አንድ መንግስት ልማታዊ ሊባል የሚችለው የሚመራውን ሕዝብ ከዃላ ቀርነትና ከድህነት ኣሮንቓ መንጥቆ ሲያወጣ፣ የህዝቡን ኣንድነትና መልካም ግንኙነት ሲያጠናክር፣ የኣገርን ብሔራዊ ጥቅምና ዳር ድንበር ሲያስከብር ነው። ሕዝብ በኑሮ ክብደት የሚሰቃይበትና የበይ ተመልካች በሆነበት፣ ወጣቱ ተስፋ ቆርጦ ለስደት ሲዳረግና እግረመንገዱን ለተለያዩ ኣደጋዎች የሚጋለጥበት፣ የጎሳ ስሜት ነግሶ ኣንዱ ሌላውን እንዲጠላና ሰላም እንዲናጋ፣ ዜጋ ለዘመናት ከኖረበት ቦታና መሬት በሃይል እየተፈናቀለ እንዲበታተን የሚያደርግ ስርዓት ያሰፈነ ቡድን የሚመራው መንግስት ጥፋታዊ እንጂ ልማታዊ ተብሎ ሊጠራ አይገባውም። የሕዝቡን መብት ገፎ፣ የአገሩን ሃብትና ንብረት፣ ለም መሬት ጭምር ለባእዳን አሳልፎ እየሰጠ፣ እየሸጠና ተባብሮ እየመዘበረ በውጭ አገር ባንክ የሚያካብት ቡድን ስልጣን ላይ ባለበት አገር ውስጥ ልማታዊ … [Read more...] about ጎሳን ለይቶ የሚደረግ ጥቃትን ለማስወገድ መሰረታዊ ለውጥ ያሻል
Opinions
የኔ ሃሳብ
በቤንሻንጉል-ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በሚኖሩ ዐማሮች ላይ የተፈፀመ የዘር ማጥፋት ወንጀል
መግቢያ ሞረሽ-ወገኔ ይህ አስደንጋጭ ዜና እንደደረሰው የድርጊቱን ዘግናኝነት እና ፍፁም ኢሰብዓዊነት ከግንዛቤ ውስጥ በማስገባት፣ ከዚያም አልፎ ያለአግባብ ግለሰቦችንም ሆነ ድርጅቶችን ላለመወንጀል፣ ስለሁኔታው ከሥር መሠረቱ መረጃዎችን ለማጣራት ሙከራ አድርጓል። ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን እና ሰብዓዊነት የሚሰማችሁ ግለሰቦች ሁሉ እንድትገነዘቡልን የምንፈልገው፣ በእንዲህ ዓይነት እጅግ የሚሠቀጥጥ ድርጊት ላይ ዘገባ ለማዘጋጀት ምን ያህል ከባድ የኅሊና ፈተና እንደሚደቅን ንፁሕ ኅሊና እና አስተዋይ አዕምሮ ያለው ሰው ይስተዋል አልባልም። አንዳንድ ጊዜ «ቋንቋ ኃሣብን በትክክል ለመግለጽ ያስቸግራል» ይባላል። ዕውነት ነው፣ እንደዚህ ያለ ለመስማትም ሆነ ለመናገርም የሚቀፍ እና የሚከብድን ድርጊት፣ ድርጊቱን ባየው ሰው፣ በተረዳው እና በገባው መልክ ለሁለተኛ እና ለሦስተኛ ወገን ለመግለጽ … [Read more...] about በቤንሻንጉል-ጉሙዝ ክልል፣ መተከል ዞን በሚኖሩ ዐማሮች ላይ የተፈፀመ የዘር ማጥፋት ወንጀል
ሀገር የማያድስ አዲስ ዓመት ለእኔ ምኔ ነው?!
