የሰማያዊ ፓርቲ ብሄራዊ ምክር ቤት መጋቢት 14 ቀን 2006 ዓ.ም ባካሄደው ሁለተኛ ዓመት አራተኛ መደበኛ ስብሰባው የካቲት 30 ቀን 2006 ዓም የሴቶች ቀንን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው ሩጫ ላይ በተገኙ የሰማያዊ ፓርቲ ሴት አባላት ላይ ፖሊስና ፍርድ ቤት በመተባበር የፈጸሙትን ሕገ መንግስት የጣሰ ተግባር፣ እንዲሁም ከአሜሪካ መንግስት በደረሳቸው ግብዣ መጋቢት 12 ቀን 2006 ዓም ምሽት ወደ አሜሪካ ለመጓዝ ቦሌ አውሮፕላን ማረፈያ በተገኙት የፓርቲያችን ሊቀመንበር ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ላይ ራሳቸውን ከህግ በላይ ያደረጉ የደህንነት ኋይሎች የፈጸሙትን አሳፋሪና ሕገ ወጥ ተግባር በመመርመር የሚከተለውን የአቋም መግለጫ አውጥቷል፡፡ የሴቶችን ቀን ምክንያት በማድረግ በተዘጋጀው ሩጫ ላይ የተገኙ የሰማያዊ ፓርቲ ሴት አባላት በሩጫው ከተሳተፉ በሺዎች የሚቆጠሩ ሴቶች የሚለዩት … [Read more...] about ለዜጎች ዴሞክራሲያዊ ጥያቄ አፈናና እሰራት ምላሽ አይሆንም
Left Column
እናቴ የእኔ እናት…
እኔ ልሙት አንቺ፣ አንቺ ትሞች እኔ፣ ሳያውቅብን ቀኑ፣ ሳናውቅበት ቀኑን፣ በቁም ያለን መስሎን፣ እናቴ እኔና አንቺ፣ ተለያይተን ቀረን። ሞትን መቀበር ነው፣ በጉድጓድ መከተት፣ ከምድር በታች መዋል፣ ብለህ አትናገር፣ ሌላ ሞትም አለ፣ አታውራ ዝም በል። በእኔና በእናቴ፣ በልጅና በእናት፣ ደርሷል ቆሞ መሞት፣ ቀኑ ወር ተክቷል፣ ወራት ብዙ ዓመታት፣ ሳታየኝ ሳላያት። አዎን! አለች አለሁ፣ አለን እንላለን፣ በስጋ ቆመናል፣ ነገር ግን ውሸት ነው፣ የለሁም የለችም፣ መለየት ገድሎናል። እንዴት ነው፣ ያለችው?፣ እንዴት ነው፣ ያለሁት? እሷ ልጄ እንዳለች፣ እኔ እናቴ እንዳልኳት፣ ተስፋችን ሞቶብን፣ ላታየኝ ላላያት፣ ቆመናል አልልም፣ የለሁም የለችም፣ እናቴ የእኔ እናት... … [Read more...] about እናቴ የእኔ እናት…
A String of Lies Emerged from the ESFNA President Getachew Tesfaye’s Corrupt Leadership
Where does the buck stop? The Ethiopian Sport Federation in North America, ESFNA, needs strengthening. In order to do so, the ESFNA board and its supports need to be informed of the situation at hand and act. This article’s intent is solely to inform the board, the public and establish