ለወትሮው ከገዢው ፓርቲ አካባቢ የተለመደው የተሃድሶ ትርጉምለየትያለ ነበር። “ኢህአዴግ” ስብሰባዎችን ያደርግና ሲጨርስ “የተሃድሶ ሰኣት!” ይባልና በዚያን ጊዜ የማእድ አገልግሎትና የተለያዩ መጠጦች የኪነት ትርኢት የሚቀርብበት ሰኣት ተሃድሶ ይባላል። ለአንድ የገዠው ፓርቲአባል ተሃድሶ ሲባል ቶሎ ወደ ህሊናው የሚመጣው ነገር ድግስ ይመስላል። ከስብሰባ በኋላ ዘና ማለት። ይሁን እንጂ በቅርቡ ጠቅላይ ሚንስትሩ በጥልቀት በመታደስ ላይ ነን ሲሉ የገለፁ ሲሆን ይህ ተሃድሶ በአእምሮ መታደስን-መለወጥን የሚያሳይ እንደሆነ ተገልፃልናል። ይሁን ይሏል። መቼስ የተሃድሶ ትርጉም ከድግስ አልፎ እውነተኛ ትርጉሙን ከያዘና በአእምሮ መታደስን ከጨመረ አንዳንድ ለውጥ የናፈቀው ቢጓጓ አይፈረድም ይሆናል። በመሆኑም ተሃድሶከተለመደው ትርጉም አልፎ በአእምሮ መለወጥን መታደስን ሪፎርሜሽንን ካመጣ ግሩም ነበር። … [Read more...] about ከጥልቅ ተሃድሶው ማግስት ዘመቻ ዘ-ፀዓት
Right Column - Primary Sidebar
ካሰቡት ግብ ለመድረስ ፣ያመኑበትን ዓላማ አንግቦ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ!
የዛሬ አራት ዓመት ዐማራ ነኝ ብሎ ደፍሮ ለመናገር ብዙ ማሰብና ማውጠንጠን ይጠይቅ ነበር። ምክንያቱም ላለፉት 50 እና 60 ዓመታት በዐማራው ነገድ ላይ የተነዛው ፕሮፓጋንዳ በሁለት መሠረታዊ ምክንያቶች ዐማራ ነኝ እንዳይሉ ገደብ የጣሉ ነበሩ። የመጀመሪያው ምክንያት ዐማራው ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ የሚያምን በመሆኑ፣ ራሱን ወደ ነገድ ደረጃ ማውረድ ውርደት ወይም ከኢትዮጵያዊነት የሚያፋታው አድርጎ መቁጠሩ አንዱ እና ዋነኛው ምክንያት ነው። ሁለተኛው በኢትዮጵያ ታሪካዊ፣ የሩቅና የቅርብ፣ የውጭና የውስጥ ጠላቶች የተራገበው ኢትዮጵያን የማጥፋት የተቀነባበረ ዘመቻ ዋነኛው ዒላማ ዐማራው በመሆኑ፣ የዐማራውን ማንነት ጥላሸት የቀባ፣ መልካም ስሙንና ዝናውን ያጎደፈ፣ «በጡት ቆራጭነት፣ በወራሪነት፣ በገዥ መደብነት፣ በጨቋኝ ብሔርነት፣ በነፍጠኝነትና በኢትዮጵያ ውስጥ ተፈጠሩ ለተባሉ ችግሮች ሁሉ ፈጣሪ» … [Read more...] about ካሰቡት ግብ ለመድረስ ፣ያመኑበትን ዓላማ አንግቦ በቁርጠኝነት መንቀሳቀስ!