ዛሬ ላይ የጊዜ ዑደት ተፈጥሮአዊ ልማድ አጃቢና አድማቂ ከመሆን በቀር ዘመን ተሸኝቶ ዘመን ሲተካ አላፊውን ዘመን በመልካምና በበጎ የምንዘክርበት መጪውንም ተስፋ የምናደርግበት አንዳች ተጨባጭና በቂ አመክንዮ (ምክንያት) ያለን መስሎ አይሰማኝም!! ይህን ስል ግን ከእያንዳንዱ ግለሰብ አሊያም ቡድን አንፃር ሳይሆን አንደሀገር ማለቴ ነው፡፡ እነሆ ዳር ላይ ቆመን እንቀበለው ዘንድ የምናሰፈስፍለት የ2008 ዓ.ም በተዳፈነ ዲሞክራሲ የአማራጭ እሳቤ አልባ ወደሆነ የፓርላማ እና የክልል ምክር ቤቶች አስተዳደር ስር የሚዘፍቀን ከዛም ባለፈ ምንአልባትም ሳንሰማና ሳናይ፤ መስማማትና አለመስማማታችንም ሳይታወቅልን በሚደነገጉ የሕግ፣ የደንብ እና የፖሊሲ ድንጋጌዎች የምንዋጥበት ወቅት ጅማሬ ነው ማለት ይቻላል! ለመጠናቀቅና የዘመኑን መቁጠሪያ ወደ 2008 ለመቀየር ጥቂት ቀናት የቀሩት ይህ … [Read more...] about ሀገር የማያድስ አዲስ ዓመት ለእኔ ምኔ ነው?!
ሃሰት ነገሰ፤ ዳቢሎስ ነገሰ ነው
ክርስቶስ በደሙ የዋጀን እኛ ክርስቲያኖችና ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ሃሰትና ቅጥፈት የሚናኝበት እየሆንን ነውና ይህንን ክርስቲያናዊ ያልሆነ ከፋፋይ የሃጢአት ሥራ ለማስቆምና ለማስወገድ የምንጥር እንጂ የሃስትና የቅጥፈት መሣሪያ በመሆን ከክርስቲያን ወገኖቻችን ጋር የምንናቆር አንሁን። ዛሬ በቤተ ክርስቲያናችን ውስጥ ሕዝብን ከሕዝብ የሚከፋፍልና የሚያናቁር ሃሰትና የቅጥፈት ስራ ብቻ መሆንኑን ሁሉም ይረዳ። ሃስትና ቅጥፈትን የደገፈና የተከተለ ክርስቲያን ሁሉ ከሃሰተኞቹና ከቀጣፊዎቹ ያነሰ ሃሰተኛና ኅጢዓተኛ ሊሆን እንደማይችል በሚገባ ሊረዳው ይገባናል። አዕምሮውን የሰይጣን ማደሪያ ካላደረገና የሰው ልጅ ጤና ካልነሳው በስተቀር ውሸትንና ቅጥፈትን መተዳደሪያዬ ብሎ ሊይዝ አይችልም። በተለይም ደግሞ፤ በፈጣሪው አምኖ በክርስትና የተጠመቀና እግዚአብሔርን የሚፈራ ሰው ከሃሰትና ከውሸት ሁሉ … [Read more...] about ሃሰት ነገሰ፤ ዳቢሎስ ነገሰ ነው
Is Africa really rising?
Introduction President Barack Obama praised Africa’s economic performance in his speech on the 2015 Global entrepreneurship summit which was held in Nairobi from July 25-26, 2015. He stressed that Africa is “on the move and the continent is one of the fastest growing region in the world.” Further, he emphasized that “the people are being lifted out of poverty, and income is growing.” In his words, “the middle class is growing and young people are harnessing technology to change the way Africa … [Read more...] about Is Africa really rising?