a stronger ESFNA. An effective board relies on the guidance of an Executive Committee’s (executives) experience, knowledge, and professional opinion. The executives have to recognize that within the boundaries … [Read more...] about A String of Lies Emerged from the ESFNA President Getachew Tesfaye’s Corrupt Leadership
ውዳሴ መስከረም ወጽዮን
በብዙ አገሮች እንዲሁም በኢትዮጵያ የሴቶችና የወንዶች ቁጥር ብዙም አይለያይም፤ እኩል ለእኩል ይሆናሉ፤ ነገር ግን ይህ የቁጥር እኩልነት በኑሮአችን ላይ አይታይም፤ በ1983 የወያኔ ሠራዊት በየመንገዱ ይታይ በነበረበት ጊዜ አንድ ቀን ወደሂልተን ሆቴል ስገባ አንዲት ልጅ ከቁመትዋ የሚረዝምና ከክብደትዋ የበለጠ ጠመንጃ ይዛ አየሁና ዕድሜዋን ብጠይቃት አሥራ አራት አንደሆነ ነገረችኝ፤ ይቺ ልጅ በዚህ ዕድሜዋ ስንት መከራ እንዳየች እግዚአብሔር ይወቀው፤ በዚያን ጊዜ እንደስዋ ያሉ ብዙ ሴቶች ወያኔዎች አይቻለሁ። የመጀመሪያው ወያኔ/ኢሕአዴግ ያዘጋጀው ጉባኤ በተካሄደበት ጊዜ በጉባኤው ውስጥ አንዲት ሴት ብቻ ነበረች፤ እስዋም ከሠራተኞች ማኅበር የተወከለች ነበረች፤ እነዚያ ጠመንጃ እየተሸከሙ በእግራቸው አዲስ አበባ የገቡትና በየመንገዱና በየመሥሪያ ቤቱ በር ላይ ሲጠብቁ የነበሩ የወያኔ ሴቶች … [Read more...] about ውዳሴ መስከረም ወጽዮን
በነፃነት ቀን ነፃነት ማጣት!
ሰብአዊ መብቶች እያንዳንዳችን ሰው በመሆናችን ብቻ የሚገቡን ከሰብአዊነታችን ተለይተው ሊታዩ የማያችሉ መብቶች ናቸው፡፡ መንግስታት እነዚህን በአለም አቀፍ ደረጃ እውቅና የተሰጣቸውን ሰብአዊ መብቶች ለማክበር ለማስከበርና ለማሟላት በቀዳሚነት ኃላፊነት አለባቸው፡፡ በዚህም መሰረት ኃላፊነት ከፈረሙ ቀደምት አገራት መካከል ኢትዩጵያ ትገኝበታላች፡፡ ይሁን እንጂ የሴቶች ሰብአዊ መብቶች በሚፈለገው መልኩ ተግባራዊ ካለመሆኑ ባሻገር ኢፍትሃዊነት እጅግ የበዛ ነው፡፡ ይህም በመሆኑም እ.ኤ.አ. በ1908 በአሜሪካ ኒወርክ ከተማ በጨርቃ ጨርቅ ፋብሪካ ይሰሩ የነበሩ ላብአደር ሴቶች ‹‹ለእኩል ሥራ እኩል ክፍያና የተመቻቸ የሥራ ሰዓት ለሴቶች›› በሚል መፈክር የሥራ ማቆም አድማ በማካሄድ የሴቶች ድምፅ እንዲስተጋባ አድርገዋል፡፡ ይህን ተከትሎ የዓለም ሴቶች በማህበር በመደራጀት ትግላቸውን በማጠናከራቸው … [Read more...] about በነፃነት ቀን ነፃነት ማጣት!
የተገነቡትና በመገንባት ላይ ያሉት የመታሰቢያ ሐውልቶች የሠማዕታት ወይስ የቅሱፋን?
