• Skip to primary navigation
  • Skip to content
  • Skip to primary sidebar

Goolgule

Ethiopian News

  • ስለ እኛ/about
  • አስፈንጣሪዎች/links
  • ቤተ መዝገብ/archives
  • አድራሻችን/contact
Header Banner Image
  • Home
    ዋና ገጽ
  • Editorials
    ርዕሰ አንቀጽ
  • News
    ዜና
  • Socio-Political
    ማኅበራዊ-ሽከታ
  • Religion
    ሃይማኖታዊ
  • Interviews
    እናውጋ
  • Law
    የሕግ ያለህ
  • Opinions
    የኔ ሃሳብ
  • Literature
    ጽፈኪን
    • Who is this person
      እኚህ ሰው ማናቸው?
  • Donate
    ለባለድርሻዎች

Left Column

የዐድዋ ድል “የታሪክ አጋጣሚ” ወይስ በዕቅድ የተከወነ?

February 24, 2017 06:27 am by Editor 3 Comments

የዐድዋ ድል “የታሪክ አጋጣሚ” ወይስ በዕቅድ የተከወነ?

ሰሞኑን የዐድዋ ድል መታሰቢያ 121ኛ ዐመት የሚዘከርበት ወቅት ነው። በፍቃዱ ዘ. ኀይሉ የተሰኘ ከታቢ (blogger) "Bilisummaa adda-ዋ!" በተሰኘ እና በድረ ገጽ እና በፌስ ቡክ በተሰራጨ አነጋጋሪ ጽሑፉ ስለ ዐድዋ ድል እና ስለ ምኒልክ አመራር ብዙ ቢልም በተለይ ኹለቱ ትርክቶች የሚጐረባብጡ፤ ፈራቸውን የሳቱ ኾነው ስላገኘኹዋቸው እነሱ ላይ ሀሳቤን ማካፈል ወደድኩ። ኹለቱ የበፍቃዱ ዘኀይሉ “Bilisummaa adda-ዋ!” ትርክቶች፤ 1) የዐድዋ ድል በታሪክ አጋጣሚ የተከሰተ ነው እና 2) ዐድዋ የጨቋኝ ምርጫ የተሰኙት ናቸው። ኹለተኛው ትርክት ቃል በቃል ባይኾንም የዐድዋ ጦርነት የኢትዮጵያ ሕዝብ ከነጭ ጨቋኝ የጥቁር ጨቋኝ መርጦ የተዋጋበት እንጂ የዐድዋ ጦርነት ሕዝቡ ለነጻነት የተዋጋበት ጦርነት አይደለም ነው። በትክክል ተረድቼው ከኾነ በፍቃዱ መነሻ ሀሳቡን ያገኘው … [Read more...] about የዐድዋ ድል “የታሪክ አጋጣሚ” ወይስ በዕቅድ የተከወነ?

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

ለማሳጠር መስራት፤ ስለመርዘምም ማሰብ

February 24, 2017 12:04 am by Editor Leave a Comment

ለማሳጠር መስራት፤ ስለመርዘምም ማሰብ

በፌብርዋሪ 11 እና 12, 2017 በሁለቱ ቀናት ውስጥ በአምስቱም ክፍለ ዓለማት በሚገኙ ከአርባ በላይ በሚሆኑ ከተሞች ለአርበኞች ግንቦት 7 የገንዘብ ድጋፍ ለማሰባሰብ የተደረጉ በዓላዊ ዘመቻዎች መካሄዳቸውን የበረታ በየአካባቢ በተደረጉት ዝግጅቶች ላይ በመገኘት ለዓይን ምስክርነት ሲበቃ የተቀረው ኢትዮጵያዊ ደግሞ በሚዲያዎች የታደመው ይመስለኛል። በዝግጅቱ ላይ ከድጋፍ ማሰባሰቡ በተጓዳኝ  ለአርበኞች ግንቦት 7 ሊቀመንበር ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ በስካይፔ ከየአካባቢው ጥያቄዎች እየቀረቡ መልስ ሲሰጥም ስለነበር፤ በዚህ አጋጣሚ ከቀረቡት ልዩ ልዩ ጥያቀዌዎች ውስጥ አንድ ሃሳቤን  የሰረቀው ጥያቄ "የትጥቅ ትግሉ በተጠበቀው ፍጥነት አልሄደም" የሚለው ነበር። ጥያቄው ማንም የባርነት ቀንበር የከበደው ሰብአዊ ፍጡር ሁሉ ሊያነሳው ጥያቄ እንደሆነ የሚያጠያይቅ አይመስለኝም። የመከራና የጭነቀት … [Read more...] about ለማሳጠር መስራት፤ ስለመርዘምም ማሰብ