“[ሰዎች] አለሙያቸው ሙያ እየጫንባቸው አበላሽተናቸዋል” ወለላዬ
ሰላም ጎልጉሎች . . . እንኳን ለገና በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ከኢትዮጵያ ዛሬ ጋር በግጥሞቼ ሳቢያ ቃለ መጠይቅ አድርጌ ነበር። እናንተም ግጥሞቼን በተገቢው ሁኔታ ያስተናገዳችሁልኝ ስለሆነ እናንተም (ዘንድ) ቢታተም እወዳለሁ። በድጋሚ መልካም በዓል ይሁንላችሁ። ወለላዬ መዝጊያ ትሁንልኝ መቶ ራት ግጥሞችን - ተሸክሜ ይዤ፤ ረብዕ ረቡዕ ስጥል - አንድ አንዷን መዝዤ በዚች ባሁኗ ቀን - በጨበጥናት ሳምንት፤ ወሩን ስደምረው - ሆነኝ ሁለት ዓመት፡፡ ዳግም በአዲስ ዓመት - እስከምንገናኝ፤ የዘንድሮው መዝጊያ - ይቺ ትሁንልኝ፡፡ (ወለላዬ) ወለላዬ በየሳምንቱ ረቡዕ ረቡዕ በኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ ላይ ለሁለት ዓመታት ያህል ሳያቋርጥ 104 ግጥሞች በመጻፍ አስነብቦናል። በነዚህ ግጥሞቹ እኛን ሆኖ ውስጣችን ገብቶ ያልተናገርነውን ተናግሮልናል። ታዝበን ያለፍነውን … [Read more...] about “[ሰዎች] አለሙያቸው ሙያ እየጫንባቸው አበላሽተናቸዋል” ወለላዬ
በማወቅና በማድረግ እውነትን መኖር?
የሕይወትን እውነትና ትክክለኛ ትርጉም ተረድተን በሰላምና በፍቅር ለመኖር የሚያስችል የአእምሮ መታደስ ለማድረግ የሚከተለውን ላካፍላችሁ፡ ከሁሉ አስቀድሜ ልረሳው የማልችለውን መልካም ባህላችንን ተጠቅሜ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ አደረሰን እላለሁ፤ እኔም ከሃገር፣ ከቤተሰብ፣ ከዘመድና ከጓደኛ ተለይቼ ባህሉንና ወጉን ጠንቅቄ ከማላውቀው ሕዝብ ጋር በእኛ አቆጣጠር ባለፈው ታሕሳስ 16 ቀን 2009 ዓ/ም የፈረንጆችን የገና በአል አክብሬ አሁን ደግሞ የእኛን ታሕሳስ 29 ቀን 2009 ላይ ከኢትዮጵያውያንና ከኤርትራውያን ወገኖቼ ጋር ለማክበር በዝግጅት ላይ ነኝ፤ እዚህ ላይ የቀን ልዩነት ቢኖርም የመከበሩ ዋና ዓላማና የቀኑ ባለቤት የሆነው ግን አንድ ነው፤ እሱም ከድንግል ማርያም ተወልዶ ሰው በመሆን በሰው ልጆች መካከል በመመላለስ “እግዚአብሔር ከእኛ ጋር” ለማለት ድፍረት እንዲሆነን “አማኑኤል” … [Read more...] about በማወቅና በማድረግ እውነትን መኖር?
የምሥራች ነፃነት ላጣው
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን «እስመ ናሁ እዜንወክሙ ዐቢየ ዜና ፍሥሓ…» « ትልቅ የምሥራች ዜናን እነግራችኋለሁ..»