“በሰባ (ሳባ) ፈረጃ” ሰሞኑን ከያኔ ቴዎድሮስ ካሳሁን የለቀቀው ነጠላ ዜማ ነው፡፡ የዘፈኑ (የሙዚቃው) በነገራችን ላይ ሙዚቃ የአማርኛ ቃል አይደለም ሚውዚክ የሚለው የእንግሊዝኛ ቃል በሀገርኛ አማርኛ ሲጠራ ነው ልክ school አስኳላ እንደተባለው ማለቴ ነው፡፡ እናም ቴዲ ይሄንን ነጠላ ዘፈን እንደለቀቀ ያው እንደሚታወቀው ቴዲ ዝም ብሎ ዘፋኝ አይደለምና ማለትም የሥነ-ኪንን ዓላማና የዜግነት ግዴታን ጠንቅቆ የሚያውቅ የተረዳ በሥራዎቹም ላይ በተደጋጋሚ ይሄንን ያሳየ ከያኔ ነውና በዚህ ነጠላ ዜማው “ምን ብሎ ይሆን?” በሚል ጉጉት አድማጩ ያተኮረው በስንኞቹና መልእክታቸው ላይ ነበር፡፡ ለሁሉም ሊባል በሚችል ደረጃ ይህ ነጠላ ዜማ ቴዲን የማይመጥን ብላሽ ዓይነት ዘፈን ነው የሆነበት፡፡ አንዳንዶችማ ጭራሽ “ቴዲ እንዴት ቢንቀን ነው እንዲህ ዓይነት ፍሬ ፈርስኪ የሆነ ዘፈን በነጠላ ዜማ … [Read more...] about የከያኔ ቴዎድሮስ ካሳሁን በሰባ (ሳባ) ደረጃና ቅኔው
Opinions
የኔ ሃሳብ
2007-A year of decision
Happy New Year Ethiopia (መልካም እንቁጣጣሸ) Meskerem is a special month. We love and honor Meskerem so much that we name our children by it signifying a new beginning for the long journey ahead. Meskerem is the end of the rainy season and our high mountains and valleys adorn themselves in bright yellow flowers as far as the eye can see, totally overwhelming our senses. For a Diaspora, Meskerem in a strange land, is another hard pill to swallow as an exile from a precious homeland. The physical … [Read more...] about 2007-A year of decision
የስደት እፍታ – ፋሲል አየር ወለድ
ጥርስ ያልነቀለበት እትብቱ ዘመዱ ያልተቀበረበት ባዕድ መሬት ባዕድ ዓይኑ ውሃ ኹኖ ቦታው ጭጋግ ለብሶ ባሳብ እየዋኘ ሄደ ተመልሶ አገሩ ናፈቀው አሁን ይህን ጊዜ ዓደይ አበባ ነው ደማቅ ሰማያዊ ወሩ መስከረም ነው አጭር ነበር ጉዞው የሄደው ባሳቡ ወዲያው ተመለሰ ተመለሰ ዓይኑ እምባ አቀረረ። (ግጥም ገብረክርስቶስ ደስታ) ስደት ከወጣሁ ሦስት ወራት አልፎኛል። በቀጥታ የገባሁት ወንድሜ ቤት ነበር። ሚስትና ሁለት ህጻናት ልጆች አሉት። ሆኖም የራሴ የሆነ አንድ መኝታ ክፍል አላጣሁም። ተዋበ በፊት የማውቀውን አይነት ሆኖ አላገኘሁትም። ሳቁ ደርቋል፣ አጫጭር ነገሮች ተናጋሪ ሆኗል። ነገሮች የሰለቹት አይነት ነው። ሊያውራ የጀመረውን እንኳን አይጨርሰውም። በእንጥልጥል እያለ ወደሌላ ይሸጋገራል። የሌላን ሰው ንግግር የሚሰማው ከፊሉን ነው። የገባው ስለሚመስለው አይፈልገውም፤ … [Read more...] about የስደት እፍታ – ፋሲል አየር ወለድ
በአዲስ ዓመት ለተግባራዊ ዕርምጃ መዘጋጀት ይገባል
እንኳን ለ፪ሺ፯ ዓ.ም. አደረሠን፣ አደረሣችሁ! ውድ ኢትዮጵያውያን ወገኖቻችን፦ እኛ ኢትዮጵያውያን በየዓመቱ የመስከረምን ወር የመጀመሪያ ቀን የዘመን መለወጫ ዕለት አድርገን ማክበር የጀመርነው በሺህዎች ለሚቆጠሩ ዘመናት እንደሆነ ይታወቃል። በረዥሙ ታሪካችን እንደየአመጣጣቸው፦ ደስታን እና ሐዘንን፣ መከራን እና ብሥራትን፣ ጦርነትን እና ሰላምን፣ መቆርቆዝን እና መበልፀግን፣ ረሃብን እና አንፃራዊ ጥጋብን፣ ወዘተርፈ አስተናግደናል። ያለፈውን ዘመን ሸኝተን አዲስ ዓመት ስንቀበል ዘወትር መልካም ምኞታችንን እንገልፃለን። ስለዚህ ይህ መግለጫም የኢትዮጵያውያን የዘመናት ትውፊት አንዱ አካል ተደርጎ ሊወሰድ ይችላል። ያገባደድነውን ዓመት ዘመነ-ማርቆስን ስንሸኝ በዓመቱ ውስጥ ያከናወናቸውን ተግባሮች መመዘን ጠቃሚ ይሆናል። ስለሆነም፦ «እኔ ለራሴ ነፃነት መከበር፣ እንዲሁም ወገኖቼ … [Read more...] about በአዲስ ዓመት ለተግባራዊ ዕርምጃ መዘጋጀት ይገባል