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

ፕሮፌሠር ፍቅሬን ለቀቅ ቧልትህን ጠበቅ

February 23, 2017 04:17 am by Editor 7 Comments

ፕሮፌሠር ፍቅሬን ለቀቅ ቧልትህን ጠበቅ

ሰሞኑን በፕሮፌሠር ፍቅሬ ስራዎች ለማሾፍ እና የእርሳቸውን ክብር ለማውረድ በጅምላ እየተካሄደ የሚገኝ የስም ማጥፋት ስራ እየተመለከትኩኝ ነው አንዳንዶቹ ባለማወቅ እና ከብስለት ማነስ የሚያደርጉት መሆኑን ባውቅም የተወሰኑት ግን ሆን ብለው የሚፈፅሙት ተግባር መሆኑን ለማወቅ ችያለው፡፡ በፕሮፌሰሩ ላይ እየተካሄደ የሚገኘው የማንቋሸሽ ተግባር ከየት እንደመነጨ ለምን እንደሚካሄድና እነማን እንደሚፈፅሙት መመልከቱ መልካም ይመስለኛል፡፡ ፕሮፌሠር ፍቅሬ በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ2008 ዓ.ም ለንባብ ያበቁት የኦሮሞና የአማራ ህዝብ ትክክለኛ የዘር ምንጭ የተሰኘው መፅሐፍ ለገበያ ከዋለ በኋላ በኢትዮጵያውያን ዘንድ እጅግ ተፈላጊ መፅሐፍ በመሆን መነበብ የቻለ ትልቅ መፅሐፍ ነው በዚህም በኢትዮጵያ የመፅሀፍ ታሪክ ውስጥ በጥቂት ጊዜያት ውስጥ በተደጋጋሚ በመታተም ታሪክ የሰራ መፅሀፍ ነው፡፡ ይህ … [Read more...] about ፕሮፌሠር ፍቅሬን ለቀቅ ቧልትህን ጠበቅ

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

የካቲት 66 መሪ ኮከቡን ያጣ አብዮት

February 23, 2017 02:26 am by Editor 2 Comments

የካቲት 66 መሪ ኮከቡን ያጣ አብዮት

(የካቲት 66 ሕዝባዊ አብዮት 43ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ) ኢትዮጵያ ሀገራችን ታዳጊ ሀገሮችን በተለይ አፍሪካን እንደ ቅርጫ የተቀራመቱት ቅኝ ገዥዎችና ወራሪዎችን ጥቃት መክታ የግዛት አንድነቷንና ሉዓላዊነቷን መጠበቅ ብቻ ሳይሆን ለማንም ባዕዳን ወራሪ ኃይል ሳትደፈርና ሳትገዛ የኖረች የማንነታችንና የክብራችን መግለጫ ናት። ዮሐንስ በመተማ፣ ቴዎድሮስ በመቅደላ፣ ምኒልክ በአድዋ እየተባለ የሚነገርላቸው፣ የሚጻፍላቸው፡ የሚዘፈንላቸው ነገስታቶች በሀገር አንድነትና በኢትዮጵያዊነት ማንነት ወራሪን ያሳፈሩና ዓለምን ያስደነቁ ኢትዮጵያዊነት የክብርና የአንድነት ተምሳሌትነቷን ያስፃፉና ያስተረኩ እስከዛሬም ሆነ ወደፊት ይህ ማንነታቸውን ታሪክ የሚያወሳላቸው ነገስታት ናቸው። በነዚህ ነገስታቶች የአገዛዝ ዘመን የሀገር አንድነትንና የግዛት ነፃነትን በማስከበር ደረጃ በየጊዜው ስማቸው የሚጠራ … [Read more...] about የካቲት 66 መሪ ኮከቡን ያጣ አብዮት

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

አድማሱ “ዛፍ” በቆረጠበት ጊዜ – (የዩኒቨርሲቲው ሥነ ውበታዊ ክስመት)

February 17, 2017 03:20 am by Editor 1 Comment

አድማሱ “ዛፍ” በቆረጠበት ጊዜ – (የዩኒቨርሲቲው ሥነ ውበታዊ ክስመት)

