* የናሚቢያው ፕሬዚዳንት የሞ ኢብራሂም ሽልማትን አሸነፉ የሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን በየዓመቱ በሚያወጣው የአፍሪካ መልካም አስተዳደር ጠቋሚ ኢትዮጵያ ከ52 አገሮች 32ኛ ወጣች፡፡ እ.ኤ.አ. የ2014 የሞ ኢብራሂም የመልካም አስተዳደር ጠቋሚ ከ30 ገለልተኛ የአፍሪካና ዓለም አቀፍ ታማኝ ምንጮች የተገኙ ከመቶ በላይ መለኪያዎችን በመገምገም ነው የአገሮች የመልካም አስተዳደር ደረጃን ማውጣቱን የገለጸው፡፡ ዋነኛ መለኪያዎቹ አራት ምሰሶዎች መሆናቸውን የሚገልጸው ሞ ኢብራሂም ፋውንዴሽን፣ እነዚህም ሕዝቦች ከመንግሥታቸው የሚጠብቋቸውና መንግሥትም ማቅረብ የሚጠበቅበት ግዴታዎችን የሚዳስስ ነው፡፡ እነዚህ መሠረታዊ ምሰሶዎች የመሠረተ ልማት ዝርጋታ፣ የመናገር ነፃነት፣ የንፅህናና የንብረት ባለቤትነት መብቶች ጥበቃን የሚዳስሱ ናቸው፡፡ በዚህም መሠረት ሞሪሺየስ፣ ኬፕ ቨርዴና ቦትስዋና ከአንድ እስከ … [Read more...] about በመልካም አስተዳደር ከአፍሪካ 52 አገራት ኢትዮጵያ 32ኛ!
Left Column
አስቂኙ የአቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ!
የኢሳት ራዲዮና ቴሌቪዥን (ነጋሪተ ወግና ምርዓየ ኩነት) ጋዜጠኞች ከሕዝባዊ ግንባር መሪ አቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ጋር ያደረጉትን ቃለ መጠይቅ ተከታተልነው፡፡ ያው አስቀድሜ እንደገመትኩት በአሮጌው ድሪቶ ላይ አሮጌ ጨርቅ ድረታና እብለት ክህደት እንጅ የነበረውን አሮጌውንና ያላዋጣውን በመተው በአዲስና በተመከረ በተማረ ልብ አዲስ ሐሳብ አዲስ መንገድ ለመቀየስ አልተፈለገም፡፡ የሚጠበቀውና አስፈላጊው ግን ይሄኛው ነበር፡፡ ለነገሩ ከአንባገነን ሥርዓት ባለሥልጣናት ይሄ የሚጠበቅ አይደለም እንደነዚህ ዓይነት ሰዎች እንኳን በአንድ ሰው ዕድሜ ሽህ ዓመታት የመኖር ዕድል ቢሰጣቸው እንኳን እስከ መጨረሻዋ ደቂቃ ድረስ ሱሪያቸውን በአንገት ለማጥለቅ እንደታገሉ ያልፋሉ እንጅ አይ ሐሳቤ መንገዴ ይሄንን ያህል ዘመን ብታገልም ሊሠራ አልቻለም፡፡ ሊሠራ ያልቻለበትም የራሱ ምክንያት ችግር ስላለበት ሳይሆን … [Read more...] about አስቂኙ የአቶ ኢሳይያስ አፈወርቂ ቃለ መጠይቅ!
የረዳት አብራሪ ሐይለመድህን አበራ ጉዳይና የአንድ አመት ጉዞው ባጭሩ
እለተ ሰኞ ፌብሯሪ 17 ቀን 2014 ዓ/ም ማለዳ አንድ ንብረቱ የኢትዮጵያ አየር መንገድ የሆነና በበረራ ቁጥር ET 702 የተመዘገበ ቦይንግ 767 የመንገደኞች ማመላለሻ አውሮፕላን በጣሊያን በኩል አድርጎ ወደ ስዊዘርላንድ የአየር ክልል ይገባል። የስዊዝ የአየር ክልል ጠባቂዎችም በጧት የመጣባቸውን ጥቁር እንግዳ ማንህ ወዴት ነህ ማለት። የአውሮፕላኑን የበረራ ሂደት ሙሉ በሙሉ በብቸኝነት የተቆጣጠረው ረዳት አብራሪ ሃይለመድህን አበራም ቆፍጠን ብሎ አኔ ነኝ ! ማለት። አንተ ማን? ምነው ምን ፈልገህ ነው ወደ አየር ክልላችን የገባኸው? የአየር ክልል ተቆጣጣሪዎቹ ቀጣይ ጥያቄ ነበር ። የበርካታ ወገኖቹን የብሶትና የግፍ መልዕክት ይዞ በስዊዝ አየር ላይ የሚያንዣብበው ሃይለመድህንም "ለጊዜው የምፈልገው የስዊዝ መንግስት የፖለቲካ ጥገኝነት እንዲሰጠኝ ፣ ለኢትዮጵያ … [Read more...] about የረዳት አብራሪ ሐይለመድህን አበራ ጉዳይና የአንድ አመት ጉዞው ባጭሩ
ወሬ ሲነግሩህ ሃሳብ ጨምርበት
ምኒልክ ጥቁረቱን ክዶ ነበር የሚል ቀደዳ በፌስቡክ ሲዞር ኣየሁ ልበል? ትልልቅ ቅጥፈቶች ጀርባ ኣንድ ትንሽ መነሻ ይኖራል፡፡ መነሻውን እንመርምር እስቲ፡፡ ያድዋ ድል ማግስት የምኒልክ ዝና የጠራቸው የውጭ ኣገር ሰዎች ኢትዮጵያን መጎብኘት ጀምረው ነበር፡፡ ከኒህ እንግዶች ኣንዱ የሄቲው ታጋይ ጋዜጠኛ ቤኒቶ ሲልቪያን ነው፡፡ ሲልቪያንና ምኒልክ ያደረጉትን ጭውውት ስኪነር የተባለ ኣሜሪካዊ ዘግቦታል፡፡ በጭውውታቸው መሀል ምኒልክ ለሄቲው ሰውየ I am not a Negro I am a Caucasian ማለቱን ስኪነር ዘግቧል፡፡ ምኒልክ ኔግሮ ኣይደለሁም ብለው ከሆነ ደግ ኣደረጉ ከማለት ውጭ የምለው የለኝም፡፡ ምኒልክ ጥቁር እንጂ ኔግሮ ኣይደለም።ኔግሮ የውርደት ስም ሲሆን ጥቁር የክብር ስም ነው፡፡ ኮኬሽያን የሚለው ቃል ግን ያስተርጓሚ ስተት መሆን ኣለበት፡፡በምኒልክ ዘመን ሰዎች ዘርን … [Read more...] about ወሬ ሲነግሩህ ሃሳብ ጨምርበት
Larger-than-life characters, intrigue part of history behind Battle of Adwa
