በግንቦት 20 ዋዜማ ዋልታ ቴሌቪዥንን እያየሁ ነው። ጋዜጠኛው ዝግጅቱን ከአመት አመት በማይቀየሩት መፈክሮች (ለምሳሌ "ግንቦት 20 የህዝቦች ሁሉ የዘመናት ጥያቄ ምላሽ ያገኘበት ቀን ነው) ጀመረና፣ ዛሬም በጭንቅላቴ ውስጥ የሚፈነጩትን ጥያቄዎች ዘርዝሬ ለማሰብ እንኳን እድል ሳይሰጠኝ፣ "ከግንቦት 20 ወዲህ የተወለዱ ልጆች ስለዚህ ቀን ምን ያውቃሉ?" ብሎ ለመጠየቅ በየትምህርት ቤቱ መዞር ጀመረ። የ17 አመቷ ቆንጅዬ ልጅ በፍፁም የራስ መተማመን፣ " እኛ ባንደርስበትም በአባቶቻችንና በእናቶቻችን ላይ ላይ የነበረው ጭቆና የቀረበት ቀን ነው" አለች። ከልጅቱ በኋላ አንድም ሳያነቅፋቸው ቀኑን በኢቲቪኛ፣ በፋናኛ እና በዋልታኛ የሚተነትኑ ወጣቶችን ሳይ ቆይቼ፤ ሌላ የ18 አመት ልጅ ብቅ ብሎ " ግንቦት ሃያ ባይኖር እኔም እዚህ አልገኝም ነበር" ሲል ውሃዬን ተጎንጭቼ ዋልታን … [Read more...] about “ዕድሜ ለግንቦት ሃያ…”
Left Column
የሚንተከተከው የአፍሪካ ቀንድ አካባቢና አንድምታዎቹ!
ጋምቤላ እና ብዙ ዋጋ የተከፈለበት ኦጋዴን አደጋ ላይ ናቸው! ኦጋዴን ተገንጥሎ ወደ ሞቃዲሾ እንዲጠቃለል መለስ ዜናዊ ፈርሟል። የሰነዱ ግልባጭ እንግሊዞች እጅ አለ። ወያኔ በሶስት አቅጣጫ እንደ ቆዳ የተወጠረ ቡድን ነው ሲባል ፩ ለዘመናት ሲተዳደርበት የኖረው ኢህአዴግ በሚለው ማእቀፍ ውስጥ የነበረው የአሽከርና የሎሌ ግንኙነት ማብቃቱና በራሱ በህወሃት መካከል ያለው የሃይል ክፍፍል ያመጣው አጠቃላይ የስርአቱ አደጋ መሆኑ፣ ፪ ለረጅም ግዜ ሞቅ ቀዝቀዝ ሲል የነበረው ህዝባዊ ተቃውሞ መልኩን ቀሮ ወደ ማይመለስ ህዝባዊ ተጋድሎ ማደጉና ከህዝባዊ ተጋድሎው ጀርባ ያሉት ነፍጥ ያነሱትን ድርጅቶች የመገዳደር ወይንም ችግሩን በፖለቲካዊ ውይይት ለመፍታት አቅም የማጣቱ ምክንያት ሲሆን ፫ኛው ክንፍ ደግሞ በምስራቅ አፍሪካ ላይ የተፈጠረው አለም አቀፍ የሃይል አሰላለፍ ላይ "በዚህ ሰፈር … [Read more...] about የሚንተከተከው የአፍሪካ ቀንድ አካባቢና አንድምታዎቹ!
ኢትዮጵያዊ ነኝ!!
አርነት ! _ የጥቁር ምድር አርማ ፤ ልዕልና ! _ የጥቁር ክብር ማማ፤ የጥቁር ደም - የጥቁር ዘር፤ የጥቁር ብቃይ - ከጥቁር አፈር፤ አንደበት !_ የፍሰሃ ቃል፤ ፋና ወጊ !_ የጥቁር ቀንዲል፤ አብሳሪ !_ የጥቁርን ልዕልና - የጥቁርን ድል ፤ ምንጭ ! _ የሰው ልጅ ዘር ግኝት፤ ማህተም ! _ የጥቁር ሕዝብ ዕሴት፤ ማተብ ! _ የሰው ልጆች ዕምነት፤ የክርስቲያን፤ የእስላሙ፤ _ የይሁዲው ቤት፤ ኢትዮጵያዊ ነኝ ! _ ነፃነተ ዖሪት :: ቀሪውን የአሥራደው ግጥም ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ … [Read more...] about ኢትዮጵያዊ ነኝ!!
