የተከበራችሁና የተወደዳችሁ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታዮች ሆይ፤ እትብታችሁ ስለተቀበረባት የምትወዷት ሀገራችሁ ኢትዮጵያም ሆነ ስለ ሃይማኖታችሁና ስለ ቤተ ክርስስቲያናችሁ ስታስቡ ሁሌም አስተዋይ፤ አርቆ አሳቢ፤ ብልህና ንቁ ሁኑ እንጂ ባማሩ ቃላት በመሳብም ሆነ ልብሰ ተክህኖና ግርማ ሞገስን በማየት የተንኮልና የሃሰት ሰለባ እንዳትሆኑ ተጠንቀቁ። “የበግ ለምድ ለብሰው ከሚመጡባችሁ፤ በውሥጣቸው ግን ነጣቂዎች፤ ተኩላዎች ከሆኑ ከሐሰተኞች ነብቢያት ተጠንቀቁ” ተብሏልና (የማቴ. ወ. ም. ፯ ቁጥር ፩፭) በለንደን ደብረ ጽዮን ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የተፈጠረውን ችግር ሁሉም የሚያውቀው ነው፤ መንስኤው ማን እና ምንድን ነው ከተባለ ደግሞ እውነተኛው መልስ ሥጋዊ ጥቅምን በማስቀደም ለሥልጣን፤ ለንዋይና ለዝና ያደሩ ጥቂት ካህናት የፈጠሩት ችግር መሆኑ የተረጋገጠ … [Read more...] about እውነትን ፈልጓት፤ ታገኟታላችሁም!
Left Column
ወ/ሮ ገነት ዘውዴ እውን ነገሩ እንዲያ ነውን?
ወ/ሮ ገነት ዘውዴ (ዮዲት ጉዲት) ይቅርታ መሳደቤ አይደለም ሰው የሚያውቃቸው በዚህ ስም በመሆኑና የሚኮሩበትም በመሆኑ እንጅ፡፡ እናም ወ/ሮ ገነት በቅርቡ በሸገር የኤፍ ኤም ሬዲዮ (ነጋሪተ- ወግ) “የሸገር እንግዳ” በተባለው ዝግጅት እንግዳ ሆነው አዘጋጇ ጋዜጠኛ ወ/ሮ መዓዛ ሦስት ቅዳሜ አዋይተዋቸው ነበር፡፡ በዚያ ጨዋታቸው ወ/ሮ ገነት ከተናገሩት ብዙው ነገር ከንክኖኝ ከጊዜ አንጻር ባይሆን በጥቂቶቹ ላይ ጥቂት ነገር ለማለት አስቤ እየጫጫርኩ እያለሁ እንዲያውም በወ/ሮዋ በሐሰት ስማቸው ከጠፋ ወገኖችና ጉዳዩ በቀጥታ ከሚመለከታቸው አንደኛው በጥሩ ምሁራዊ ተዋስኦ የተዋዛ ምላሽ ሰጥተው አሻሩልኝ፡፡ ይሁንና ወ/ሮዋ የተናገሩት አጉል ነገር በርካታ በመሆኑ ሁሉንም ለመዳሰስ ከጊዜና ከቦታ አንጻር የማይቻል በመሆኑ ዶክተሩ ለሁሉም አጉል ነገር መልስ ሳይሰጡ ቀሩ፡፡ እኔም እንማማርባቸው ዘንድ … [Read more...] about ወ/ሮ ገነት ዘውዴ እውን ነገሩ እንዲያ ነውን?
አገሬ!