“እና - እንደኔና እንዳንቺው የውበት ዐይኑ የታወረ፣ እግረ ኅሊናው የከረረ፤ ባሕረ ሐሳቡን ያልታደለ፣ የውበት ዐይኑ የሰለለ፣ ሰማይ ጨለማ ነው እንጂ አበባ እኮ አይደለም አለ፡፡ ያልታደለ፤…” (“እሳት ወይ አበባ”) “እና - እንደኔና እንዳንቺው የውበት ዐይኑ የታወረ፣ እግረ ኅሊናው የከረረ፤ ባሕረ ሐሳቡን ያልታደለ፣ የውበት ዐይኑ የሰለለ፣ ሰማይ ጨለማ ነው እንጂ አበባ እኮ አይደለም አለ፡፡ ያልታደለ፤…”    (“እሳት ወይ አበባ”) መግቢያ ታኅሣሥ 29 ቀን፣ 2009 ዓ.ም. በዓለ ገና፤ የአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲን ዕድገትና ደረጃን በሚመለከት በጋዜጠኝነትና ኮሚዩኒኬሽን ትምህርት ቤት በሚያስተምር ግለሰብ ዋና የመረጃ ሰጪነት፣ ዘጋቢ ፕሮግራም በኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን ተላልፎ ነበር፤ የፕሮግራሙ አቀራረብም፣ የዩኒቨርሲቲውን ፕሬዝዳንት አድማሱ ጸጋዬን … [Read more...] about አድማሱ “ዛፍ” በቆረጠበት ጊዜ – (የዩኒቨርሲቲው ሥነ ውበታዊ ክስመት)

Filed Under: Opinions, Social Tagged With: Left Column

አዲስ እንደ ቬኒስ

February 14, 2017 03:04 am by Editor Leave a Comment

አዲስ እንደ ቬኒስ

… [Read more...] about አዲስ እንደ ቬኒስ

Filed Under: Literature, Social Tagged With: Left Column

ሌላ አደገኛ የጦርነት አዋጅ በወገናችን ላይ ታወጀ!

February 13, 2017 01:16 pm by Editor 24 Comments

ሌላ አደገኛ የጦርነት አዋጅ  በወገናችን ላይ ታወጀ!

በማህበረሰባችን መካከል ወልደህ ሳም የሚባል የተለመደ ምርቃን ነበር፤ ከአንደበት የሚወጣ ቃል ደግሞ በረከትን ወይም መርገምን ሊያስከትል እንደሚችል ይገመታል፤ በምድራችን ውስጥ ልጆች በጤና ተወልደው እንዲያድጉ ወላጆች የልጆቻቸውን የጤና ስጋት ለመቀነስ ሲሉ ገና ከእርግዝና በፊት ጀምሮ ገድል ከማሳዘልና እትፍ እትፍ ከሚሉ ሰዎች እስከ የቡና ስኒ ገልባጭ መናፍስት ጠሪዎች ድረስ በልጁ የማደግና የወደፊት የሕይወት እጣፋንታ ላይ ትንቢት መሰል ሟርት እያውጁበት እንዲያድግ ይደረጋል፤ በዚህ ሁሉ ግን ሁላችንም ምንም ዓይነት የጤና ድጋፍ በሌለበትና የመናፍስት ጠሪዎች ቁጥር በርካታ በሆነባት ምድር ውስጥ ተወልደን ማደጋችን ገብቶን በማወቅ ባናከብረውም የፈጣሪ ጥበቃና ምህረት እንደሆነ አምናለሁ። ከዚህ ችግር ስፋትና ጥልቀት የተነሳ በርካታ ልጆች ተወልደው የማደግ እድል ሳያገኙ ከእናታቸው ጋር … [Read more...] about ሌላ አደገኛ የጦርነት አዋጅ በወገናችን ላይ ታወጀ!

