• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

“ሕዝቡ እኔን አይቶ መታረቅ አለበት” ፈይሣ ሌሊሣ

September 15, 2016 11:01 pm by Editor Leave a Comment

አትሌት ፈይሣ ሌሊሣ ዛሬ በፌሰቡክ ከጋቢና ቪኦኤ ጋር የቀጥታ ውይይት አካሂዷል፡፡ ስላሳ ደቂቃ አካባቢ በፈጀው ቆይታው ከፕሮግራሙ ተከታታዮች ለቀረበለት ጥያቄዎች ምላሽ ሰጥቷል፡፡ ሕወሃት ደንቁሯል እንጂ ከዚህ በላይ መልዕክት አያስፈልገውም ነበር፡፡

ዜግነቱን ለመቀየር ሃሳብ እንደሌለውና ራሱን ጀግና ብሎ እንደማይቆጥር የተናገረው ፈይሣ ለትግራይ ተወላጆች፣ ትግራዮችን በትግሬነታቸው ለሚጠሉ፣ ለትግራይ ወጣቶች፣ በሥልጣን ለሚገኙት ግፈኛ የህወሃት ባለሥልጣናት፣ ለነ ኃይሌ ገ/ሥላሴና መሰል አንጋፋ አትሌቶች፣ ለኢትዮጵያ ሕዝብ፣ ለወጣቶች፣ … እስኪበቃው ተናግሯል፡፡ የሰላም ታጋይና ዕርቅ ወዳድ የሆነው ፈይሣ ስለ ዕርቅም በሚገባው ሁኔታ አስረድቷል፡፡

በአማርኛ ያደረገውን ሙሉውን ቃለምልልስ እዚህ ላይ መመልከት ይቻላል፡፡

በአፋን ኦሮሞ ያደረገው ቃለምልልስ እዚህ ላይ ይገኛል፡፡

ከተናገራቸው በጥቂቱ፤

“ሰው በጅምላ እየተገደለ፣ እየታሰረ ነው፤ ይህንን አይቼ ነው የተቃወምኩት”

“ለሕዝብ ብዬ ነው ተቃውሞ ሰማሁት፤ ለራሴ ጥቅም አይደለም፤ ጥሩ ኑሮ አለኝ፤ …”fayissa

“ሕዝብ የሥልጣን ባለቤት እንዲሆን ነው ምኞቴ”

“ይህ ሥርዓት ተቀይሮ ለአገራችን ብሮጥ ደስ ይለኛል እንጂ ለየትም አገር መሮጥ አልፈልግም፤ ዜግነቴን አልቀይርም”

“አንድ ቀን ወደ ኢትዮጵያ ተመልሼ እንደምሮጥ ነው ተስፋ የማደርገው”

“ሕዝቡ እኔን አይቶ መታረቅ አለበት”

“ጀግንነት አይሰማኝም፤ ጀግና አይደለሁም፤ የዜግነት ግዴታዬን ነው የተወጣሁት”

ለነኃይሌ ገ/ሥላሴ፤

“እነኃይሌ … ስለ ሪዮ ሲነጋገሩ ነበር፤ … አሁን የምንነጋገረውና የምናስበው ስለሜዳሊያ አይደለም፤ … ስለ አገራችን ስለ ህዝባችን ለምን አይሰማንም”

“ሕዝብ እየተገደለ፣ እየሞተ እንዴት ስለ ሕዝብ አናስብም”

“እናንተ (አንጋፋ አትሌቶች) ሕዝብንና መንግሥትን ማገናኘት ትችላላችሁ”

ለህወሃት ኃላፊዎች፤

“ብዙ ሃብታም መሆን ይጎዳል፤ ለህዝባችሁ አስቡ፤ ለራሳችሁ ጥቅም ብላችሁ አገራችንን ከማፍረስ ብትቆጠቡ ደስ ይለኛል”

ለትግራይ ተወላጆች፤

“ከኦሮሞ፣ ከአማራ፣ ከጋምቤላ ሕዝብ ጋር ሆነው ይህንን ሥርዓት መቃወም አለባቸው፤ ሕዝቡን መደገፍ አለባቸው”

በአጠቃላይ፤

“የአንድ ብሔር የበላይነት (የትግራይ) አለ፤ግን ብዙም አይደለም፤ የተወሰኑ ሰዎች ናቸው፤ ትግሬ ሆኖ ደሃ አለ – የሚለምኑ ትግሬዎች አይቻለሁ”

“የኢትዮጵያ ሕዝብ በትግሬ ቅር ብሎታል”

“እኔ ትግሬ አልጠላም፤ … ጓደኞቼም አሉ፤ … ትግሬዎችን ግን የሚጠሉ አሉ፤ የሚሳደቡ አሉ፤ (ይህንን) ከማድረግ እንዲቆጠቡ ልንግራቸው እፈልጋለሁ”

“እኛ አንድነት ነው የምንፈልገው፤ ይህ መንግሥት ይወድቃል፤ ስለዚህ እነርሱ ሰዉን እንዳያስከፉ”

“(ወጣቶች) በሰላማዊ መንገድ ትግል መቀጠል አለባቸው፤ ሞትም ቢሆን ለትውልድ ነጻነት ሰጥቶ መሞት ነው፡፡”


ማሳሰቢያ፤ በተለይ በስም ወይም በድርጅት ስም እስካልተጠቀሰ ድረስ በጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ® ላይ የሚወጡት ጽሁፎች በሙሉ የጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ®ንብረት ናቸው፡፡ ይህንን ጽሁፍ ለመጠቀም የሚፈልጉ ሁሉ የዚህን ጽሁፍ አስፈንጣሪ (link) ወይም የድረገጻችንን አድራሻ (http://staging.goolgule.com/) አብረው መለጠፍ ከጋዜጠኛነት የሚጠበቅና ህጋዊ አሠራር መሆኑን ልናሳስብ እንወዳለን፡፡

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: News Tagged With: Full Width Top, Middle Column

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule