ታዲያ ሁላችሁም ለምን ከሥልጣን አትወርዱም? "ለአመጽ የግብረ መልስ የሚሰጥ አመራር እንጂ ለችግሮች ቀድሞ መፍትሄ የሚሰጥ አመራር አይደለም"፤ "አመራሩ ህዝቡ ከሚጠብቀው በታች ነው"፤ "አመራሩ ከሽፏል"፤ የማሸማቀቅና የማስፈራራት ተግባር ነው በፓርቲው ውስጥ ያለው፤ ተመሳሳይ ዓይነት ነገር ወደ ሕዝቡ ሰርጾዋል፤ ወዘተ በማለት "በድፍረት" የተናገረው የኦህዴዱ ለማ መገርሳ እንደዚህ ብቃት የሌለውን አመራር ቢያንስ "ሥልጣኑን መልቀቅ ይገባዋል" ሳይል ወይም ራሱ ሁኔታው የማይስተካከል ከሆነ ሥልጣኑን እንደሚለቅ ምንም ፍንጭ ሳይሰጥ ንግግሩን አብቅቷል። ህወሓት/ኢህ አዴግ እንደ ድርጅት ከሽፏል! ይህ የተመሰከረው ደግሞ በራሱ በአመራሩ ነው። እስካሁን በሥልጣን ለምን እንደቆዩ እና ወደፊትም ለመቆየት ለምን እንዳሰቡ ግልጽ ቢያደርጉ የተሻለ ነው። መለስም "እስከ እንጥላችን ገምተናል" እያለ … [Read more...] about “አመራሩ ከሽፏል” ለማ
tplf
ፎቶና ታሪኩ – እስረኞች [የህወሓት ግፍ ሰለባ ስለሆኑት ወገኖቻችን ሲባል ሊነበብ የሚገባው]
{ፈላስፋ በወህኒ ቤት በራፍ ላይ እንዲህ የሚል ፅሁፍ አነበብኩ አለ፤ ይህች ቦታ የመከራና የጭንቅ ናት፤ ያልሞቱ (በሕይወት ያሉ) ሰዎች የሚቀበሩባት መቃብርም ናት። የወዳጆች መፈተኛ፤ የጠላቶች መደሰቻ የሆነች ቦታ ናትና።} አንጋረ ፈላስፋ (የፈላስፎች አነጋገር)፤ በሊቀ መዘምራን ሞገስ ዕቁበ ጊዮርጊስ በ1953 ዓ/ም ከግዕዝ ወደ አማርኛ ተተረጎመ። ************************************************************* በወያኔ አገዛዝ፤ በወያኔ ቀንበር የካቴናው ስርስር የኮረንቲው ንዝር የመቀመቅ ፍዳው የጨለማው እስር የሰቆቃው ንረት የአውሬዎቹ ምንዝር እንዴት እንደ ሆነ እንዴት እንደነበር ፍትህ በሌለበት ለዳኛ ከመንገር ጠበቃ ከማቆም ዕማኝ ከመደርደር ይኸው የኛ ፎቶ ታሪኩን ይናገር። ፎቶ፤ ሴፕቴምበር 14 2011 (እአአ) የወያኔ ፀጥታ … [Read more...] about ፎቶና ታሪኩ – እስረኞች [የህወሓት ግፍ ሰለባ ስለሆኑት ወገኖቻችን ሲባል ሊነበብ የሚገባው]
የወያኔ “መርህ-አልባ” ክስ ስረ-መሰረትና አፀያፊ “ውነትነት”
ሰሞነኛ መነጋገሪያ የሆነው "ለፖለቲካ እስረኞች ይቅርታ ልሰጥ ነው?” የሚለው ድንገተኛየወያኔ ዛባር (ቅዠት) መሰል ወግ ከመንገዳችን እንዳያወጣን መነጋገሩ አስፈላጊ ሆኖ ስለተሰማኝ የዚህ ጽሁፍ ማጠንጠኛ ላደርገው ፈቀድኩ። “የእስረኛ መልቀቅ” ጩኸት ከአፋኞቹ አፍ አምልጦ እንዲወጣ ያስገደደው ዋነኛ ሀቅ የህዝብ እምቢተኛነትና አልገዛም ባይነት አመጽ ለመሆኑ አንዳች ብዥታ እንደሌለን እየታወቀ ወያኔ “ምህረትና-ይቅርታ” በሚሉ ቃላቶች ዙሪያ፤ በማፈራረቅ ሲዋዥቅ አውቆም ሆነ ሳያውቅ በፈጠረልን “አጀንዳ” የተነጠቀውን ኳስ አስመልሶ ዋናውን የነጻነት ጥያቄበብርሃን ፍጥነት ወደ እስረኛ የማስፈታት ባህሪ እንዳይወርደው ልብ ማለት የተገባ ነው። ለመሆኑ አሁንም አሁንም አጥፍቻለሁ፤ በስብሻለሁ፤ ተግማምቸ -አግምቻችኋለሁ እያለ ሲወሻከት የነበረው የወሮበላ ቡድን “ይቅርታ አስጠይቄ … [Read more...] about የወያኔ “መርህ-አልባ” ክስ ስረ-መሰረትና አፀያፊ “ውነትነት”
መልስ ለዶ/ር በያን አሶባ ቃለ መጠይቅ
የተከበራችሁ አንባቢያን፤ ይህችን መጣጥፍ ለመከተብ የተነሳሁት የዶ/ር በያን አሶባን (የኦሮሞ ዴሞክራሲ ግንባር ቃል አቀባይ) ቃለ መጠይቅ ካደመጥኩ በኋላ ነው፤ አመለካከታቸው ብዙ መልካም አስተሳሰቦችን በውስጡ ያካትታል፤ መልካም የምላቸው አመለካክቶች የኢትዮጵያ ችግር መፈታት ያለበት እዛው ኢትዮጵያ ውስጥ መሆኑ፤ መሰረታዊ ለውጥ ማስፈለጉ፣ በሙሉ እከሌ ከእከሌ ሳይባል የፖለቲካ እስረኞች የመፈታትን ሃሳብ፣ የውጭው ትግል አጋዥነት እንጂ መሪ ቦታ መያዝ እንደማይገባው፤ የሚሉትን ሲሆን ትልቁ ተቃውሞዬ ወያኔን የሽግግሩ አካል ማድረጉ ላይ ነው፤ (በሰላምና እርቅ ሰበብ) ፍራቻቸው ወያኔ አጓጉል አወዳደቅ ከወደቀ አገሪቱ የማትወጣበት ችግር ውስጥ ትገባለች ነው፤ {አገሪቱ የማትወጣበት ችግር ውስጥ ከገባች ሰንብታለች}። ወደ በያን አሶባ ማንነት ስመለስ ለዶ/ር ፍቅሬ ቶሎሳ በመለሱት ደብዳቤ … [Read more...] about መልስ ለዶ/ር በያን አሶባ ቃለ መጠይቅ
