• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

እኔና አንቺ…፪

November 1, 2013 05:49 am by Editor Leave a Comment

መቼም እኔና አንቺን ሲፈጥረን

ጉዳችሁ አይለቅ ያለን ነን

የኛ ብለን ክብር ሰጥተን

ያመነው ሰው ደ’ሞ ከዳን።

ይሄን ሰማሁ ይሄውልሽ

አንቺም ሰሚው አይቅርብሽ

እንደው ቢገርመኝ እንጂ ነገሩ፥ይሄማ ምኑ ይወራል

የኛ ያሉት ሲከዳ፥ቃሉ ለአፍ ይመራል

ብቻ ምን ይደረግ?  ”ውሻ በቀደደው…” ይባል የል

የሱስ መክደት ምን ይደንቃል?

እንደው ግን ለነገሩ፤ እየገደሉ እያያቸው

በደም ተጨማልቆ እጃቸው

ከነሱ ጋር አብሮ

እየደለቀ ከበሮ

የተለጠፈው ውስጣቸው

ምን አግኝቶ ምን አጥቶ ነው?

በምኑስ ላይ ምን ሊጨምር?

መች አነሰው? ንዋይ ክብር

በይ ተይው ግድ የለም፤ መቼም-እኔና አንቺን ሲፈጥረን

ጉዳችሁ አይለቅ ያለን ነን።

እንግዲህ ካልሰማሽም ስሚ፤ ከሰማሽም-ቻልአድርጊው

እኛን ያልከዳን ማን አለ? የበደለን እኮ ብዙ ነው

አረ! ብዙ ነው የተጫነን ሊጫነንም የተነሳ

በስቃያችን የወፈረ በረሃባችን ያገሳ

እንተወው ግድ የለም! ምን ያደርጋል ቁጥሩ

ምን ሊሰራልን ስፍሩ

ስሙንም ተይው ማንም ይባል

ስሙ ከክዳት መች ያድናል

ታዲያ ይሄንን በልቦናሽ እያወቅሽ

ስምና ክብሩ ምን ሊበጅሽ?

ይሄው አታይም ደፋ ቢልብን ቀኑ

ከዘፋኙ፣ ከደራሲው፣ ከገጣው፣ ከካህኑ

ከሯጩ ሳይቀር ከጋዜጠኛው፣ ከዶክተሩ

ከተዋኒው፣ ከተማሪው፣ መምህሩ

ማል ሳንለው ምሎ

በል ሳንለው ብሎ

ባነጋገሩ ፈሊጥ አታሎ

ራሱን ከኛ ጋር ሸምልሎ

አናምነው የለን አምነነው

ልባችንን ከፍተን ሰጥተነው

ሲተሻሸን ሲያሸተን ከርሞ

አፍንጫውን እንደውሻ አቁሞ

ስንቱ ከድቶናል እባክሽ

መክዳትማ ብርቅ እንዳይሆንብሽ

አንዳንዴ ግን-ክህደቱ ሲጠናብኝ

ነገሩ ሆዴ ገብቶ ሲያማስለኝ…

ብቻዬን መሆኔን ፈትሼ

አንገቴን ደፍቼ አይኔን መልሼ

የታሪክ ዘርፋችንን ጉዞ ሚስጥር

በልቦናዬ እያገዋለልኩ ስመረምር

ይሄ ሁሉ የቤታችን ጋሬጣ

ይሄ ሁሉ የውጪ ባላንጣ

ጨርሰናቸዋል ብሎ ሊቀብረን ሲመጣ

እንደገና ቀና ብለን

ዓይናችንን ከፍተን ያየን

ማንም ችሎ ያላጠፋን

በዘር በቂም የማንፋጅ

ታሪካችን የማያረጅ

አለ መሪ አለዳኛ

የምንኖር እናው በኛ

ከግዜሩ ቃል የማንርቅ

በይቅርታ ምንታረቅ

መልከ መልካም ጨዋ ደጎች

ሰላም ፍቅር ፈላጊዎች

መሆናችችንን ሳስብ

የኛነታችንን ልክ ስገነዘብ

ይች የአሁኗ ክዳት

ይች ያሁኗ ዘረኝነት

ይች ያሁኗ ጭካኔ

ይቺ ያሁኗ ሁሉን ለኔ

እንኳንስ የአንድነታችንን ችካል

አቅም ኖሯት ልትነቃቅል

እንኳንስ የታሪካችንን ሀቅ

አቅም ኖሯት ልትነቀንቅ

እንኳንስ የባንዲራችንን ቀለም

መልኩን ሽራ ልታጨልም

እንኳንስ የቃል ኪዳናችንን ተስፋ

አቅም ቋጥራ ልታጠፋ

እንኳንስ በወሬ ስፍር ክምር

የኢትዮጵያዊነታችንን  ልትሸረሽር

እንኳንስ ልትመርዘን፤ ልትበርዘን ይቅርና

ለራሷንም አይኖራት እርባና

ለዘመናት የደረጀን የባህል ውርስ

በደማችን የታተመን የታሪክ ቅርስ

የኢትዮጵያዊነታችንን ጽኑ መንፈስ

ማንም አይችል ለመደምሰስ

ይሄንን ተረጂልኝ፤ ፊትሽ አይጥቆር- እባክሽ

በስንቱ አዝነሽ ትችያለሽ

ይልቅስ ለከዳን ነው የሚታዘንት

ህዘብ ፍቅሩን ላነሳበት

ዝና ክብሩን ለሻረበት

ስራው በቁም ለሞተበት

ለሱነው ማዘን ለስሙ

ለጠወለገችበት አለሙ

ለሱ ነው ሀዘን የሚአስፈለገው

ቀብሩን በቁሙ ላደኸየው

አዎን! ለሱ ነው ማዘን አይዞሽ

ደጋግሜ እንደነገርኩሽ

እኛማ ምን እንሆናለን ብለሽ?

በዘር በቂም የማንፋጅ

ታሪካችን የማያረጅ

አለ መሪ አለዳኛ

የምንኖር እኛው በኛ

ቀሩ ሲሉን የቀደምን

ሞቱ ሲሉን የተነሳን

ስንቱ ክህደት ያላጠፋን

ታምረኛ ብቻ ሳንሆን

እኔና አንቺ ታምርም ነን!

***

Welelaye2@yahoo.com

እኔና አንቺ … ፩  ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

 

Print Friendly, PDF & Email

60

SHARES
Share on Facebook
Tweet
Follow us
Share
Share
Share
Share
Share

Filed Under: Literature Tagged With: Right Column - Primary Sidebar

Reader Interactions

Leave a Reply Cancel reply

Your email address will not be published. Required fields are marked *

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule