ሰሞኑን የፈረንጆቹን አዲስ ዓመት ምክንያት በማድረግ ይመስላል ወያኔ/ኢሕአዴግ ለሀገር ውስጥ ጋዜጠኞች ጋዜጣዊ መግለጫ በጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ አማካኝነት ሰጥቷል። ዶላር እስካስገኘ ድረስ ሕፃናትንና ወጣት እህቶቻችንን በቁማቸው እየቸበቸበ ያለው ወያኔ ፀጉር መላጨት እንዳይጀምር ጠንቀቅ ነው። “አለና! ምንም አልሆንም! ምን ታመጣላችሁ! አሁንም ከማንም በላይ ነን” የሚለው የሰሞኑ የጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ጋዜጣዊ መግለጫ በሚገባ ለተረዳው ከሥልጣኑ አንፃር የወያኔን አቋምና የሀገሪቷን ቀጣይ ራዕይ መላሽ ነው። (ሙሉውን መግለጫ ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ) … [Read more...] about አይደለም እንዴ? ዋሸን እንዴ?
Left Column
የዛ ሰውዬ ድምጽ . . .
ፊቱ አሸቦ መስሎ፣ እንደደነገጠ፣ ተጎልጉሎ ወጥቶ፣ ዓይኑ እንደፈጠጠ፣ ባንኮኒው ጋ ሄዶ፣ ቢራውን ጨበጠ። የሆነውን እንጃ! ሁኔታው ያስፈራል፣ እንባው በጉንጩ ላይ፣ አቋርጦ ይፈሳል አልቅሶ ሲበቃው፣ ውጪ እየሰለለ፤ ያየውን በውስጡ፣ እያሰላሰለ፣ ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ። ወደ ተናጋሪው፣ አፍጠን እያየን፤ እንደልማዳችን፣ ዝም ተባባልን። ሰውዬው ቀጠለ፣ ገድለው ሲጥሏቸው፣ በዓይኖቼ አየሁ አለ! ዘለው ያልጠገቡ፣ እህል የተራቡ፣ አገር የተቀሙ፣ ፍትሕ የተጠሙ፣ አንድ ፍሬ ናቸው! ገና እንዳገኟቸው፣ ከበው ይዘዋቸው፣ መሣሪያ አስጠግተው፣ ወደ ግንባራቸው፣ ጭንቅላታቸውን ... ፈረካከሷቸው። እያለ ሲናገር፣ ሰውዬው ሲቆጣ፣ ሲያለቅስ ሲያማርር፣ እኔም ልክ እንደሱው፣ በዓይኖቹ ገብቼ፣ አንገቴን አቅፌ፣ በሁለት እጆቼ፣ ጉልበቴ እየራደ፣ ነፍሴ … [Read more...] about የዛ ሰውዬ ድምጽ . . .
ለጀግናው አትሌት ስንብት!
. . . በዚያ ቀውጢ ጊዜ - በዚያ ቀውጢ ዘመን፣ ከአገር በራቀበት - የደስታ ሰመመን፤ ያገር ፍቅር ስሜት - መገለጫ ፈርጦች፣ ብቸኛው አማራጭ - የደስታችን ምንጮች፣ ነበሩን! ነበሩ! “አረንጓዴ ጎርፎች”. . .፤ እንዲህ እንደዛሬው - ሳይዘምን ዘመኑ፣ ያለም መገናኛ - ሳይራቀቅ ኪኑ፣ ዩ ቲዩብ፣ ኢንተርኔት፣ ስማርት ፎን..ሳይኖር፣ ዜና መቀበያው - ራድዮናችን ነበር፤ “. . . ክቡራትና ክቡራን ውድ አድማጮቻችን..”፣ የኦሎምፒክ ውጤት፣ ልክ እንደደረሰን፣ እናስደምጣለን...”፤ በለሆሳስ ሙዚቃ መሳሪያ ቅንብር መሻገሪያ ዜማ፣ ከተራራ ጫፍ ላይ፣ ወይ ከሰማየ-ሰማያት ከሩቅ እሚሰማ፣ “የኛ ነው ድሉ-ድሉ፣ የኛ ነው ድሉ-ድሉ፣ በርቱና ታገሉ..”፤ አገር ትንፋሽ አጥሮት - ጸጥ-ረጭ ብሎ፣ ዐይኖቹን ጎልጉሎ - ራድዮን ላይ … [Read more...] about ለጀግናው አትሌት ስንብት!
The TPLF Hired a Rubbish Writer to Defend it against Prof. Al Mariam
With an open mind, I read an article titled “TEACHING ALMARIAIM HOW TO WRITE” on the Aiga Forum website, the Tigrayan People’s Liberation Front’s (TPLF’s) mouthpiece. The article was written by Yenieta A, who claimed that Ethiopian political writers don’t know how to write. To make his point, he used Professor Al Mariam’s commentary titled “Ethiopia: Cry! Cry Freedom the Beloved Country!” as his example because he thinks Al Mariam is the worst kind of political writer. To help him to improve … [Read more...] about The TPLF Hired a Rubbish Writer to Defend it against Prof. Al Mariam
“ሐሩርም ይሁን በረዶ እኔ ከማሸነፍ የሚገታኝ አንዳች ኃይል የለም” – “Yifter the Shifter”!