LONDON STREETS HOST ANGRY ETHIOPIANS FROM ALL OVER EUROPE
5th September 2014 will go down the history of Diaspora Ethiopians as a one of the great events in the struggle against the treacherous Woyyane regime. It was the third time that Ethiopians from all over Europe came together to raise a storm on the streets of London. The first was on 8th December 2005[i]. The 2nd was on 9th April 2009, when Meles Zenawi came to take part on the G20 London at Excel Business Centre. Now this one raising dust in London with a boom! It appears that the … [Read more...] about LONDON STREETS HOST ANGRY ETHIOPIANS FROM ALL OVER EUROPE
ደኅና ሁኝ ቤተክርስቲያን
ይሄንን ጽሑፍ የጻፍኩት ታች አምና አሁን የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ፓትርያርክ ሆኘ እየመራሁ ነኝ የሚሉት አባ ማትያስ ለማወናበዱ እንዲመች እጣ መሆኑ ቀርቶ በይስሙላ ምርጫ ሐሙስ እንደተመረጡ ቅዳሜ በዕንቁ መጽሔት ላይ የወጣ ነው፡፡ በወቅቱ በጽሑፉ ላይ ሁለት ነገሮችን ተንብየ ነበር፡፡ አንደኛው ፓትርያርክ ተብለው የተመረጡት ሰው እንደ አባ ጳውሎስ ሁሉ ለቤተክርስቲያን ደኅንነትና ህልውና አደጋ እንደሚሆኑ የሚናገረው ሲሆን፡፡ ሌላው ደግሞ የሰይጣን ጆሮው ይደፈንና ከአንድ ዐሥርት ዓመታት በኋላ የክርስቲያኖች (የኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን ምእመናን) በመላዋ ሀገሪቱ የሚኖራቸው ብዛት እጅግ አሽቆልቁሎ ከአዲስ አበባ ሕዝብ ብዛት ያልበለጠ ይሆናል የሚል ነበር፡፡ በወቅቱ ይሄንን ትንበያየን አለቅጥ የተጋነነ አድርገው የቆጠሩት ብዙ ነበሩ፡፡ አስደንጋጭ በሆነ ሁኔታ በጥቂት ወራት ውስጥ አባ … [Read more...] about ደኅና ሁኝ ቤተክርስቲያን
“ሕወሀት ኢሕአዴግ” በቅርብ ጊዜ የብሔራዊ እርቅ ተማጻኝ!
ብሔራዊ እርቅ (National Reconciliation) በተለይ በእርስ በእርስ ግጭት ደም የተቃባንና የከፋ አደጋ የተጋረጠበትን ኅብረተሰብ ወይም የመበታተን አደጋ የተጋረጠባትን ሀገር በይቅር ለእግዚአብሔር ይቅር አባብሎ ሰላም ለማውረድና የቂም በቀልን ዶሴ ዘግቶ በአዲስ መንፈስ ብሔራዊ መግባባትን (National Consensus) ፈጥሮ የአንዲት ሀገርን ሕዝብ በአንድነት አስተባብሮ ለማንቀሳቀስና ህልውናውን ከመረጋጋቱ ጋራ ለማስቀጠል ዓይነተኛ መንገድ ነው፡፡ በሕወሀት ኢሕአዴግ የአገዛዝ ዘመን የዚህ የብሔራዊ እርቅ (National Reconciliation) ጥያቄ በተለያዩ አካላት በተደጋጋሚ ሲቀርብ ቆይቷል፡፡ ነገር ግን የአገዛዝ ሥርዓቱ ይህ እርቅ ቢፈጸም የመጀመሪያውና ዋነኛው ተጠቃሚ እሱ መሆኑን እስከአሁንም ቢሆን መረዳት ባለመቻሉ ምክንያት የተለያዩ የእብሪት ኃይለ ቃሎችን … [Read more...] about “ሕወሀት ኢሕአዴግ” በቅርብ ጊዜ የብሔራዊ እርቅ ተማጻኝ!