IS THE EPRDF OFFER FOR REAL?
IS THE RELEASE OF POLITICAL PRISONERS AN HONEST FIRST STEP TO PRODUCTIVE DIALOGUE LEADING TO RECONCILIATION, MEANINGFUL REFORMS AND RESTORATIVE JUSTICE OR IS IT A MANIPULATIVE SURVIVAL TECHNIQUE FOR THE EPRDF? Washington, DC-- On January 3, 2018, Prime Minister Hailemariam Desalegn publicly declared the EPRDF’S (Ethiopian Peoples Revolutionary Democratic Front) decision to release all political prisoners and to close down the infamous Maekelawi detention center as a confidence-building measure … [Read more...] about IS THE EPRDF OFFER FOR REAL?
The TPLF Should Face an Immediate, Complete & Independent Investigations
Amnesty International, Human Rights Watch,concerned US politicians like Rep. Chris Smith, Rep. Mike Coffman, Ethiopian activists and others who care about human rights in Ethiopia have been exposing tortures, killings and massacres committed by the TPLF (Tigrayan People’s Liberation Front) regime for more than twenty-five years. Most of these crimes are still being committed against many Ethiopians for their political views and ethnicities. Former prisoners, like Habtamu Ayalew, who were lucky … [Read more...] about The TPLF Should Face an Immediate, Complete & Independent Investigations
ጥያቄው አሁንም ግልጽ ነው!
ያለ ሕዝብ ፍላጎትና ምርጫ በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ ራሱን የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) በማለት የሰየመ የአሸባሪ ወንበዴዎች ቡድን አሁንም የውንብድና ተግባሩን እየፈጸመ ይገኛል። ይህ በዓለምአቀፋዊ የአሸባሪዎች መረጃ ቋት ውስጥ በአሸባሪነት የተመዘገበ ድርጅት በነጻ አውጪ ስም ሕዝብ ሲጨፈጭፍ፣ ሲያዋርድ፣ ሲያስር፣ ከአገር ሲባርር፣ ሲያፈናቅል፣ … የኖረ ድርጅት አሁንም በዚሁ ተግባሩ ቀጥሏል። ዓላማ ብሎ የተነሣለትን አገር ማፍረስ የተቃወሙ፣ ሃሳባቸውን በሰላማዊ መንገድ የገለጹ በሙሉ አሸባሪ፣ ጸረ ልማት፣ ጸረ ህዝብ፣ … በማለት ሲገድልና ሲያሰቃይ ኖሮ አሁን ደግም “አላሰርኩም” ሲላቸው የነበረውን እስረኞች “እፈታለሁ” ብሏል። ይህ በህወሓት/ኢህአዴግ ስለተነገረው መግለጫ ጥቂት ነጥቦች ብቻ እናንሳ፤ በመጀመሪያ ኃይለማርያምና ጓደኞቹ በኢትዮጵያ ስም እና ስለ ኢትዮጵያ … [Read more...] about ጥያቄው አሁንም ግልጽ ነው!