ከሠላሳ ሰባት ዓመት በፊት የተካሄደው የሞስኮ ኦሊምፒክ ሲነሣ ቀድሞ የሚመጣው የሚወሳው ረዥም ርቀት ሯጩ ምሩፅ ይፍጠር ነው፡፡ የድል ቁርጠኝነት የተሞላበት አሯሯጡ የመላው ዓለምን ምናብ ሰንጎ መያዙ አይረሳም፡፡ በሞስኮ ኦሊምፒክ በሁለቱ ርቀቶች በ5,000 ሜተርና በ10,000 ሜትር ለተቀናቃኞቹ ዕድል ሳይሰጥ ተፈትልኮ የሮጠበትና ያሸነፈበት መንገድ ‹‹ይፍጠር ዘ ሺፍተር›› (ማርሽ ለዋጩ ምሩፅ - አካለ ማርሹ ምሩፅ) የተባለበትን ዳግም ያረጋገጠበት ነበር፡፡ በሞስኮ ድሉ ከተመሰጡና አርአያ ከሆነላቸው መካከል በወቅቱ የሰባት ዓመት ልጅ የነበረው ኃይሌ ገብረ ሥላሴ ውድድሩን በትራንዚተር ሬዲዮ ጆሮውን ደቅኖ ሲከታተል አንድ ቀን የርሱን ዱካ እንደሚከተል አልሞ ነበር፡፡ ኢትዮጵያን የኦሊምፒክ ብርሃን ከዘጠና ሦስት ዓመት በፊት የዳሰሰው በፓሪስ ኦሊምፒክ አልጋ ወራሽ ተፈሪ መኰንንና የክብር … [Read more...] about “ሐሩርም ይሁን በረዶ እኔ ከማሸነፍ የሚገታኝ አንዳች ኃይል የለም” – “Yifter the Shifter”!
ለማንነታችን መከታ ያልሆነን፣ ለመጠቃታችን ምክንያት እየሆነ ነው!
ዛሬ በኢትዮጵያ ምድር ዘረኛው የትግሬ ወያኔ አገዛዝ በሕዝባችን ላይ፣ በተለይም በዐማራው ነገድ ላይ የሚፈጽመው የዘር ማጥፋትና የዘር ማጽዳት ወንጀል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መንገድ በ«አርበኞች ግንቦት 7» እያመካኘ ነው። ለዚህም ምክንያት የሆነው አርበኞች ግንቦት ሰባት፣ በሚቆጣጠረው የብዙኃን መገናኛ ያላደረገውን አደረኩ፣ ያላዘመተውን ወታደር አዘመትኩ፣ «የክተት አዋጁ ፊሽካ ተነፋ»፣ በሁሉም ሕዝባዊ እንቢተኝነት እንቅስቃሴዎች እኔ አለሁበት፣ የምመራው እኔ ነኝ፣ የሚለው ወሬ ቀድሞ መነዛቱ ነው። ወሬው በትንሽ ተግባር ቢደገፍ ኖሮ ባልከፋ። ክፋቱ ምንም ዓይነት ተግባራዊ እንቅስቃሴ ሳይጀምር፣ ኤርትራ በረሃ ከትሟል የሚባለው ፋኖ፣ የተከዜን ወንዝ ሳይሻገር፣ የወያኔ አገዛዝ አንገሽግሾት ባመቸውና በመሰለው መንገድ ጥይት የተኮሰውን ሁሉ የእኔ ነው ማለቱ፣ «ለወያኔ ሊበሏት ያሰቧትን … [Read more...] about ለማንነታችን መከታ ያልሆነን፣ ለመጠቃታችን ምክንያት እየሆነ ነው!
“እውነተኛው የዘር ምንጭ?”