የኔነት መለያ ~ የናት ያባቴ አገር ~ የተወለድኩባት፣ ስረ መሰረቴ ~ ቅርንጫፍ ሀረጌ ~ እትብቴ ያለባት፣ ተስፋዬ : ውጥነኔ ~ ህልሜ ሚፈታባት፣ ሀገሬ የኔ ናት~ ፣ ሀገሬ እርስቴ ናት~። አፈሩን ፈጭቼ ፣ ውሀ ተራጥቼ ፣ ዘልዬ ቦርቄ ~ ያደኩበት መንደር ፣ በሀሳብ በርሬ ~ በምናብ ከንፌ~ የማርፍባት ሰፈር ፣ የማንነቴ ምንጭ ~ መመኪያ አገሬ፣ አድባሬ አውጋሬ ፣ የዘወትር ህልሜ ~ የድካሜ እፎይታ ~ ማረፊያዬ ጎጆዬ፣ የትም የትም ዞሬ ~ ማሳረጊያ ቤቴ ~ አንገት ማስገቢያዬ፣ አገሬ እማማዬ ። ቀየሩት ይሉኛል ~ አፈረሱት አሉኝ ~ ለወጡት ባዱኛ፣ የኛ ሰፈርማ ፣ ሜዳው ሸንተሩ ~ መቦረቂያ መስኩ ~ አሁን የት አለና፣ ተሸጠ ለሌላ ~ የነሱን ኪስ ሞላ። ይህው በቀደም ለት ፣ ደውዬ ልጠይቅ ~ የወዳጅ ደህንነት፣ ስልኩ ጠርቶ ጠርቶ ~ "• • … [Read more...] about አገሬ!
ከሁለት ሳምንት እንግልት በኋላ ቴዲ አፍሮ ወደ አውሮፓ በረረ
ድምፃዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ከሁለት ሳምንት እንግልት በኋላ ዛሬ ምሽት ከቦሌ አውሮፕላን ማረፍያ ተነስቶ ወደ ኦስሎ ኖርዌይ ጉዞውን ጀምሯል። ኢትዮጵያዊው የፖፕ እና ሬጌ ሚዚቃ አቀንቃኝ በአውሮፓ ከተሞች የሙዚቃ ዝግጅቱን ለማድረግ ከአዲስ አበባ ተነስቶ የነበረው በወሩ መጀመርያ ላይ ነበር። ባለፈው ሃሙስ ዲሴምበር 4፣ 2014 ቦሌ አለም ዓቀፍ አውሮፕላን ጣብያ እንደደረሰ የደህንነት አካላት እንዳገቱት እና ፓስፖርቱንም እንደቀሙበት በልዩ ልዩ የዜና ምንጮች መዘገቡ ይታወሳል። አርቲስቱ ለምን ወደ ውጭ እንዳይወጣ እንደታገደና ፓስፖርቱም ለምን እንደተቀማ እስካሁን በይፋ የተነገረ ነገር የለም። አንዳንድ የዜና ምንጮች ጉዳዩን ቀረጥ ካለመክፈል ክስ ጋር አያይዘው አቅርበውታል። ይህ መላ ምት ፍጹም ስህተት ነው። ምክንያቱም ድምጻዊው በጥቅምት 3 ቀን 2007 ዓ.ም. በኢትዮጵያ … [Read more...] about ከሁለት ሳምንት እንግልት በኋላ ቴዲ አፍሮ ወደ አውሮፓ በረረ
የኦባንግ ጉዞና ለዲያስፖራው ፖለቲካ ያለው አስተዋጽኦ
በቅርቡ በዋሽንግተን ዲሲ ከተማ በአቶ ኦባንግ ሜቶ በተጠራው ስብስባ ላይ የመገኘት እድል አጋጥሞኝ ነበር:: በስብሰባው ላይ ከተለያዩ የአለም ክፍሎችና ከአሜሪካ ግዛቶች የተሰባሰቡ በርካታ ኢትዮጵያውያን ተገኝተዋል:: የስብሰባው መሪ ሀሳብ “ስለ እያንዳንዳችን ከመናገር እያንዳንዳችን እንነጋገር” የሚል ድፍረትን፣ ግልፅነትን፣ መከባበርን፣ መነጋገር መቻልን ሃላፊነት በተሞላበት ስሜት ይቀርቡ በነበሩት አስተያየቶች የሚያረጋግጡ ከመሆናቸውም በላይ የተለየዩ የፖለቲካ አመለካከት፣ እምነት እንዲሁም የተለየዩ ብሄረሰቦች ዉሁድ ኢትዮጵያውያን በአንድ ጠረጴዛ ዙርያ ተቀምጠው ያነሱዋቸው የነበሩት ሃሳቦች በጥንታዊት ኢትዮጵያና በአዲሲቱ ኢትዮጵያ የፖለቲካ ገመድ ጉተታ ግራ ለተጋቡ ጥሩ አስተማሪ መድረክ ነበር:: ኢትዮጵያ የምትባል ጥንታዊት ሃገርን የሲኦል መገለጫ አድርገው ለሚስሉዋት የህወሃት … [Read more...] about የኦባንግ ጉዞና ለዲያስፖራው ፖለቲካ ያለው አስተዋጽኦ
ግፍና አፈና ዐመጽን ይወልዳሉ!