ሞተውም ይፈራሉ
ፕሮፌሰር አሥራት ወልደየስ ከ1920ዎቹ ትውልዶች የቀለም ቀንድ፣ የአገርና የሃይማኖት ፍቅር፣ የአንድነትና የነፃነት ቀናዒ ከነበሩት አንዱ እንደሆኑ ይታወቃል። አሥራት ሞትን ታግለው፣ ድል እየነሱ የአያሌ ኢትዮጵያውያንን ሕይዎት ሲታደጉ የኖሩ፣ ምርጥ የቀዶ ጥገና ሐኪም እንደነበሩ ሕያው ታሪካቸው ያስረዳል። በኢትዮጵያ ታሪካዊ ጠላቶች በተገዙት ሽዕቢያና ወያኔ ትብብር፣ የአገራችን ዳር ድንበር ሲቆራረስ፣ ሰንደቅ ዓላማችን ሲራከስ፣ ቀይባሕር የባዕድ እንዲሆን ሲደረግ፣ ሕዝቡ በነገድ ተከፋፍሎ ዓይንና ናጫ እንዲሆን ሕገ መንግሥታዊ ዕውቅና ሲሰጥ፣ አሥራት ይህ ሊሆን አይገባውም በማለት ከተሰበሰቡት የነገድ ድርጅቶች መካከል ድምፃቸውን ያሰሙት እርሳቸው ነበሩ። ቀጥሎም ዐማራን ለማጥፋት ዓላማው አድርጎ የተሰለፈው ወያኔና ጓደኞቹ በሐረርጌ፣ በአርሲ፣ በወለጋ፣ በኢሉባቡር፣ በወልቃይት፣ ጠገዴ፣ … [Read more...] about ሞተውም ይፈራሉ
US Lobbying Firm (SGR) Cozy with a Ruthless Dictatorial Regime in Ethiopia For 1.8 Million Dollars
Lobbying Firms in the US are known to represent big corporations like oil, construction, food manufacturing and pharmaceutical industries, trying to persuade lawmakers to support business friendly legislations. As this is a controversial practice, politicians running for office do not want to be associated with Lobbying firms. In fact, it was a major discussion topic during the 2016 presidential election season for both candidates. The main reason for politicians to discredit lobbying firms … [Read more...] about US Lobbying Firm (SGR) Cozy with a Ruthless Dictatorial Regime in Ethiopia For 1.8 Million Dollars
የጃንሆይ እናት!
ነገሩ ትንሽ ቆየ። እኔ ግን በሆነ አጋጣሚ በቅርቡ ነው ቃለ ምልልሱን የሰማሁት። ተስፋዬ ገብረአብ አዲስ ስላሳተመው - “የጀሚላ እናት” መጽሃፍ፤ ከጋዜጠኛ በፍቃዱ ሞረዳ ጋር አጭር ቃለ ምልልስ አድርጎ ነበር። በትክክል እንዳዳመጥነው ከሆነ፤ “የቀዳማዊ ኃይለስላሴ እናት ስም ጀሚላ ነው፤ አንድ ወገናቸው ስልጤ ጉራጌ ነው - በሌላ ወገን ኦሮሞ ናቸው።” ይለናል። በመቀጠልም፤ “የጀሚላ እናት በአቶ በዛብህ ተጠልፈው ነበር። አቶ በዛብህ ከምኒልክ ጋር በጦርነት ሞቱ። የቀዳማዊ ኃይለስላሴ ወይም የጀሚላ እናት እልፍኝ ውስጥ፤ በአጼ ምኒልክ ተገደሉ።” የሚሉና ሌሎች ተዘርዝረው የማያልቁ የልብወለድ ነገሮች በመጽሃፉ ውስጥ ማካተቱን በቃለ ምልልሱ ላይ ሰማን። ወደ ኋላ በመመለስ ‘በወቅቱ ምላሽ የሰጠ ሰው ይኖር ይሆን?’ በማለት አንዳንድ ድረ ገጾችን ብመለከት፤ በዚህ የተዛባ ታሪክ ምክንያት… … [Read more...] about የጃንሆይ እናት!
ፍትህን ሰቀለው በፍትህ ስም የፕሮፓጋንዳ ዳንኪራ – የጨለማው ሳምንት!!
የ“ፍትህ” ወይስ የጨለማ ሳምንት? (ርዕሰ አንቀጽ) “ገንዘብ ሲናገር ፍትህ ጸጥ ይላል!” ይህ የተጻፈው በአንድ የጎንደር እስር ቤት ውስጥ ነው። የተጻፈው በግድግዳ ላይ ሲሆን በብዕር ወይም በቀለም አይደለም። ፍትህ ከተጓደለባቸው አንዱ የእጁን ጣት በመብጣጥ በደሙ ነው። ፍትህ የተዛባባቸው ይህንኑ አባባል ልክ እስር ቤት እንደገቡ ይሳለሙታል። በብዙ የአገሪቱ ማጎሪያዎች ውስጥ ተመሳሳይ ስሜት ገላጭ ሃረጎች ይጻፋሉ። ፍትህን አደባባይ ሰቅለው በምስኪኖች ህይወት ለሚጫወቱ ይህ ሁሉ ስላቅ ነው። ፍትህን አደባባይ ሰቅለዋት፣ በፍትህ ስም እየማሉ በድግስ ሊያሽካኩ ይወዳሉ። ፍትህ የዜጎች ሁለንተናዊ ህይወታቸው ትርጉም የሚያገኝበት ውድ ጉዳይ ነው። ይህንን ሃቅ የበረሃው አባዜው አልለቅ ያለው ህወሃት ጥንቅቆ ያውቀዋል። ሊክደውም አይችልም። ለዚህም ነው “ህገ መንግስት፣ ህግ፣ አዋጅ፣ የሰብዓዊ … [Read more...] about ፍትህን ሰቀለው በፍትህ ስም የፕሮፓጋንዳ ዳንኪራ – የጨለማው ሳምንት!!