ዶ/ር ፍቅሬ በ “የኦሮሞ እና የአማራ እውነተኛው የዘር ምንጭ” መጽሐፉ አዲስ እሳት ለኵሶልናል። እሳቱ ባጭሩ፣ ሁሉም የሚስማማውን ታሪክ ይጻፍ የሚል ነው። ቍጥራቸውና ማንነታቸው ያልታወቀ አወዳሾቹ፣ “ሐቀኛ የኦሮሞ ልጅ የኢትዮጵያ ልጅ” “የመከራ ቀን ደራሽ” “የመከራ ቀን ልጅ” “የታሪክና የፍቅር አባት” “የኢትዮጵያ መድን” “የህዝብ እርቅ አባት” “አስታራቂ” “የኢትዮጵያ ቤዛ” “ነብይ” ብለውታል። ሙገሳው የለመደበት “ካብ ካብ፣ ጣል ጣል” ባህላችን ነው ብለን እንለፈው። አንዳንድ “ምሑራን” ጭሱ አፍኗቸው መስኮት ለመክፈት ይሯሯጣሉ። አንዳንዶች የጎሳ ክልል መደብዘዝ የሥልጣን ወንበር እንዳያሳጣቸው ሠግተው። ሌሎች በአገር ወዳድነት። አንዳንዶችም ያልተፈጠረ ንጹሕ ጎሳ በስውር የሚያውጁ ናቸው። ከኢትዮጵያ መንደር ውጭ ማሰብ የተሳናቸው፤ በምድር ዙሪያ የሕዝቦች አሠፋፈር፣ መፍለስና … [Read more...] about “እውነተኛው የዘር ምንጭ?”
STANDING TOGETHER AS ONE
This past year of 2016 may have been the worst year in recent history for Ethiopians within the country. Many families will be facing Christmas or the New Year without the presence of a beloved family member at their side. The reasons have been many and most point to the actions or lack of actions taken by the TPLF/EPRDF. Too many have been taken from this earth early due to the deadly violence perpetrated against them by TPLF/EPRDF security forces. The ruling regime used deadly force against … [Read more...] about STANDING TOGETHER AS ONE
ዘ-ሃበሻ! እባክሽ “ሙድ” አትያዢብን!
አንድ ሰው በማህበራዊ መገናኛ ብዙሃን በሚናገራቸው/በሚጽፋቸው ጽሁፎች አስተሳሰቡ እና ብቃቱ ይገመታል፤ የሚመራውን ድርጅት/ተቋም ብቃትም ይናገራል። እንደ ግለ-ሰብ ስለ ራስ፣ ስለ ቤተሰብ እና ስለ ጓደኛ የሚናገራቸው ወይም የሚጽፋቸው ጽሁፎች ከሙያዊ ብቃት እና ችሎታ አኳያ ብዙም የሚያስከትለው ተጽዕኖ አይኖርም። ጋዜጠኛ ነኝ ያለ ሁሉ ጋዜጠኛ እንዳልሆነ ግምት ውስጥ በማስገባት፣ የጋዜጣ አዘጋጅ ስትሆን፣ ከዚያም ብዙ ተከታዩች ሲኖሩህ እና ስለ አገር እና የማህበራዊ ጉዳይ የምትጽፋቸው ሲሆን ግን ቢያንስ ከጋዜጠኛነት ሙያ፣ ከጭብጥም ሆነ ከቋንቋ አጠቃቀም አኳያ ይሄን ያህል መወረድ በ“ሙደኞች” (“ሙድ” የዘ-ሃበሻ የራሷ አማርኛ ነው) ቋንቋ ሙያዊ “ቅሽምና” ነው። ስለዚህ እኛም ዘ-ሃበሻን በ“ሙድ” ልንተች ነው። “ወያኔ በየቀኑ ህዝባችንን እየገደለና እያሰረ ሙድ ሲይዝብን...” እንዳለችው … [Read more...] about ዘ-ሃበሻ! እባክሽ “ሙድ” አትያዢብን!
የአጋንንት ፖለቲካ – ውጣ!!
ልብ ማለት ያቃተን ለምን ይሆን? የማንሰለጥነውስ ለምንድን ነው? በፖለቲካ ትግል ውስጥ ዕድሜ ገፍተን የማንበስለው እስከመቼ ነው? አድሮ ቃሪያ፣ አድሮ ጥሬ ... እንዲሉ በጫጫታ ትውልድን የምናሰቃየው ስለ ምንድን ነው? ብዙ ጥያቄዎችን ማንሳት ይቻላል። ይህ በድህነትና በችጋር የሚቃጠለው ህዝብስ ማን ያስብለት? ማን ይድረስለት? በእነማን ብርሃን ይመልከት? ማን ከጨለማ እንዲወጣ ይምራው? ሩብ ምዕተ ዓመት እንደተባላን እንቀጥል? ያሳዝናል? ያስለቅሳል፣ እጅግ ያንገበግባል ... ንስሃ የማያውቅ የአጋንንት ፖለቲካ ይሏል እኛ ነን!! ችግሩ አንድ ወገን ዘንድ ብቻ አይደለም። ችግሩ ሁሉም ዘንድ በውጭም በውስጥም ነው። በውስጥ የተመቸ የመፎካከሪያ ሜዳ የለም። እያደር ይሻላል ሲባል ጭራሹኑ ህወሃት/ኢህአዴግ ሌሎችን “አያገባችሁም” አለና አረፈው። ይህ አልበቃ ብሎ ምክንያት እየተፈለገ ማሳደድና … [Read more...] about የአጋንንት ፖለቲካ – ውጣ!!