ሉቃ ፪፦፲-፲፬፤ ነገር ከሥሩ ውኃ ከጥሩ እንዲሉ የምሥራች ህገ ወንጌልን ለመታወጅ ያበቃውን ስንመረምር ፤ እግዚአብሔር አምላክ በጥንተ ፍጥረት የሰውን ልጅ ወደዚህ ምድር ፈጥሮ እንዲያስተዳድረው ከማድርጉ አስቀድሞ፤የሚተዳድርበትን የሥነ ፍጥረት ህግ አዘጋጀለት፤ ሥጋዊ አካሉ እንዳይዝል የሚያርፍበት ሌሊት ተሐድሶ የሚነሣበት መዓልትን ሰጠው፤ በጨረሯ ሙቀትን በነጸብራቋ ብርሃንን፤ በክበቧ ደስታን የምታጎናጽፈውን የሥሉስ ቅዱስ ተምሳሌት የሆነችውን ጨለማን የምታስወግደውን ፀሐይን አደለው። በልቶ የሚያረካውን ምግበ ሥጋን ሰጠው፤ በጥላው የሚጠለልብትን አበቦችን ዓይቶ በመንፈሱ የሚረካበትን ዕፀዋትን፤ አትክልትና አዝርዕትን የየብስ መደሰቻ መዝናኛውን … [Read more...] about የምሥራች ነፃነት ላጣው
“ኢትዮጵያን አፈራርሰን ኦሮሚያን እንገነጥላለን”
“ሀገር አጥፊው አረም በሀገሬ ሲስፋፋ፣ ሁሉም ተዳከመ የሚያርመው ጠፋ፣ የጊዜ ጉዳይ ነው እኔ አለቆርጥም ተስፋ፣ ሀገሬ ነው የሚል ኢትዮጵያዊ ሁሉ፣ ጥቃቱ ይሰማው ሲቆረስ አካሉ።” ከሊቀ ማዕመራን አበባው ይግዛው “ወይ ሀገሬ” ከሚለው ግጥም የተወሰደ። የአውሮፓ ቅኝ ገዥዎች አፍሪካን እንደ ቅርጫ ሥጋ ለመቀራመት በተነሱበት ወቅት በተለያዩ ሀገሮች እገራቸውን ያስገቡት በሀይማኖት አስተማሪነት ሰም የቄስ ካባ አልብሰው የመረጃ (ሰላይ) ሰዎቻቸውን በመላክ ነው። ማርቲን ሉተር የተባለው የተባለው የጀርመን የሀይማኖት ሊቅ እ.ኢ.አ. በ1517 የካቶሊክ ሃይማኖት መሻሻል አለበት በሚል ያቀረበው ፅንሰ ሃሳብ ተቀባይነት አግኝቶ ዛሬ ሉተራን የሚባል የፕሮቴስታንት ሃይማኖት ዋናው ቅርንጫፍ እንዲፈጠር አድርጓል። እዚህ ላይ የሉተራን ቤተ ክርስቲያን፣ የጀርመንና የኦሮሞ የሉተራን ቤተክርስቲያን … [Read more...] about “ኢትዮጵያን አፈራርሰን ኦሮሚያን እንገነጥላለን”
በኢንተርኔት መቋረጥ 9 ሚሊዮን ዶላር፣ በሞባይል ኢንተርኔት ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር ኪሣራ!
ከአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ መታወጅና ከዚያ በፊት በነበረው ሁኔታ የኢንተርኔት መቆራረጥና መታገድ በኢትዮጵያ ኢኮኖሚ ላይ ጉዳት ማድረሱ የተጠቀሰ ሲሆን ባለፈው አንድ ዓመት አገሪቱን 9 ሚሊዮን ዶላር ገቢ ማሣጣቱን የአሜሪካው ብሩኪንግስ ኢንስቲቲዩት ይፋ ያደረገው ጥናት አመልክቷል። ዴልዮት የተባለው ዓለማቀፍ አማካሪ ተቋም በበኩሉ፤ የሞባይል ኢንተርኔት መዘጋት ሀገሪቱን በቀን 5 መቶ ሺህ ዶላር እያሳጣት ነው ብሏል። በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች ተቃውሞና ግጭቶች መከሰታቸውን ተከትሎ የኢንተርኔት አገልግሎቶች መቆራረጥ፣ ሃገሪቱን በአንድ አመት ጊዜ ውስጥ ብቻ ከ200 ሚሊዮን ብር በላይ አሳጥቷል ብሏል - ዴልዮት። የኢንተርኔት አገልግሎት መቃወስ የኢኮኖሚ እድገቱን እንዲቀዛቀዝ አድርጓል ያለው "አፍሪካን ቢዝነስ"፤ ፈጠራዎች እንዳይበረታቱ፣ የገቢ ታክሶች በአግባቡ እንዳይሰበሰቡና ነጋዴዎች … [Read more...] about በኢንተርኔት መቋረጥ 9 ሚሊዮን ዶላር፣ በሞባይል ኢንተርኔት ደግሞ 200 ሚሊዮን ዶላር ኪሣራ!
