ቀልድ ሲነሳ አስቂኝ ሶስቱ ድንቅ ተዋናዮች አለባቸው ተካ፣ ልመንህ ታደሰና አብርሃም አስመላሽ በልዩ ችሎታቸው ለእኔ እና ለብዙዎች ከፍ ያለ ቦታ አላቸው። ነፍሱን ይማረው አለባቸው ተካ ድሃ እንደደገፈ በአሳዛኝ የመኪና አደጋ አለፈ! ህይወቱን ለጥበብና በፋና ወጊ መልካም ተግባር ተሰልፎ ሲያሳልፍ ተስገብግቦ ሃብት አላካበተምና ለእሱና ለቤተሰቦቹ የረባ ጥሪት ሳይጥል አለፈ ... መልከ መልካሙ ልመንህ ከምድረ አሜሪካ አዕምሮውን ስቶ ከሞቱት በላይ ካሉት በታች ሆኖ በአዲስ አበባ አውራ ጎዳናዎች ይንከራተታል ... የሙያ አጋሮቹ ከምድረ አሜሪካ ያደረጉት ሁሉ ትብብር ቢሳካ ኖሮ ልመንህ ዛሬ ድኖ እናየው ነበር፣ ግን አልሆነምና በናኘበት ከተማ ራሱን ጥሎ ነሁልሎ ማየቱ ልብ ይሰብራል፣ ያሳዝናል! አንዳንድ ወዳጆቸ ልመንህን ለመደገፍ በግል ከሚደረገው ጥረት ባለፈ በተቀናጀ መልኩ እርዳታ … [Read more...] about ስቀው ያሳሳቁን፣ በርተው የጠፉ የጥበብ ሰዎች እና ልናሽረው የማንችለው ቁስል!
Right Column - Primary Sidebar
እኔና አንቺ…፪
መቼም እኔና አንቺን ሲፈጥረን ጉዳችሁ አይለቅ ያለን ነን የኛ ብለን ክብር ሰጥተን ያመነው ሰው ደ’ሞ ከዳን። ይሄን ሰማሁ ይሄውልሽ አንቺም ሰሚው አይቅርብሽ እንደው ቢገርመኝ እንጂ ነገሩ፥ይሄማ ምኑ ይወራል የኛ ያሉት ሲከዳ፥ቃሉ ለአፍ ይመራል ብቻ ምን ይደረግ? ”ውሻ በቀደደው…” ይባል የል የሱስ መክደት ምን ይደንቃል? እንደው ግን ለነገሩ፤ እየገደሉ እያያቸው በደም ተጨማልቆ እጃቸው ከነሱ ጋር አብሮ እየደለቀ ከበሮ የተለጠፈው ውስጣቸው ምን አግኝቶ ምን አጥቶ ነው? በምኑስ ላይ ምን ሊጨምር? መች አነሰው? ንዋይ ክብር በይ ተይው ግድ የለም፤ መቼም-እኔና አንቺን ሲፈጥረን ጉዳችሁ አይለቅ ያለን ነን። እንግዲህ ካልሰማሽም ስሚ፤ ከሰማሽም-ቻልአድርጊው እኛን ያልከዳን ማን አለ? የበደለን … [Read more...] about እኔና አንቺ…፪
No Easy Way to Democratize Ethiopia?
When I read Tagel Getahun’s article - Ethiopia: No Easy Way to Democratize Ethiopia, on one of the Ethiopian websites, I was shocked. Then I went to find out the original source of the article. Alas! – it was the All Africa. Taking it seriously, I figured this is not written by any lawyer ( Tagel Getahun Is a Lawyer. He Can Be Contacted At Tagelgbekele@yahoo.com ) or any one individual but by TPLF leaders, the governing body of the country. It is carefully planned, written, rewritten, reviewed, … [Read more...] about No Easy Way to Democratize Ethiopia?