የዐመጸኛ አፍ ጥልቅ ጉድጓድ ነው (መ. ምሳሌ ም. 22፣ ቁ. 14) ሰብአዊ መበቶችን በመጣስ፣ ግፍ በመፈጸምና አፈናን በማጠናከር እደሜ የሚሸምት የአገዛዝ ሥርዓት የእያንዳንዱን ሰው መንፈሳዊና አካላዉ ጥንካሬ የማዳከም፣ ቅስምን የመስበርና ፍርሃትን የማንገስ ከፍተኛ አቅም እንዳለው ሁሉ በብሶት የሚወለዱ፣ እምቢኝ ለግፈኞች፣ እምቢኝ ለአንባገነኖች፣ እምቢኝ ለነጻነቴ የሚሉ መንፈሰ ጠንካራ ጀግኖችንና ታጋዮችንም ይወልዳል:: የአለማችን ስመ ጥርና ዘመን የማይረሳቸው የነጻነት ታጋዮች እነ ማህተመ ጋንዲ፣ ማርቲን ሉተር ኪነግ፣ ማንዴላ፣ ኡንግ ሳን ሱ ኪ እና ሌሎችም ብዙዎች የፈለቁት በብሶት ከተሞላ፣ ጭቆና ካንገሸገሸውና በአፋኝ ሥርዓት ከታመቀ ማኅበረሰቡ ጉያ ነው:: አንድን ማኅበረሰብ በአፈሙዝ፣ በሕግና በገንዘብ ኃይል ጭፍሎቆና አፍኖ ማቆየት የሚቻለውም ለተወሰነ ጊዜ ብቻ መሆኑን … [Read more...] about ግፍና አፈና ዐመጽን ይወልዳሉ!
The Role of Civil Society Organization (CSOs) in the Upcoming Elections in Ethiopia
Fourth International Conference of Ethiopian Women in the Diaspora March 7, 2015 Washington DC, USA The Role of Civil Society Organization (CSOs) in the Upcoming Elections in Ethiopia Call for papers Civil society organizations (CSOs) flourished in Ethiopia from early 1990s to 2005 better than ever before. Some of these civil society organizations focused on service delivery, others on civil rights, gender equality and good governance, and still others on consciousness raising and … [Read more...] about The Role of Civil Society Organization (CSOs) in the Upcoming Elections in Ethiopia
አስገራሚው ትዕይንት “በተስፋዋ” የአረብ ምድር በሳውዲ!
* የሳውዲ መንግስት "ህገ ወጦችን" የማጽዳቱ ዘመቻ ቀጥሏል * ስፍር ቁጥር የሌላቸው ዜጎች ከሞት ጋር ተፋጠው እየተሰደዱ ነው * የሳውዲ መንግስት ማስጠንቀቂያና እርምጃ . . . የሳውዲ መንግስት የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውንና ህጉ በማይፈቅደው መንገድ የመኖሪያ ፈቃዳቸው ካለው ሙያ ውጭ የሚሰሩ የማናቸውንም ሀገር ዜጎች በመላ ሀገሪቱ ለማጽዳት የተደራጀ ዘመቻ ከተጀመረ ወር ደፍኗል። በየቀኑ በመንግስትና በግል መገናኛ ብዙሃን የሚለቀቁት የማስጠንቀቂያ መረጃዎች ከበድ ከበድ ያሉ ናቸው። ዛሬ ማለዳ "ህገ ወጦችን ጠራርገን እናስወጣለን" ያሉትን የሰራተኛ ሚኒስትር አድል ፈቂን ይዞ የወጣው አረብ ኒውስ ሚኒስትሩ ሃገራቸው ለህገ ወጥ ሰራተኞች ቦታ እንደሌላት በአጽንኦት መጠቆማቸውን ያስረዳል። የሰራተኛ ሚኒስትሩ በማከልም መንግስት ህገ ወጦችን እግር በእግር እየተከታተለ በመያዝ … [Read more...] about አስገራሚው ትዕይንት “በተስፋዋ” የአረብ ምድር በሳውዲ!