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

ሁለት ፕሮፌሰሮች፡– ፍቅሬ ቶሎሳና ጌታቸው ኃይሌ

February 12, 2017 06:36 pm by Editor Leave a Comment

ሁለት ፕሮፌሰሮች፡– ፍቅሬ ቶሎሳና ጌታቸው ኃይሌ

በአንድ ሰኮንድ ውስጥ ስንት ነገሮች ስንት ሁኔታዎች ይታያሉ?፣ ስንት ድርጊቶች፣ ስንት ሥራዎች ይፈጸማሉ? ስንት ሰዎች ይሞታሉ? ስንት ሰዎች ይወለዳሉ? … አንድ ሰኮንድ ባዘለው ጊዜ ውስጥ ብዙ ጥያቄዎች አሉ፤ በአንድ ደቂቃ ውስጥ ባለው ጊዜ ውስጥ ቢያንስ የስድሳ ሰኮንዶችን ያህል ጥያቄዎች ይፈለፈላሉ፤ በአንድ ሰዓት ውስጥ 60*60= 3600 እነዚህ ደግሞ በ24 ሰዓት ሲባዙ 86 400 ይሆናሉ፤ የሚሆኑትንና የሚደረጉትን ነገሮች ሁሉ መዝግቦ፣ የሚነገሩትን ነገሮች ሁሉ አጣርቶ ይዞ ለሚቀጥለው ትውልድ የሚያስተላልፍ አለ ወይ? የትናንትናውን ሃያ አራት ሰዓት በዝርዝር ማስታወስ የሚችል አለ ወይ? ጊዜውና መሣሪያው ያላችሁ የሳምንቱን፣ የወሩን፣ የዓመቱን ሰኮንዶችና ያቀፉትንና ያዘሉትን ጉዳዮች አጣርታችሁ ለማወቅና ‹‹ተረቱንና ታሪኩን›› ለመለየት ሞክሩ፡፡ እንደኔ የጂኦሎጂ ሀሁ የሚያውቅ … [Read more...] about ሁለት ፕሮፌሰሮች፡– ፍቅሬ ቶሎሳና ጌታቸው ኃይሌ

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

የትግራይ ወፍ ገልብጣ ነፋች

February 10, 2017 02:04 am by Editor 3 Comments

የትግራይ ወፍ ገልብጣ ነፋች

ታሪክ እንደ ፀሃፊው ነው። ትርክትም ዕውነቱና ውሸቱ እንደ ዶናልድ ትራምፕ አገላለጽ ተለዋጭ ሀቅ (alternate fact) የለውም። ነጭና ጥቁር ነው። አንድም ዕውነት አለያም ውሸት። ተለዋጭ ዕውነት ብሎ ነገር የለም። ታሪክና ትርክት ግን ለዘመናት የውሸትና የዕውነት ገጽታ ተላብሰው ሲጓዙ መኖራቸው አይካድም። ሩቅ ሳንሄድ “የኢትዮጵያ ታሪክ የመቶ ዓመት ታሪክ ነው” የሚለውን የወያኔን ክህደት ይጠቅሷል። “ኢትዮጵያ ጀግና ኖሯት አያውቅም። የኢትዮጵያ ህዝብ እንግዳ ተቀባይ ሆኖም አያውቅ...” የመሳሰሉት የስብሃት ነጋ የተስፋ መቁረጥ ምልክቶችን ልብ ይሏል። የዛሬው አነሳሴ  እንኳ የስብሃት ነጋን ውሸት ለመዘርዘር አልነበረም። የመምህር ገብረኪዳን ደስታን የእንጨት ሽበት አበቃቀል ለመዳሰስ እንጂ። የወያኔ ሽማግሌ የለውም። ከብዙዎቹ ራስ ላይ የምታዩት ነጭ ፀጉር የዕንጨት ሽበት ነው። … [Read more...] about የትግራይ ወፍ ገልብጣ ነፋች

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

ታሪክን ምርኮኛ የማድረግ ዘመቻ

February 9, 2017 02:32 am by Editor Leave a Comment

ታሪክን ምርኮኛ የማድረግ ዘመቻ

ከሰሞኑ የፖለቲካችን የስበት ማእከል ታሪክ እና የታሪክ ባለሙያዎች ሆነዋል። ዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ የተባሉ የታሪክ ምሁር ከኢሳት ጋር ያደረጉት ቃለ ምልልስ በሶሻል ሚዲያው ከፍተኛ አዋራ ማስነሳቱ ሳያንስ፣ የተዳፈኑ የመሰሉ ጉዳዮችንም በመቀስቀስ ላይ ይገኛል። በመጀመሪያ የዶክተሩን ቃለምልልስ ከመጀመሪያ እስከ መጨረሻ በጽሞና ለመከታተል ሞክሬአለሁ። በዚህም ተጠያቂውን ዶ/ር ሃይሌ ላሬቦ ከሙያም  ሆነ ስነምግባር አንጻር የበቃ ችሎታቸውን ለመታዘብ ችያለሁ። ውዝግቡ ከተቀሰቀሰም በኋላ የኦሮሞ አክቲቪስት ነን ከሚሉ ሰዎች በተሰነዘረውን ክስ ላይ ተመስርቼ ቃለ-ምልልሱን በሂሳዊ አይን ለማየት ሞክሬአሁ። ህዝብ የተሰደበበት እና ወደ አንድ ሚዛን ያጋደለ አቀራረብ ፈልጌ ማግኘት ተቸግሬአለሁ። እንዳውም ዶ/ር ሃይሌ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ አወዛጋቢ ቦታ ስለሚይዘው ግራኝ አህመድ በጎ የሆነ እይታ … [Read more...] about ታሪክን ምርኮኛ የማድረግ ዘመቻ