እረፍት የሚነሳው ህምም
እረፍት አደርግ ብየ ከማህበራዊ መገናኛ መድረኩ ገለል ባልኩባቸው እንደ ብርሃን ፍጥነት በሚወረወሩት ባለፉት ጥቂት ቀናት ከበርካታ ወዳጆቸ በርካታ መልዕክቶች ይደርሱኛል። ብዙው መልዕክት ደግሞ የሚያጠነጥነው በጅዳ እና በአካባቢው በተፈናቃይ የኮንትራት ሰራተኞች አሰቃቂ ስቃይ ላይ ያተኮራል ... ለነገሩ የአብዛኞቹ መልዕክቶች ብቻ ሳይሆኑ ከመልዕክቶች ጋር የሚላኩልኝ መረጃዎች እረፍት የሚነሱ ናቸው! ... አዎ ተንቀሳቃሽ ምስል ጭምር በመረጃነት የታጨቀባቸውን የመልዕክት መረጃ ጭብጦች እውነታ ለማረጋገጥ ወደ ጅዳ ቆንስል አመራሁ ... መኪናየን አቁሜ ትንሽ እንደ ተራመድኩ እያለ ከፊት ለፊቴ አንዲት ልጅ እግር ኢትዮጵያዊ ብቻዋን እያወራች ስታልፍ ስመለከት በመደናገጥ ሰላምታ አቅረብኩላት፣ መልስ ሳትሰጠኝ አለፈች! ደነገጥኩና ባለሁበት ቆሜ በአይኔ ተከተልኳት ... በፈጣን እርምጃ … [Read more...] about እረፍት የሚነሳው ህምም
ኢትዮጵያን እንደገና ማነጽ
መግቢያ የዛሬው የመወያያ ሃሳብ ኢትዮጵያን እንደገና ለማነጽ ኣዲስ የማህበራዊ ፖለቲካ መዋቅር በማስተዋወቅ ላይ ያተኮረ ነው። ይህ መዋቅር ኢትዮጵያን ወደ ኣዲስ ኪዳን የሚጋብዝ ነው። ኢትዮጵያ የገጠማት የከፋ ችግር በኣብዛኛው ከታችኛው የማህበራዊ ፖለቲካ (socio politics) መዋቅር ጋር የተገናኘ በመሆኑ በዚህ ላይ ኣማራጭ ሃሳብ ማምጣት በተለይ ይህ የኣሁኑ ትውልድ የሚጠበቅበት ይመስላል። ያለፉትን ችግሮች ኣስር ጊዜ እያወጣን ብናወርዳቸው ድካም ብቻ ይሆንብናልና። በተለምዶ ያ ትውልድ እያልን የምንጠራው ቀዳሚው ትውልድ ኣንድ የሆነ ሼል ሰብሮ የወጣ ነበር። ያ ትውልድ ለዘመናት የነበረውን ዘውዳዊ ኣገዛዝ ደፍሮ የጠየቀ፣ የፍትህና የእኩልነትን ጥያቄዎች ኣንግቦ ግንባሩን ለጥይት የሰጠ በመሆኑ ታሪክ ሁልጊዜም ያ ትውልድ....እያለ ሲያስታውሰው እንዲሁ ይኖራል። ያ ትውልድ የሆነ … [Read more...] about ኢትዮጵያን እንደገና ማነጽ
”ዛሬም ታለቅሳለች!”
''ዛሬም ታለቅሳለች!'' ትላ’ትናም - ዛሬም ቁማም - ተቀምጣም በውኗም - በህልሟም፤ እምባ እያዘነበች ደም እያፈሰሰች፤ ሁሉንም እያየች ዛሬም ታለቅሳለች።……. ‘’ረስታ - ተረስታ በራሷ ላይ ዘግታ፤ ከጥዋት እስከማታ እንቅልፏን ተኝታ’’። ተብሎ ተወርቶባት ለብዙ ዘመናት ታሪክ ተጽፎባት፤……. እሷ ግን፣ እሷ ናት ዓለም የሚያያት፤ እምባ እያዘነበች እህህ…… ትላለች ትንሰቀሰቃለች፤ ሁሉንም እያየች ዛሬም ታለቅሳለች።……… ተማፅኖ ተማሎ ተገዝቶ ምሎ ገ’ሎና አስገድሎ ፤ ‘’ለ’ርሀብ - ‘ርዛትሽ ለልመና - ፅናትሽ ለፍትህ - እጦትሽ ለሰላም - ለፍቅርሽ፤ መድሀኒት አውቃለሁ እኔ እሻልሻለሁ’’፤ ብሎ የሚገባው እምባዋን ሊጠርገው መፍሰሱን ሊያቆመው፤...... ጭራሽ አብሶባት ሀዘን ደራርቦባት፤ ማቁን አስለብሶ አመድ … [Read more...] about ”ዛሬም ታለቅሳለች!”