“ደሸት” የብርሃን እውነት!
“ደሸት” የብርሃን እውነት! የማጂ፣ የጂማ፣ የመንዲ፣ የመደባይ አባት የማራ፣ የዥማ፣ የገንቲ፣ የአሬቲ ... አያት የአማራው፣ የኦሮሞው፣ ... የዘር ግንድ አውራ የመተሳሰሪያ እውነተኛ ምንጭ አሻራ! “ደሸት” ኢፋ ዹጋ ፍጥረተ ማለዳ የዘር ሀረግ ገመድ ምስጢራዊ ጓዳ አባ ቃሉ አባ ውሉ አያ ፍቅሩ ትስስሩ ዘረ ሸጋ ኢፋ ዹጋ መሆንህን አምኖ አማራ ኦሮሞ ስምህን በስሙ አትሞ “ደ”ን ደግ ብሎ አንብቦ “ሸ”ን ሸበበ ብሎት አንግቦ “ት”ን ትስስር ይለዋል ውልደቱን ከትቦ “ደሸት” የዘር ምንጩ አባ እቅጩ ስመ ክብሩ ውስጠ ምስጢሩ “ደሸት” የብርሃን እውነት! (ኢፋ ዹጋ!) ዘሩን ሲያበዛ ሲዘረጋ ማጂ፣ ጂማ፣ መንዲ፣ መደባይ ብሎ ሰይሞ የዘር ሲሳይ መደባይ ስሙን ከስሙ … [Read more...] about “ደሸት” የብርሃን እውነት!
የእግዚአብሔር መልእክት በነቢዩ ኢሳይያስ በኩል
"ኑና እንዋቀስ ይላል እግዚአብሔር፤ ኃጢአታችሁ እንደአለላ ብትሆን እንደአመዳይ ትጸዳለች እንደደምም ብትቀላ እንደባዘቶ ትጠራለች፤ እሺ ብትሉ ለእኔም ብትታዘዙ የምድርን በረከት ትበላላችሁ፤ እንቢ ብትሉ ግን ብታምጹም ሰይፍ ይበላችኋል፤ የእግዚአብሔር አፍ ይህን ተናገሮአልና፡፡" ኢሳ. 1/18. በእግዚአብሔር ለሚያምን ሰው፣ እግዚአብሔር ሁልጊዜም፣ ለዘለዓለም ሙሉና የማይወዳደሩት ኃይል እንዳለው ለሚያምን ሰው፣ ለእግዚአብሔር ትናንትም፣ ዛሬም፣ ነገም አሁን መሆኑን ለሚያምን ሰው "ኑና እንዋቀስ" (በእንግሊዝኛው "come now let us reason together") ማለት ለእግዚአብሔር ምን ያህል መውረድ እንደሆነ መገንዘብ የሚዳግት አይመስለኝም፤ የእንግሊዝኛው ትንሽ ሻል ያለ መስሎ "ኑና እንከራከር" የሚል ቢሆንም ከመጨረሻው የላይኛው ዳኛ ጋር መከራከር የሚችለው ማን ነው? እግዚአብሔር … [Read more...] about የእግዚአብሔር መልእክት በነቢዩ ኢሳይያስ በኩል
“ጠርጥሮ የሚይዝህ፤ የሚመረምርህ፤ ዓቃቤ ሕግ ሆኖ የሚከስህ፤ ዳኛ ሆኖ የሚፈርድብህ፤ ሽማግሌ ሆኖ ይቅርታ ጠይቅ የሚልህ፤ [በሙሉ] ህወሃት ነው” ሃብታሙ አያሌው
ሃብታሙ አያሌው ከአዲስ ድምጽ ጋር ያደረገው ቃለምልልስ … [Read more...] about “ጠርጥሮ የሚይዝህ፤ የሚመረምርህ፤ ዓቃቤ ሕግ ሆኖ የሚከስህ፤ ዳኛ ሆኖ የሚፈርድብህ፤ ሽማግሌ ሆኖ ይቅርታ ጠይቅ የሚልህ፤ [በሙሉ] ህወሃት ነው” ሃብታሙ አያሌው










![“ጠርጥሮ የሚይዝህ፤ የሚመረምርህ፤ ዓቃቤ ሕግ ሆኖ የሚከስህ፤ ዳኛ ሆኖ የሚፈርድብህ፤ ሽማግሌ ሆኖ ይቅርታ ጠይቅ የሚልህ፤ [በሙሉ] ህወሃት ነው” ሃብታሙ አያሌው](https://staging.goolgule.com/wp-content/uploads/2016/07/abraha-and-habtamu-300x200.jpg)