መድረክ የሰላማዊ ሰልፉን አካሄደ
የኢትዮጵያ ፌደራላዊ ዲሞክራሲያዊ አንድነት መድረክ (መድረክ) እሁድ ዕለት ያቀደውን ሰላማዊ ሠልፍ በ37 መፈክሮች በማጀብ አካሂዶዋል፡፡ አብዛኛዎቹ መፈክሮች ምርጫን፣ ምርጫ ቦርድን፣ የፖለቲካ ፓርቲዎች ሁኔታን፣ የአገሪቱን የኢኮኖሚ ሁኔታ፣ የኑሮ ውድነት፣ የመሠረታዊ አገልግሎቶች መቆራረጥና መንግሥትን ከሃይማኖት ጣልቃ ገብነት እንዲወጣ የሚጠይቁ ነበር፡፡ ከመፈክሮቹ መካከልም "ዲሞክራሲያዊ ሥርዓት በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ እንጂ በአስመሳይ ፕሮፖጋንዳ፣ በኃይልና በተፅዕኖ አይገነባም"፣ "የአገራችን ችግሮች በነፃና ፍትሐዊ ምርጫ በሚገለጽ የሕዝብ ውሳኔ እንጂ በኃይል ዕርምጃ አይፈቱም"፣ "ከምርጫ በፊት የምርጫ ውድድር ሜዳው የሚስተካከልበት ውይይትና ድርድር ይካሄድ"፣ ወዘተ የሚሉ መፈክሮች ተካተዋል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ሕዝቡ በ1ለ5 መረብ አፈናና ቁጥጥር ከሚካሄድ የምርጫ ድምፅ አሰጣጥ … [Read more...] about መድረክ የሰላማዊ ሰልፉን አካሄደ
የሀገራችን ፖለቲካና ስሉጣን (Activists) በቅሊንጦ!
ክፍል አንድ አስቀድሜ ጽሑፉ ትንሽ በመርዘሙ ይቅርታ እጠይቃለሁ፡፡ ከያዘው አንገብጋቢ ሀገራዊ ጉዳይ አንጻር ነውና ተረዱኝ ያውም ብዙ ነገር ትቸ ነው፡፡ ባይሆን ከሦስት እከፍለዋለሁ ቀጣዮችን ጽሑፎች ተከታትለው ይቀርቡላቹሀል፡፡ ጽሑፉ ብዙ ብዥታ ያጠራላቹሀልና አንብቡት፡፡ ለነገሩ የኔን ጽሑፎች ባሕርያት ለምዳቹህታልና በመርዘሙ እጅግም የምትማረሩ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ረዘመ ብላቹህ ሳታነቡት የምትቀሩ ብትኖሩ አመለጣቹህ! ማሳሰቢያ ጽሑፉን ስታነቡ አማራ ኦሮሞ ትግሬ ወዘተ. እያልኩ ስል አሉ ብለው ከሚያምኑ ሰዎች ጋር ነውና እያወራሁ ያለሁት ከነሱ ጋር በነሱ ቋንቋ ተናግሬ ለመግባባት ያህል እንጅ በዚህ ዘመን የብሔረሰቦች እሴቶች ቢኖሩም ብሔረሰቦቹ ግን አሉ ማለቴ አይደለምና በዚህ ግንዛቤ አንብቡልኝ፡፡ የተከሰስኩበትን ጉዳይ ታውቁታላቹህ ብየ አስባለሁ እሱም አምና መጋቢት ወር ላይ … [Read more...] about የሀገራችን ፖለቲካና ስሉጣን (Activists) በቅሊንጦ!