ፈስ አጣርቶ የሚያስቀር ውስጥሱሪ በአሜሪካ እጅግ ተፈላጊ ሆኗል
በእንግሊዝ የተፈበረከው ፈስ የሚያጣራ ውስጥሱሪ በአሜሪካውያን ዘንድ በከፍተኛ ሁኔታ ተፈላጊነቱ እየመጣ መምጣቱ ተሰምቷል፡፡ የአምራች ኩባንያ አፈቀላጤ የሆኑት ሲናገሩ “ከአጠቃላይ ሽያጫችን ውስጥ በአሜሪካውያን የሚገዛው እጅግ ከፍተኛውን ቁጥር የያዘ ነው” ብለዋል፡፡ ታዋቂው የውስጥሱሪ አምራች ሽሬዲስ በቅርቡ ፈስ አጣርቶ በማስቀረት እንዳይሸት የሚያደርግ ውስጥሱሪ ለወንዶችና ለሴቶች ለገበያ ማቅረቡ ከተሰማ በኋላ ሽያጩ በ400% አድጓል፡፡ ኩባንያው እንደሚለው በውስጥሱሪው የውስጠኛ ክፍል ከካርቦን የተሰራ ዞርፍሌክስ የሚባል ጨርቅ የተሰፋ ሲሆን ይህም አማካይ የሽታ መጠን ያላቸውን የፈስ ዓይነቶችን 200 ጊዜ ያህል እንዳይሸቱ የማድረግ ችሎታ እንዳለው አፈቀላጤዋ ጨምረው ገልጸዋል፡፡ ሲቀጥሉም “ይህ የውስጥሱሪ ለሁሉም የሚያስፈልግ ነው፤ ምክንያቱም ሁሉም ሰው ይፈሳል” በማለት … [Read more...] about ፈስ አጣርቶ የሚያስቀር ውስጥሱሪ በአሜሪካ እጅግ ተፈላጊ ሆኗል
“በአንድ ቀን ትምህርት ፎቶ አንሺ ሆኜ ቁጭ አልኩ” የ69 ዓመቷ አረጋዊ ወ/ሮ ባዩሽ
ካዛንቺስ አካባቢ በልመና የሚተዳደሩ አንድ አይነሥውር ሽማግሌ አሉ፡፡ የሚለምኑት ከካዛንቺስ ስድስት ኪሎና ፒያሳ ለመሄድ ታክሲ ከሚጠብቁ ተሳፋሪዎች ነው፡፡ አንድ ቀን በእለቱ የለመኑትን ገንዘብ ታክሲ እየጠበቅሁ ባለሁበት ቁጠርልኝ አሉኝ፡፡ እስከ ቀኑ 11 ሰዓት አርባ ብር ለምነዋል፡፡ በሌላ ቀን ተመልሼ ጠየቅኋቸው። በልመና ከሚያገኙት ገንዘብ ልጃቸውን ኮሌጅ አስተምረዋል፡፡ ልጃቸው ሥራ ከያዘ ከዓመታት በኋላም ግን ልመና አላቆሙም፡፡ አሁንም እዚያው ካዛንቺስ እየለመኑ ነው፡፡ “ለምን ልመና አያቆሙም?” አልኳቸው፡፡ “ምን ላድርግ ቁጭ ልበል እንዴ?” በማለት እኔኑ መልሰው ጠየቁኝ፡፡ እዚያው ካዛንቺስ የሚለምኑ ሌላ አረጋዊ ከፍተኛ የእይታ ችግር አለባቸው፡፡ በምፅዋት የሚያገኙትን ሳንቲም ይዳብሱና አምስት ሳንቲም ከሆነ መልሰው ይወረውሩታል፡፡ በአንፃሩ የእይታም የአቅምም ችግር … [Read more...] about “በአንድ ቀን ትምህርት ፎቶ አንሺ ሆኜ ቁጭ አልኩ” የ69 ዓመቷ አረጋዊ ወ/ሮ ባዩሽ