የድህረ-መለሱ ኢሕአዴግ አሰላለፍና የ“አዲሱ” ሥራ አስፈጻሚ የቢሆን ዕድል
የአራት ድርጅቶች ስብሰብ የሆነው ኢሕአዴግ፤ በሕወሓታዊ የድርጅት መንፈስ እየተመራ የስልጣን ቆይታ ዘመኑን ከአመታት ልኬት ወደ አስርታት ያሻገረ በመሆኑ፣ ከእንግዲህ የአገዛዝ ዘመኑን በክፍለ ዘመን ክፋይ አገላለጽ መጥራቱ ተራዛሚ የስልጣን ቆይታውን ይበልጥ የሚገልፀው ይሆናል፡፡ እናም ሩብ ክፍለ ዘመን ያህል በስልጣን ላይ ያለው ኢሕአዴግ በሰሜን ኢትዮጵያ የፖለቲካ ተዋረድ አገሪቱን “እየመራ” እዚህ ደርሷል፡፡ ግንባሩ ከፊት ለፊቱ አንደ “ትልቅ” ድርጅታዊ ጉባኤ ይጠብቀዋል፡፡ ነሐሴ 20/2007 ዓ.ም በመቀሌ ከተማ የድርጅቱ አስረኛ ጉባኤ መካሄድ ይጀምራል፡፡ የመቀሌው ጉባኤ ከመካሄዱ ከቀናት በፊት፣ አራቱም ድርጅቶች በየክልል ርዕስ ከተማቸዉ የየራሳቸውን ጠቅላላ ጉባኤ በማካሄድ የድርጅታችዉን ሊቀ-መንበርና ም/ሊቀመንበር የሚመርጡ ይሆናል፡፡ ዛሬ ላይ እየታየ ካለው የግንባሩ ከፍተኛ … [Read more...] about የድህረ-መለሱ ኢሕአዴግ አሰላለፍና የ“አዲሱ” ሥራ አስፈጻሚ የቢሆን ዕድል
እነሆ ፍትሃችን
… ቋንጣ ዜና አመጣሽ አትበሉኝና፤ ሰሞኑን ከፌስቡክ ጠፍቼ በከረምኩበት ወቅት የአራት አመት ከስድስት ወር ልጅ የደፈረው ዋልጌ በአራት ወር "ሲቀጣ"፣ ምስር ወጥ የሰረቀው ሰው ደግሞ አመት ከአራት ወር እስር ተፈርዶበታል ሲባል ሰምቼ በንዴት ስንተከተክ ከርምኩ፡፡ ከዚያ ደግሞ እነ አብርሃ ደስታ ሲፈቱ በደስታ ተፍነከነኩ፡፡ …ልጅ ሆኜ እናቴ ሰው ቤት ይዛኝ ሄዳ ለየኔ ቢጤ ምግብ ለመስጠት የሚሰስት ሰው ስታይ፤ "አበስኩ ገበርኩ…!ደግሞ ለሞተ…ለበሰለ ምግብ መስቆንቆን ምንድነው!" ትል ነበር፡፡ እነሆ ፍትሃችን፣ "የበሰለ" እና "የሞተ" ምግብ ለሰረቀው ሰውዬ ፣ አመት ከአራት ወር! "ያልበሰለች" እና "ታዳጊ" ልጅ ለደፈረው ሰውዬ፣ አራት ወር ሆኗል፡፡ እነሆ ፍትሃችን፣ እንዲህ እንዲህ የሌሎችን መብት ግጥም አደርጎ የሚጥስን ማበረታቻ በሚመስል የአራት ወር "ቅጣት" … [Read more...] about እነሆ ፍትሃችን
ለአሚራና ቤተሰቦቿ የጎደለው ፍትህ…!
* የ4 ዓመት ከ6 ወር ህጻን የደፋረን በ4 ወር እስር መቅጣት ምን ይሉታል? * ወላጆቿ "ወላጅ ይፍረደን፣ ህዝብና ሀገር ይፍረደን!"ይላሉ የኢፌዴሪ ህገ መንግሥት ሴቶች ልክ እንደ ወንዶች በሕገ-መንግሥቱ እኩል መብትና ጥበቃ እንዲሰጣቸው ይደነግጋል። ትግበራውን መከታተልና ማስፈጸም ያለባቸው ህግ እውጭና አስፈጻሚ አካላት የሴቶችን መደፈር ለመከላከል የከበደ ኃላፊነት እንዳለባቸው ይህው የፈረደበት ህገ መንግስት ያስረዳል! ዳሩ ግና አልፎ አልፎ የሚሰማ የሚታየው የነገር ጭብጥ ውጤት ህግ አውጭና የሚያወጡት ህግ ደንብና መመሪያ ከወንጀል ፈጻሚው ባልተናነሰ በህግ አስከባሪና አስፈጻሚዎች ህጉ ይጣሳል። ህግ ተጥሶ የዜጎች ሰብአዊ መብት መዳጡ በአደባባይ እየተሰማና እየታየ ህግ አውጭ አካላት የሚወስዱት እርምት እርምጃ አያስደስትም። የሴት ጠለፋ በተለይም በህጻናትና ታዳጊዎች ላይ የሚፈጸም … [Read more...] about ለአሚራና ቤተሰቦቿ የጎደለው ፍትህ…!