Filed Under: Opinions Tagged With: Left Column

  • « Previous Page
  • Page 1
  • …
  • Page 21
  • Page 22
  • Page 23
  • Page 24
  • Page 25
  • …
  • Page 85
  • Next Page »

Primary Sidebar

በማኅበራዊ ገጾቻችን ይከታተሉን

Follow by Email
Facebook
fb-share-icon
Twitter
Tweet

Recent Posts

  • ጃዋርና በቀለ መታሠራቸው ተሰማ June 30, 2020 09:17 am
  • አገራዊ መድረክ ውጪ ድብቅ ውይይትን አንቀበልም June 17, 2020 06:57 am
  • ዴክሳሜታሶን! የኮሮና መድሀኒት June 17, 2020 06:49 am
  • የሰኔ 14ቱ ቀለበታዊ የፀሃይ ግርዶሽ በኢትዮጵያ! June 17, 2020 06:38 am
  • የግብፅ የአባይን ውሃ ብቻዬን ልጠቀም ግትር አቋም ድርድር እንቅፋት ሆኗል June 10, 2020 07:15 am
  • የቴድሮስ “ሥልጣን” – የመጨረሻው መጀመሪያ!? April 12, 2020 02:48 am
  • በብዛት የትግራይ ተወላጆች የሚጠቀሙበት የኤርትራ ስደተኛ ካምፕ ሊዘጋ ነው March 18, 2020 08:37 pm
  • እየተፈረካከሰ ያለው አንጋፋው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ March 18, 2020 08:09 pm
  • ኮሮና አዲስ ጉድ መዘዘ – ከቻይና በፊት በአሜሪካ ቁጥራቸው የማይታወቅ ሰዎችን ቀጥፏል March 16, 2020 11:41 pm
  • የኮንዶሚኒየም ቤቶች በደላሎችና በመመሪያ ሰጪዎች ኔትዎርክ እየተቸበቸበ ነው! ታከለ የት ናቸው? March 9, 2020 10:18 am
  • ኤርሚያስ ለገሠ ከባለአደራ ተባረረ March 9, 2020 08:09 am
  • ድፍድፍ ሲቀል ይንሳፈፋል፤ ምሁር ሲዘቅት ይመራል፥ March 7, 2020 11:24 pm
  • ኢትዮጵያዊ ምን ይመስላል? በምንስ ይመሰላል? March 7, 2020 10:29 pm
  • WHY I WROTE “MONEY, BLOOD AND CONSCIENCE” March 4, 2020 11:15 pm
  • አድዋ፤ የጥቁር ሕዝብ ድል! March 2, 2020 11:24 am
  • ፊታውራሪ ገበየሁ ገቦ (አባ ጎራው) March 2, 2020 11:12 am
  • የኦነግ ሁለት መልክና ሦስት ግብሮች – ቃርሚያው ኃይል ቅጥር ነፍሰገዳይ ሆኗል February 25, 2020 11:26 pm
  • በቡራዩ “የጃል ማሮ” ፎቶ ጨረታ አፈናከተ፤ “ቡራዩ ሆኖ ከሃዲን ማሞካሸት አይቻልም” ነዋሪዎች February 17, 2020 09:13 pm
  • “ዲቃላ” የፍረጃ ፖለቲካ በኦሮሚያ የኃይል አሰላለፉን እየቀየረ ነው February 13, 2020 11:58 pm
  • “ከዚህ በኋላ ማናቸውንም በወንጀል ድርጊት ውስጥ የሚሳተፉ አካላትን” አንታገስም – ጠቅላይ ዐቃቤ ሕግ February 13, 2020 05:07 pm
  • “እኛ ማንም ተሳዳቢ እንዲመጣብን አንፈልግም” የጅማ ነዋሪ February 13, 2020 09:28 am
  • “ወላጆቻችሁ ሰላማዊ ሰልፍ በሕዝቡ ያስደርጉልን” – አጋቾች February 11, 2020 07:53 pm
  • “ወንጀል የፈጸመም ያስፈጸመም ተይዞ ለህግ ይቀርባል፤ ምርመራም ተጀምሯል” February 11, 2020 06:59 pm
  • ጃዋር ወደ መጨረሻው “የትግል” ስልቱ – አማራን ማበጣበጥ! February 10, 2020 11:54 pm

ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣን በኢሜይል ለማግኘት ይመዝገቡ Subscribe to Golgul via Email

ከዚህ በታች ባለው ሣጥን ውስጥ የኢሜይል አድራሻዎን ያስገቡና “Subscribe” የሚለውን ይጫኑ፡፡
Enter your email address to receive notifications of new posts by email.

Copyright © 2026 · Goolgule