ምሁር (intellectual)
ከሰው ወይ ከአምላክ ፤ ተምሮ የረቀቀ ቀለም ብዙ የጠጣ ፤ ከባሕር እየጠለቀ ተለይቶ የወጣ ፤ በርቶለት የራቀ አንጥሮ አብጠርጥሮ ፤ መርምሮ የላቀ በአዎንታዊ እሴቶች ፤ ጌጦ ያሸበረቀ ደግነትን ከሸር ፤ ልማትን ከጥፋት ፤ ለይቶ የጠበቀ የሚያሰነካክለውን ፤ የት እንዴት እንደሆን ፤ ነቅቶ የጠነቀቀ ነበር ምሁር ማለት ፤ መሻል መብለጣቸውን ፤ አጣጥሞ ያወቀ አዬ ድንቄም አያ ii ፤ ምሁሩ ሊቅ ዐዋቂ የሀገር አደራ ጠባቂ በአረጋዊያን ተመራቂ በታናናሾቹ ተደናቂ ትውልድን አናጭ አምጣቂ አብእናን ቀራጭ አላቂ በዕውቀት በጥበብ አርቃቂ ለችግር መፍትሔን አፍላቂ የሥልጣኔን ብርሃን ፈንጣቂ ለሀገር ለወገን መከታ ለትውልድ ተስፋ አለኝታ መመኪያ ደጀን ስጦታ አይደለም ? ትርጉሙ ሲፈታ ? አዪ … እ !! ድንቄም ዐዋቂ የመጠቀ የእንስቷን ተስፋ የደመቀ በወላጅ … [Read more...] about ምሁር (intellectual)
አህያው ማን ነው? የሚመለከተውስ ብሔር አለን?
ይህንን ጽሑፍ ከጻፍኩት ዓመታት ተቆጥረዋል፡፡ በወቅቱ ጽሑፎቸን ያስተናግድ የነበረ አንድ ዝነኛ የሬዲዬ (የነጋሪት-ወግ) ዝግጅት የጽሑፉን ይዘት ነግሬው እንዲያቀርበው ስጠይቀው አይ ስላለ የሚስተናገድበትን የነጋሪተ-ወግ መድረክ በማጣት በኋላም ተዘንግቶ ቆይቶ አንድ ሰነድ ፈልጌ ካርቶን ሳገላብጥ አገኘሁትና አሀ……. ለምን ታዲያ አሁን ቢያንስ በጋዜጣና በመካነ-ድሮች በኩል ለአንባቢያን አላደርሰውም በሚል አምጥቸዋለሁ የተጻፈው እንዳልኳቹህ ከ4 እና 5 ዓመታት በፊት ነው እንካቹህ፡- ሰሞኑን በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን (ምርዓየ-ኩነት) ራሱ ጣቢያው ያዘጋጀውን አንድ ውይይት ተመለከትኩ የመወያያ ርእሳቸው የነበረው አዲስ አበባ ውስጥ ባሉ የሀብታም ልጆች በሚማሩባቸው የመጀመሪያ ደረጃ ት/ቤቶች በከፊሎቹ ልክ ተማክረው ያደረጉት በሚመስል መልኩ ማሰብ ከሚችሉ ዜጎች ፈጽሞ የማይጠበቁና የድፍረት … [Read more...] about አህያው ማን ነው? የሚመለከተውስ ብሔር አለን?