የወያኔ የጎሳ አፓርታይድ ሥርዓት በዲያስፖራው ኢትዮጵያዊ ላይ
ወያኔ በለስ ቀንቶት የኢትዮጵያን በትረ ስልጣን ከተቆጣጠረ ጊዜ አንስቶ ከጫካ አዝሎት የመጣውን አብዮታዊ ዲሞክራሲና የአንድን ጎሳ ሁለንተናዊ የበላይነት የማስፈን ዓላማ ለማሳካት ባለው አቅም ሁሉ ሲሰራ ኖሯል። ዘረኛው ወያኔ የትግሬ ጎሳን በመሣሪያነት ለመጠቀም ሲል ጎሳውን በሞራል፤ በኢኮኖሚ፤ በጤናና በትምሕርት ከሌላው የላቀ ደረጃ ላይ ማድረስ በሚለው መርሁ መሠረት የሃገሪቱን ማህበራዊ፤ ኢኮኖሚያዊ፤ ወታደራዊና የደህንነቱን ዘርፍ ሁሉ በትግሬዎች ቁጥጥር ሥር እንዲውል በማድረግ በኢትዮጵያ ውስጥ የጎሳ አፓርታይድ ሥርዓትን ዘርግቶ ይገኛል። ይህ ብቻም አይደለም የወያኔ አገዛዝ መሣሪያ ይሆነኛል ከሚለው ከትግሬ ህዝብና ከትግራይ ክልል በዘለለ ኢትዮጵያ ስለምትባል ሃገርም ሆነ ኢትዮጵያዊ ስለሚባል ሕዝብ ዘለቄታዊ ጥቅምና ጉዳት ባለማሰብ የሥልጣን ዘመኑን ዘለዓለማዊ ለማድረግ ያስችለኛል … [Read more...] about የወያኔ የጎሳ አፓርታይድ ሥርዓት በዲያስፖራው ኢትዮጵያዊ ላይ
የአረብ ሃገሩ ክፉ ስደት!
ገና ረፋዱ ላይ ጸሃዩ ናላን ያዞራል ... የቢሮ የቤት ማቀዝቀዣዎች እንኳ ሙቀቱን ተቋቁመው የማብረድ ስራቸውን እንዳይከውኑ የሳውዲ ጅዳ በጋ ሃሩር ጸሃይ ፈተና ሆኖባቸዋል! ... በዚህ የቀለጠ የበርሃ ሃሩር ጤነኛ መቋቋም ያልቻለው ሙቀት በአንዲት ሰውነቷ የደቀቀ እህት ይወርድባታል ... ቦታውም ከጅዳ ቆንስል ግቢ የቅርብ ርቀት በሚገኝ የአንድ አረብ ግቢ በር ላይ ነው .... ስለዛሬው የማለዳ አሳዛኝ አጋጣሚ ላጫውታችሁ...! ያሻችሁ ተከተሉኝ! የኩባንያ ስራየን በመከዎን ላይ እንዳለሁ እግረ መንገዴን ቀዝቃዛ ውሃና ማኪያቶዋን ለመነቃቂያ ፉት ልበል ለማለት በጅዳ ቆንስል ቅጽር ግቢ ውስጥ ወደሚገኘው የኮሚኒቲ ካፍቴርያ ብቅ ብየ ያችኑ ማኪያቶ አዘዝኩ ... ማኪያቶየን እየቀማመስኩ እንደኔው የካፍቴሪያ ታዋቂ ደንበኞች ከሆኑ ወዳጆቸ ጋር ስንጨዋወት አንድ ሌላው ወዳጃችን ግዙፍ ሰውነቱ … [Read more...] about የአረብ ሃገሩ ክፉ ስደት!
ቴዲ አፍሮ – በሁለት ጽንፎች
ኢትዮጵያ ውስጥ ፈጽሞ ሊተቹ የማይችሉ ሶስት ግዝፍ ነገሮች አሉ። እነዚህም 1ኛ - ሃይማኖት 2ኛ - መንግስት 3ኛ - ቴዲ አፍሮ ናቸው። ከእንግዲህ ቴዲ አፍሮ ዘፋኝ ብቻ ሳይሆን የፖለቲካ መቆራቆዣ ተቋም ሆኗል። ይህን አስመልክቶ ወዳጃችን Girmabbaacabsaa Guutamaa እንዲህ ይላል.... "ቴውድሮስ ካሳሁን aka ቴዲ ኣፍሮ ዘፋኝ ብቻ ኣይደለም። በሃገሪቱ ውስጥ ካሉት ይልቁንም ባብዛኛው ሊታረቁ የማይችሉ (divergent) ማህበረ-ፖለቲካዊ እሳቤዎችን በሚያራምዱ ኤሊቶች ከሚመሩት የተለያዩ ቡድኖች መካከል የኣንዱ ግሩፕ political ideologue ነው ቴዲ።" ይህ ብያኔ (Definition) የተለጠጠ ቢሆንም ውሸት ግን አይደለም። ቴዲ በሁለት ጽንፍ የቆሙ የፖለቲካ ወገኖች መቆራቆዣ አእማድ (Pillar) ሆኗል። የቴዲን ዘፈኖች መተቸት … [Read more...] about ቴዲ አፍሮ – በሁለት ጽንፎች