ሕወሓት/ኢሕአዴግ ሥልጣን ከያዘ ጊዜ ጀምሮ በመቶዎች ሚሊዮኖች (አእላፋት) የሚቆጠር የሀገሪቱን ሀብት በማፍሰስ በመጠናቸው በሀገሪቱ ታይተው በማይታወቁ መልኩ በተለያዩ ሥፍራዎች "የሠማዕታት" የመታሰቢያ ሐውልት በማለት አስገንብቷል እያስገነባም ይገኛል፡፡ በምሳሌነት መቀሌ፣ ባሕርዳር፣ ናዝሬት፣ የተገነቡ የመታሰቢያ ሐውልቶችን መጥቀስ ይቻላል፡፡ እነዚህ ሐውልቶች እንዲዘክሩ እንዲያስቡ የሚፈለገው ሕውሓት ኢሕአዴግ በትግል ላይ በነበረበት ወቅት "የተሠው" ታጋዮቻቸውን እንደሆነ ከየሐውልቶቹ ስር ያለው የማስገንዘብያ ጽሑፍ ይገልጻል፡፡ ለመሆኑ በእርግጥስ እነዚህ ጓዶች ሠማዕታት ናቸውን ከሆኑስ ሠማዕትነታቸው ለማንነው? በበኩሌ እነኝህን ታጋዮች ሠማዕታት ብዬ ልዘክራቸው ሳስባቸው ክብር ልሰጣቸው የምችለው ኢትዮጵያንና ጥቅሞቿን በተመለከተ አሁን በሕይወት ካሉት የሕወሓት ኢሕአዴግ ባለሥልጣናትና … [Read more...] about የተገነቡትና በመገንባት ላይ ያሉት የመታሰቢያ ሐውልቶች የሠማዕታት ወይስ የቅሱፋን?
የፀረ ግብረ ሰዶማዊነት ሕጋችን ቢከለስስ?
የዛሬው ጽሑፌ መነሻውና መድረሻው በዚህ ሳምንት አነጋጋሪ ስለነበረው የኡጋንዳ የፀረ ግብረ ሰዶም ሕግና አገራችን በንፅፅር የምትወስደውን ልምድ መቃኘት ነው፡፡ ኡጋንዳ ይህንን ሕግ በማውጣቷ ዓለም ተደንቋል፡፡ አፍሪካን ግን የሚደንቅ አይደለም፡፡ አገራችንንማ ሕጓን እንድታጠነክር ካልሆነ ግብረ ሰዶማዊነትን የሚታገስ ባህልም ሕግም ኖሯት አያውቅም፡፡ ዜናው እጅጉን የሳበው ምዕራባውያንን ነው፡፡ ኡጋንዳ እንደ ሌሎቹ የአፍሪካ አገሮች በአንድ ወቅት ቅኝ ገዥ ስለነበራት የድሮው አስተሳሰብ የተፀናወታቸው ወገኖች ተቃውሞውን አድምቀውት ሰንብተዋል፡፡ አገራችን በማንም ቅኝ ተገዝታ ባለማወቋ፣ ባህሏ የራሷ በመሆኑ ተቃዋሚዎች የመተቸቱን ሞራል የኡጋንዳን ያህል አያገኙትም፡፡ ከዓለም ጋር አንድ በሚያደርገን በተባበሩት መንግሥታትም ቢሆን አንድ የሆነ አቋም ባለመኖሩ፤ ቢኖርም በተዓቅቦ … [Read more...] about የፀረ ግብረ ሰዶማዊነት ሕጋችን ቢከለስስ?
ሙሰኞችና “ሙሰኛው” ፀረ ሙስና
“ . . .የኢትዮጵያ ፀረ ሙስና ኮሚሽን የህዝብንና የመንግስትን ንብረት ለግል ጥቅማቸው በማዋል ክስ የመሰረተባቸውን ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት በቁጥጥር ስር አውሎ ምርመራ እያካሄደ መሆኑን . . . . . . “ የኢቲቪ ዜና “. . . ጉድ ፈላ በቃ ቀጥሎ ሴትዮዋ ነች . . . " የዋህ ኢትዮጵያውያን “. . . እባካችሁ በጥቂት ሺህ ብሮች የወር ደሞዝ የህዝብ አገልጋይ ነን እያላችሁ የሰባት ሚሊዮን ብር መኪና አትንዱ . . .” አፈጉባኤው “. . . የቀድሞው የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት ሙስናን በማጋለጥ ጋር በተያያዘ በታሸገ ውሃ ተመርዘው ነው የሞቱት መባሉን ባናረጋግጥም ከቅርብ ግዜ ወዲህ ግን በኦሮሚያ ክልል መንግስታዊ ስብሰባዎች የታሸገ ውሃ መቅረብ መቆሙን አውቀናል . . . “ ለስርዓቱ እጅግ የቀረቡ የመንግስት ጋዜጠኞች ባለፈው ሰሞን ጥቂት የመንግስት … [Read more...] about ሙሰኞችና “ሙሰኛው” ፀረ ሙስና
ኢህአዴግ – ሌባ ወይስ አገር አስተዳዳሪ?