ታሪክ የማይረሳው የኮሚቴዎቹ ስቅየት
የኢትዮጵያን ቀጣይ እጣ ፈንታ አጨልመን እንድናይ ከሚያስገድዱን ሁነቶች ውስጥ ለእስልምና ሃይማኖት የትኞችም አይነት ጥያቄዎች በአገዛዙ በኩል እየተሰጡ ያሉ አሉታዊ ምላሾች አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ በኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ ሐምሌ 27/2007 ዓ/ም የተላለፈው “የፍርድ ውሳኔ” ኢሕአዴግ የሚል ገዥ መደብ እስልምናን በምን ያህል መጠን አፍኖ እየገዛ እንዳለ የአደባባይ ማስረጃ ሆኖ ቀርቧል፡፡ በኮሚቴው አባላት ላይ የተላለፈውን “የፍርድ ውሳኔ” ከሃይማኖታዊ መነጸር ባሻገር ጉዳዩን ከፍትህና ከሞራል ልዕልና አኳያ ማየት ተገቢ ነው፡፡ የዚህ አጀንዳ ቀዳሚ ጉዳይ የኮሚቴውን አመሰራረት በማስታወስ የፍርድ ሂደቱን በመጠኑም ቢሆን በመቃኘት የኮሚቴ አባላቱ ቀጣይ እጣ ፈንታ በተመለከተ ሦስት የሚሆን እድል (Scenarios) በማስቀመጥ ማሳየት ይሆናል፡፡ የንቅናቄው … [Read more...] about ታሪክ የማይረሳው የኮሚቴዎቹ ስቅየት
በሪያድ ከተማ በሙስሊም ኢትዮጵያውያን የፀረ ህወሃት/ኢህአዴግ ተቃውሞ ተደረገ
ሰሞኑን ህወሃት/ኢህአዴግ በሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት ላይ የወሰደውን ኢፍተሃዊ ውሳኔ በመቃወም ሪያድ ከተማ ውስጥ አርብ ኦገስት 7 2015 ምሸት ኢትዮጵያዊው ህዝበ ሙስሊም አንድነቱን ጠብቆ ተቃውሞውን አሰምቷል። ቁጥሩ ከፍተኛ እንደሆነ ህዝብ የተገኘበት ይህ ታላቅ ተቃውሞ የአካባቢውን ድባብ ለውጦት እንደ ነበር ለማወቅ ተችሏል። የተከሰተው ነገር በራሳችን እንደደረሰ ተሰምቶን በሶስት ቀን ውስጥ በተጠራ የተቃውሞ ጥሪ ይህን ያህል ህዝብ አንድነቱን ጥብቆ ለተቃውሞ በነቂስ መውጣቱ የትግሉ አንድነት ጥንካሬ መገለጫ መሆኑን የገለጹት ሼክ ሲዒድ አህመድ ህዝበ ሙስሊሙ በአገዛዙ ከባድ ፈተና እንደ ተጋረጠበት አውስተዋል፡፡ ሲቀጥሉም ይህ ፈተና አዲስ ሆኖብን ሳንደናገጥ ትግሉን በበሰለና በሰለጠነ መንገድ በማጠናከር እስከ ድል መቀጠል እንደሚገባ በቁጣ የወጣውን ህዝብ ሙስሊም … [Read more...] about በሪያድ ከተማ በሙስሊም ኢትዮጵያውያን የፀረ ህወሃት/ኢህአዴግ ተቃውሞ ተደረገ