ህወሓት/ኢህአዴግ “አሸባሪ” እስረኞችን እፈታለሁ አለ
ላለፉት በርካታ ዓመታት በየአደባባዩ "በኢትዮጵያ ውስጥ አንድም የፖለቲካ እስረኛ የለም" ሲል የነበረው ህወሓት/ኢህአዴግ ዛሬ በኃይለማርያም አማካኝነት "እስረኞችን እፈታለሁ፥ ማዕከላዊን እዘጋለሁ" ብሏል። ባለፉት ዓመታት በግፍ የታሰሩት በሙሉ የተከሰሱት በአሸባሪነት መሆኑ የሚታወቅ ነው። ይህ መግለጫ በራሱ ህወሓት/ኢህአዴግ ሲዋሽ እንደነበር የሚያሳይ ነው ወይም ይቺ ጊዜ መግዣ የህወሓት ጨዋታ ነች። ለሁሉም በመቆየት የሚታይ ነው። የእኛ አቋም ማንኛውም ኢትዮጵያዊ በፖለቲካ አመለካከቱ መታሰር የለበትም፥ በግፍ የታሰሩት ሁሉም የፖለቲካ እና የኅሊና እሥረኞች ህወሓት/ኢህአዴግ ይቅርታ እየጠየቀ ካሣ ከፍሎ በነጻ ይልቀቃቸው ነው። ጎልጉል! … [Read more...] about ህወሓት/ኢህአዴግ “አሸባሪ” እስረኞችን እፈታለሁ አለ
ኢህአዴግና እነለማ ከ“ምን ይዤ ልመለስ?” እስከ “መግለጫ” ማጽደቅ!
ህወሓት የሚዘውረው ኢህአዴግ ከሁለት ሳምንታት በላይ ስብሰባ አድርጎ “መግለጫ” ያለውን “ቀጭን ትዕዛዝ” በማውጣት ተጠናቋል። ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በለውጥ አራማጅነት ሲጠቀሱ የነበሩት እነለማ መገርሳ “መግለጫውን” አብረው አጽድቀው ወጥተዋል። “የጨለንቆን ፍጅት የፈጸመው ማነው?” የሚለውም ደፋር አጀንዳ አብሮ የሞተ ጉዳይ ሆኗል። “ምን ይዤ (ወደ ሕዝቤ) ልመለስ?” በማለት ወደስብሰባው የገቡት ኦህዴድና ብአዴን “የተቀናጁ ተጨማሪ እርምጃዎች” እወስዳለሁ (መግደሌን እቀጥላለሁ) ለሚለው የህወሓት “መግለጫ” ይሁንታቸውን ሰጥተው ወጥተዋል። የትግራይ ሕዝብ ነጻ አውጪ ግምባር (ህወሓት) ከወር በላይ ስብሰባ በማድረግ የደቆሰውና የፈጨውን በተስፈኞቹ ብአዴንና ኦህዴድ ላይ በመድፋት በድንፋታ ኢህአዴግ የሚለውን የድርጅቱን ሥራ አስፈጻሚ መግለጫ በማውጣት መጠናቀቁ ከራሱ ከአገዛዙ የሚዲያ ተቋማት … [Read more...] about ኢህአዴግና እነለማ ከ“ምን ይዤ ልመለስ?” እስከ “መግለጫ” ማጽደቅ!
መፍትሄው በብሄራዊ መግባባት የሽግግር ሂደትን እውን ማድረግ እንጂ ለ27 ዓመት የተደረገውን መድገም አይደለም
ህወሓት-መራሹ የኢህአዴግ ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ 17 ቀናት የወሰደ ስብሰባውን እንዳጠናቀቀ በማመልከት መግለጫ አውጥቷል። ስብሰባው ከመጠናቀቁ በፊት ትልቅና አዲስ ነገር አመላካች የሆነ ውሳኔ እንደሚያሰተላልፍ በተለያየ መልክ ሲጠቁም ቢከርምም፣ የመጨረሻው መግለጫ እንደሚያመለክተው ግን ለኢትዮጵያ ሕዝብ ካለፉት ጊዜያት የተለየ ተስፋ ሰጭ ነገር ይዞ አልመጣም። ይህ ደግሞ ሀገራችን ባለችበት ሁኔታና ሕዝባችን ለመብቱ መከበር እያሳየ ከሚገኘው ቆራጥነት አንፃር ሲታይ ገዥው ህወሓት-መራሹ ኢህአዴግ አሁንም ለሕዝባችን ብሶት፣ ለሀገር ደህንነትና ለአካባቢውም መረጋጋት ደንታ እንደሌለው፤ ከዚያም አልፎ ሥልጣኑን ይዞ ለመቆየት ደግሞ አፈናውን፣ ረገጣውን፣ ከፋፋይነቱን ባጠቃላይም ከፍተኛ ወንጀልን ከመፈጸም እንደማይመለስ አመላክቷል። ሙሉውን ጽሁፍ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ “ጎልጉል፡ … [Read more...] about መፍትሄው በብሄራዊ መግባባት የሽግግር ሂደትን እውን ማድረግ እንጂ ለ27 ዓመት የተደረገውን መድገም አይደለም


![ፎቶና ታሪኩ – እስረኞች [የህወሓት ግፍ ሰለባ ስለሆኑት ወገኖቻችን ሲባል ሊነበብ የሚገባው]](https://staging.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/12/ehrc-300x111.jpg)