ከላይ የጠየቅነው ጥያቄ ዛሬ የተነሳ አዲስ ነገር አይደለም። ኢህአዴግ መሰረቱን ዝርፊያ ላይ ያደረገ አገር አስተዳዳሪ መሆኑ ግብሩ ራሱ ምስክር ነውና "ሌባ አገር አስተዳዳሪ" ስለመሆኑ ማስተባበያ ሊያቀርብም አይቻለውም፤ አያስፈልገውም። ሌብነቱ አገርንና ህዝብን ወደ ገደል እየሰደደ መሆኑ ግን ሁሌም የሚያስጨንቅ ነውና ዛሬ እንደ አዲስ አነሳነው እንጂ!! ኢህአዴግ ግዙፍ፣ ሃብቱ በዶላር ካልሆነ በብር የማይቆጠር፣ በህገወጥ ንግድ ሰላማዊ ነጋዴዎችን የሚውጥ፣ ለብቻው መግቢያና መውጪያ የተዘጋጀለት፣ የተለየ ጨረታና የነጻ ቀረጥ እድል የሚበጅለት፣ በየትኛውም ተቋም እንደፈለገ መጋለብ የሚችል ልጓም አልባ የሆነ፣ በፈለገው ቦታና ማህበረሰብ ጥቅም ላይ እንዳሻው ከበሮ እየደለቀ የሚጨፍር፣ ጡሩምባ ይዞ የሚያንጠራባ፣ የፈለገውን ማስወገድ፣ ማሳገድ፣ ማስከፈት፣ ማዘጋት የሚችል፣ ድንበርና ኬላ … [Read more...] about ኢህአዴግ – ሌባ ወይስ አገር አስተዳዳሪ?
በክርስትና ላይ ጥናታዊ ምርምር ሲያደርግ የነበረው ሰው በራሱ ሕይወት ላይ ምርመራ ተደርጎበት እጁን ሰጠ!!!
ወንድ ልጅ ሲወለድ አባት ለተወለደው ልጁ ጠብ - መንጃ (ጠመንጃ) ለመግዛት ደፋ ቀና ከሚባልበት አካባቢ ነው ተወልጄ ያደኩት፡፡ ይህ የሚደረገው ደግሞ በቂ ሃብት ስላለ ሳይሆን “ወንድ ልጅ ተወልዶ ካልሆነ እንደ አባቱ እንዝርት አቅርቡለት ይፍተል እንደ እናቱ” የሚለው የንቀት አባባል በልጁ ላይ ሲያድግ እንዳይደርስበት ከወዲሁ ለማዘጋጀት ነው፡፡ እንዲያውም ልጅ በልጅ ተሸንፎና ተመትቶ እያለቀሰ ወደ ወላጆቹ ለእርዳታ ሲቀርብ አልቃሻ ልጅ አልወድም/የለኝም ተብሎ በጥፊ ወይም በአለንጋ ይደገማል፡፡ በለው! ትሸነፍና ወዮለህ! እንዳታሳፍረኝ! የሴት ልጅ! (ከወንድ ብቻ የተወለደ ያለ ይመስል)፣ ሊጥ አትሁን!፣ አስለቅስ እንጂ አታልቅስ!፤ አትበለጥ! ኩራት እራቱ! ከአረባባ ግልድም ሙልጭ ያለ ቂ . . . ይሻላል! ከማን አንሼ!. . . ወዘተ እየተባልንና እያልን ነው እኛ ኢትዮጵያውያን … [Read more...] about በክርስትና ላይ ጥናታዊ ምርምር ሲያደርግ የነበረው ሰው በራሱ ሕይወት ላይ ምርመራ ተደርጎበት እጁን ሰጠ!!!










