadres are brought out to prove their worthiness in this time of crisis for the mafia group and bloggers and social media activists are on double time. Their task is very easy in Ethiopia. There are no dissenting voices … [Read more...] about Ethnic cleansing and Ethiopia
አክቲቪስቶችና ፖለቲከኞቻችን
ሕዝባዊ ንቅናቄው ከተቀጣጠለ አነሆ አመት አየተጠጋ ነው። በተለይም በጉልህ የኦሮሞ ሞቭመንት አና የአማራው ሞቭመንት በመባል የሚታወቁት ሁለቱ ንቅናቄዎች ሚሊዮኖችን ያሳተፈ በመሆኑ ሕዝባዊነቱ ሌላ ማረጋገጫ አያስፈልገውም። ወያኔ ኢሕአዴግ በሕዝባዊ ንቅናቄና በፖለቲካ ስልጣን ጥያቄ መካከል ያለው ልዩነትና ዝምድና ከባህርዩ የተነሳ ሊገነዘብ ባለመቻሉ ሕዝባዊ ንቅናቄውን የጥቂት ፖለቲከኞች ወይም ጸረ ሰላም ሃይሎች አድርጎ በመቁጠር በተለመደ ጥቂቶችን የማጥፋት የጉልበት ስልቱ ሕዝባዊ ንቅናቄውንም ለማዳፈን ደፋ ቀና እያለ ይገኛል። ይህም እኩይ ተግባሩ በየቀኑ ከሕዝብ አየነጠለው እነሆ አሁን ጠመንጃውን የሚያዙ ጥቂቶች አየተንገዋለሉ ይገኛሉ። በቲዎሪም ሆነ በተግባር ለወያኔ ኢሕአዴግ የሚቀርበው የሌኒን የአብዮት ቲዎሪ አብዮትን ለማምጣት የሚያስፈልጉ ሁኔታዎች ብሎ የገለጻቸው እንደ ቀድሞ መግዛት … [Read more...] about አክቲቪስቶችና ፖለቲከኞቻችን