ሚዲያ አለኝ ተብሎ የሰው ስብዕና ላይ ክተት አይታወጅም
ሚዲያ እንደ ሰዎች አረዳድ የሚሰጠው ደረጃና አቅም የተለያየ ቢሆንም ያለ አንዳች ማመንታት “ኃይል” ወይም ኃይል ያላቸው መገልገያ መሆኑ ጥርጥር የለውም። ሁሉም ሚዲያ “የሕዝብ” መሆናቸውን ቢገልጹም ፍጹም ነጻና ገለልተኛ ሆነው አይታዩም። ወደ አገራችን ሚዲያ ስንመጣ በውጭ ያሉትም ሆኑ በአገር ቤት፣ የግል የሚባሉትም ሆነ የመንግሥት የራሳቸው ወገንተኛነትና መንሸዋረር ይታይባቸዋል። ይህ እውነት ባደጉት አገሮችም ቢሆን ረቀቅ ባለ መልኩ የሚዘወተር ነው። ከሁሉም የሚቀፈው ግን ፍጹም ጭፍንነት ነው። ምክንያቱም በጭፍንነት ውስጥ አንድ ሰው ከተነገረውና ከተሞላው በቀር አሻግሮ ማየት አይችልምና ነው። “መቃብር ቆፋሪው እና የሬሳ ሳጥን ሻጩ የሚለው ተውኔት የተሰረቀ ነው” የማለት አዝማሚያ በሚስተዋልበት ስሜት የተጀመረ ቃለ ምልልስ። ሲጠናቀቅም የተለያዩ ጉዳዮች ውስጥ ትገባለህ “የባከንክ ነህ” … [Read more...] about ሚዲያ አለኝ ተብሎ የሰው ስብዕና ላይ ክተት አይታወጅም
የሕወሓትን “ሌጋሲ” በጨረፍታ
የወያኔው መንግሥት ያላወረሰን ነገር የለም፡፡ ሁለመናችንን እከክ በእከክ አድርጎናል - በቀላሉ በማይድን እከክ አውርሶን ወያኔም እኛም ጣር ላይ እንገኛለን - አሸናፊው ባልለየለት እልህ አስጨራሽ የአውራ ዶሮዎች ጦርነት ተጠምደን፡፡ የመለስና የድርጅቱ የሕወሓት ውርስ (ሌጋሲ) በአሥራዎች ቀርቶ በመቶዎች ዓመታትም ተዝቆ የማያልቅ ዕዳ አሸክሞናል፡፡ በኢኮኖሚውና በትምህርቱ ረገድ የደረሰብን ኪሣራ ምናልባት በጊዜ ሂደትና ደጋግ ዜጎች የአስተዳደሩን ልጓም ሲይዙ ሊስተካከል ይችላል፡፡ ይህም ሲባል ሚሊዮኖችን በእሳት አለንጋው እየገረፈ የሚገኘው ድህነት ጥርሱን አግጥጦና ዐይኑን አፍጥጦ ዜጎችን የበይ ተመልካች በማድረግ ከማንኛውም ጨዋታ ውጪ እያደረጋቸው እንደሆነና በትምህርቱም በኩል በዘልማድ ከኢትዮጵያ ሕዝብ 85 በመቶው እንደሆነ ከሚነገርለት የሀገራችን ገበሬ በዕውቀት የማይሻሉ ምሩቅ ማይማን … [Read more...] about የሕወሓትን “ሌጋሲ” በጨረፍታ
Ethiopia: The Peril of Complacency in our Community
Hilary Clinton’s historical defeat is no doubt one for the history books, and it is going to be minced and diced for a while. No body, not even Trump and his supporters, saw it coming. Trump, despite his braggadocio, might even have agonized in his mind to himself, “I didn’t mean to win, I swear to God! Why is it happening to me?” For those who are fond of the outcome, it is a miracle that can be compared to hitting the jackpot at the Taj Mahal Casino that Trump himself once owned; and for those … [Read more...] about Ethiopia: The Peril of Complacency in our Community



![“[ሰዎች] አለሙያቸው ሙያ እየጫንባቸው አበላሽተናቸዋል” ወለላዬ](https://staging.goolgule.com/wp-content/uploads/2017/01/fake-mask-300x225.jpg)