“(ከአድዋ ሌላ) አፍሪካውያን ጦርነት ያሸነፉባቸው ሌሎች በማስረጃ የሚጠቀሱ አሉ፡፡ የእንግሊዝን ጦር ያሸነፈው ዙሉ ዓይነተኛ ምሳሌ በማድረግ መጥቀስ ይቻላል፤ ይህም በየጊዜው በተሰራ ፊልም ታዋቂ ለመሆን ችሏል፡፡ ሆኖም ድሉ ጊዜያዊ ነው፡፡ ከዚያ በኋላ ዙሉዎች ተሸንፈዋል፡፡ የኢትዮጵያ ግን ከዚህ ለየት ያለ ነው፤ (ምኒልክ ጣልያንን አድዋ ላይ ካሸነፉ በኋላ) በንጉሠነገሥቱ የግዛት ዘመን ያልተሸነፈች ብቸኛ አገር ናት” ሬይሞንድ ጆናስ “The Battle of Adwa - 1896” ደራሲ፡፡ Raymond Jonas went to the Boston Museum of Fine Arts one day when he was in town for a conference, aiming to see an exhibit of European art. But on the way out, he stumbled onto a … [Read more...] about Larger-than-life characters, intrigue part of history behind Battle of Adwa
ኢሳያስ አፈወርቂን በጨረፍታ
"አንድም ቀን ስቀን አናውቅም!" አሉ ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማርያም። ይህን በሚሉ ጊዜ እፊታቸው ላይ ፈገግታ ይታይ ነበር - ምሬቱ እንዳለ ሆኖ። ኢሳያስ አፈወርቂ ሲስቁ አይተናቸው አናውቅም። ግን ኮስተር ብለው የሚናገሩት ነገር እኛኑ አያሳቀን ነው። "ካሳ ይገባናል! ካሳ ስጡን" ሲሉ አሳቁን። ቀጠል አድርገውም "ምጽዋና አሰብን ወያኔ ሳይሆን የኢትዮጵያ ህዝብ እንዲጠቀምበት ፈልገው" እንደነበር ተናግረው አሳቁን። "...የሰራነው ጥፋት ስለሌለ የሚጸጥተን ነገር የለም።" አሉ እጃቸውን እንደ ጲላጦስ እያጠቡ። ከዚህ ቀደም ለስዊድኑ ጋዜጠኛ የአስመራው የፖለቲካ ስርዓት ስዊድን ካለው ስርዓት የተሻለ እንደሆነ አስረግጠው ነገሩት። ስለ ብሄራዊ ምርጫ ለጠየቀቻቸው የአልጃዚራዋ ጋዜጠኛም "ምርጫ ምንድነው?" ብለዋት ነበር። ከዚህ በላይ ምን የሚያስቅ ነገር አለ? የፈለጉት ካሳ ግን ምን ይሆን? … [Read more...] about ኢሳያስ አፈወርቂን በጨረፍታ
አድዋ!
ዋ! አድዋ ፤ ያ ሑዳዴ መድፍና ፈንጅ ፤ በጎራዴ ባሕር ተሻግሮ ፤ የሐበሻን ምድር ቅኝ ሊገዛ ፤ የማን ደፋር! አንች አድዋ ፤ የበኩር ልጅ ላንቺ ውልደት ፤ ስንቱ ሲፈጅ ተጸንሰሽ ፤ ከውጫሌ ለደም መሬት ፤ ለአሞሌ እርግዝናሽ ፤ ዘጠኝ ወሩ ዓመታትን ፤ ማስቆጠሩ ክፉውን ቀን ፤ ይዞ አሳሩ ከብቱ እረግፎ ፤ ባገር ምድሩ ሰው ሁሉ አልቆ ፤ በችጋሩ በፋሽስት ሸር ፤ በእኩይ ግብሩ ከብት የሚፈጅ ፤ ደዌ ረጭቶ በምን ታርሶ ፣ በምን ለምቶ የገበሬው ፤ ሀብት ጠፍቶ አከርካሪው ፤ ተመትቶ የሚቀመስ ፤ እህል ታጥቶ ረሀቡ ፤ ሕዝቡን በልቶ ምኑ ተብሎ ፤ ስንቱን ነግሮ የግፍ ግፉ ፤ ተዘርዝሮ ዝም ይሻላል ፤ ምን ተቆጥሮ በክፉው ቀን ፤ ራብ ደክሞ ያለቀ ሕዝብ ፤ በአዋጅ ተሞ በዚያ … [Read more...] about አድዋ!
የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር የሕይወት ጉዞ
መግቢያ፤ የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ ከተመሠረተ ጀምሮ የተለያዩ ስሞችን፣ መርኆዎችን፣ ተግባራትን፣ ባጠቃላይም ማንነትን ተከናንቧል። ይህ ማለት፤ በሂደቱ እየተቀያየረ የሄደ ድርጅት ነው። ሲነሳ፤ አሁን የያዘው እምነት፣ ግብና አሠራር አልነበረውም። እግረ መንገዱን ለዕለቱ የሚረዳውን የፖለቲካ አቋም እየውለበለበ ተጓዘ እንጂ፤ ዘላቂ የሆነ የፖለቲካ አቋም አልነበረውም። ይህ የሚነግረን፤ ይህ ድርጅት፤ አጋጣሚዎችን ተጠቃሚነትን፣ ሥልጣንን፣ ቂምና በቀልን፣ የሕልውናው መሠረቶች አድርጎ የተጓዘ እንጂ፤ መርኆ ወይንም ሕዝባዊ ግንዛቤ ያላነገበ ድርጅት መሆኑን ነው። ይህን ቡድን የሚያሽከረክረው የማርክሲስት ሌኒኒስት ሊግ ኦፍ ትግራይ ፍጹም ማርክሲስት አይደለም። የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር፤ ትግሬዎችን ነፃ ሊያወጣ የተነሳ ድርጅት አልነበረም። በርግጥ ስሙ፤ ከትግራይ ብሔራዊ ድርጅት፤ በብዙ … [Read more...] about የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር የሕይወት ጉዞ
“መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ”
በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ማዕከላዊ ፌደራል ወንጀል ምርመራ የሚገኙት የሦስት ተቃዋሚ ፓርቲዎች የቀጠና/ዞን አመራሮች ለ16 ተከታታይ ቀናት በጨለማ ክፍል መታሰራቸውን ለፍርድ ቤት አስታወቁ፡፡ የካቲት 17 ቀን 2007 ዓ.ም በፌደራሉ የመጀመሪያ ፍርድ ቤት አራዳ ምድብ ችሎት የቀረቡት የሰማያዊ (የፓርቲው የጎንደር አደራጅ አቶ አግባው ሰጠኝ)፣ የአንድነት እና መኢአድ የዞን አመራሮች "መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ" እያሉ እንደሚደበድቧቸውና በጨለማ ክፍል እንዳሰሯቸው ተናግረዋል፡፡ ፖሊስ አሁንም መረጃየን ሰብስቤ አልጨረስኩም በሚል ተጨማሪ 8 ቀናት ጠይቆ ተፈቅዶለታል፡፡ ተጠርጣዎቹ በማዕከላዊ እየደረሰባቸው የሚገኘውን ሰቆቃ አስመልክተው ለፍርድ ቤት አቤት ማለታቸውን ተከትሎ ፍርድ ቤቱ ፖሊስ የቀረበበትን አቤቱታ እንዲያስተካክል ትዕዛዝ ሰጥቷል፡፡ ተጠርጣሪዎቹ በጎንደርና … [Read more...] about “መረጃ አውጡ፣ የደበቃችሁትን ሁሉ ተናገሩ”
“አሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን (አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን)”
በተለያየ ጊዜ በተለያየ የክህደት አስተምህሮ በመሰናከል በመውደቅ ከዚህች ሐዋርያዊት አንዲት ቤተክርስቲያ እየተለዩ በኑፋቄያዊ አስተምህሮ ጸንተው በመቀጠል ለዚህች አንዲት ሃይማኖት አንዲት ቤተክርስቲያን ጠላቶች የሆኑ ዲያብሎስን የሚያገለግሉ ከ40 ሽህ በላይ ይቆጠራሉ፡፡ ሃይማኖት ነንም ይላሉ፡፡ ክርስቶስ በወንጌሉ ሐዋርያትም በመልእክቶቻቸው እንደተናገሩት ግን ከአንዲቷ በስተቀር ይሄ ሁሉ ሃይማኖት ነኝ ባይ ዝግንትል ሐሰተኛና ዲያብሎሳዊ የክህደትና የጥፋት መንገዶች ናቸው፡፡ የዘመኑ ፍጻሜ ሲቃረብ ብዙዎች ሐሰተኞች መምህራን በየ እልፍኙ የሚሰብኩላቸው ሐሰተኞች ኢየሱሶች ሐሰተኞች ክርስቶሶች ይመጡ ዘንድ እንዳላቸውና ከእነሱም እንድንጠበቅ አስጠንቅቆናል፡፡ ማቴ. 24፤1-28 “አንድ ጌታ አንድ ሃይማኖት አንዲት ጥምቀት” ኤፌ. 4፤5 “መንፈስ ግን በግልጥ በኋለኞቹ ዘመናት አንዳንዶች የሚያስቱ … [Read more...] about “አሐቲ ቅድስት ቤተክርስቲያን (አንዲት ቅድስት ቤተክርስቲያን)”










